Телеграм канал 'WALTA TV'

WALTA TV


45'197 подписчиков
4'449 просмотров на пост

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc

Детальная рекламная статистика будет доступна после прохождения простой процедуры регистрации


Что это дает?
  • Детальная аналитика 5'674'934 каналов
  • Доступ к 1'533'798'153 рекламных постов
  • Поиск по 5'980'439'538 постам
  • Отдача с каждой купленной рекламы
  • Графики динамики изменения показателей канала
  • Где и как размещался канал
  • Детальная статистика по подпискам и отпискам
Telemetr.me

Telemetr.me Подписаться

Аналитика телеграм-каналов - обновления инструмента, новости рынка.

Найдено 13691 пост

ሕዝቡ በሰላም፣ በአንድነትና በልማት ላይ በማተኮር እጅ ለእጅ ተያይዞ መስራት አለበት - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ሚያዝያ 30/2016 (አዲስ ዋልታ) ሕዝቡ በሰላም፣ በአንድነትና በልማት ላይ በማተኮር እጅ ለእጅ ተያይዞ መስራት አለበት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

በነቀምቴ ከተማ ወለጋ ስታዲየም የለውጡን መንግስት የሚደግፍ ሰልፍ ''ወለጋ የሰላምና የብልጽግና ምድር'' በሚል መሪ ሃሳብ የአራቱ ወለጋ ዞኖች ነዋሪዎች የተሳተፉበት ሰልፍ ተካሂዷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ህዝቡ በሰላም፣ በአንድነትና በልማት ላይ እንዲያተኩር ጥሪ አቅርበዋል።

ሰላም የሁሉ ነገር መሰረት መሆኑን ጠቅሰው ''ሰው ውስጡ ሰላም የሆነ፣ ሀገሩ ሰላም ከሆነ ልክ እንደ ዛሬ በፍቅርና በወንድማማችነት መንፈስ ተገናኝቶ መለያየት ይችላል'' ነው ያሉት።

ከሁሉም በላይ ለልማት፣ የተለያየ ሀሳብ ለማመንጨት አንድነት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ትውልዱን የሚጎዳ ነገር ከማድረግ በመቆጠብ በመመካከር አንድነትን ማጽናት ይገባል" ብለዋል።

ከኢኮኖሚ አኳያ ከለውጡ በፊት ብዙ ችግር ተደቅኖ እንደነበር አንስተው ከለውጡ በኋላ ግን በብዙ ችግሮች ውስጥ ትልቅ የኦኮኖሚያዊ ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑን አብራርተዋል።

በለውጡ ዓመታት በተሰራ ሥራ ግብርናንና ከተማን የሚለውጥ፣ ሀገር የሚያሸግር ኢኮኖሚ እየተመዘገበ መሆኑን አስረድተዋል።

''የጀመርነውን ስራ ከግብ ለማድረስ የሚያስቆመን ሃይል አይኖረም፣ በንጹህ ልባችን ሀገር ለመለወጥ ነው እየሰራን ያለነው'' ብለዋል፡፡
👇👇
https://shorturl.at/bQZ24
👍 7
👏 3
Изображение

የአዲስ ዋልታ የትንሳኤ በዓል የወርቅ ደረጃ አጋር!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ

🙏 7
👍 1
Изображение
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ነቅምቴ ገቡ

ሚያዝያ 30/2016 (አዲስ ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች ነቅምቴ ገቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከልዑካን ቡድናቸው ጋር ነቀምቴ የገቡት በወለጋ እየተካሄደ ባለው ሀገራዊ ለውጡን የሚደግፍ ሕዝባዊ ሰልፍ ላይ ለመገኘት ነው፡፡

ልዑክ ቡድኑ በነቀምት አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን ልዑኩ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘው ተሻገር እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት አመራሮችን ያካተተ ነው፡፡

በድጋፍ ሰልፉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች የተገኙ ስኬቶችን የሚገልጹ መልዕክቶች እየተላለፉ ሲሆን በወለጋ የተለያዩ አካባቢዎች የተወጣጡ የኅበረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
👍 18
😢 5
🙏 4
👎 3
👏 1
Изображение

ዛሬ የማክሮኢኮኖሚ ኮሚቴ ከአገርበቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ አፈፃፀም ጋር የተያያዙ ሰፋ ያለ መጠነርዕይ ያላቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል። - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

👍 16
👎 3
😢 3
Изображение

ዛሬ ምሽት በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፒ.ኤስ.ጂ ከዶርትመንድ ይጫወታሉ

ሚያዚያ 29/2016 (አዲስ ዋልታ) በሁለተኛው ዙር የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ መርኃ ግብር የፈረንሳዩ ፒ.ኤስ.ጂ ከዶርትመንድ ጋር ምሽት 4 ሰዓት ይጫወታሉ።

ሁለቱ ቡድኖች በኢግናል ኢግና ፓርክ ባደረጉት በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ዶርትመንድ 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል።

የፈረንሳዩ ሊግ ዋን ሻምፒዮናው ፒ.ኤስ.ጂ ውጤቱን ቀልብሶ ወደ ፍጻሜ ለማለፍ ጠንክሮ እንደሚቀርብ ሲጠበቅ ዶርትመንድ በበኩሉ በውድድሩ ጥሩ አቋም እያሳዬ በመሆኑ ለፈረንሳዩ ቡድን ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።

👍 9
Изображение

#ከተሞቻችን
ጅግጅጋ

የምስራቋ ፈርጥ፣ የብዙኃን መናህሪያ እና የእንግዳ ተቀባይ ሕዝብ ምድር የሆነችው የጅግጅጋ ከተማ ከመዲናችን አዲስ አበባ በስተምስራቅ አቅጣጫ 618 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡

በአብዛኛው ሜዳማ ተፈጥሯዊ የመሬት ገፅታ የተጎናጸፈችው ይህች ከተማ የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ዋና መቀመጫ ናት፡፡

ከባህር ጠለል በላይ 1ሺሕ 609 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ጅግጅጋ ሞቃታማ የአየር ንብረት አላት፡፡ ከተማዋ በ1916 ዓ.ም በፊታውራሪ ተክለ ሐዋሪያት ተክለ ማርያም እንደተመሰረተች ይነገራል።

ጅግጅጋ የሚለው ቃል መነሻው ሕዝቡ የውሃ ጉድጓዶች ሲቆፍር ከተሰሙ የተለያዩ የ"ጂግ-ጂግ" ድምፆች መሆኑ ይጠቀሳል፡፡ በአካባቢው ማኅበረሰብ "ላአ" ተብሎ ይጠራ እንደነበር እና ይህም በሶማሌ ቋንቋ "ማራኪ እይታ" ማለት እንደሆነ ይነገራል።

የካራማራ ሰንሰለታማ ተራራ ከጂግጂጋ ከተማ በ12 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ውብ እና አረንጓዴ መልከዓ ምድራዊ ተፈጥሮ ያለው ይህ ተራራ የካራማራ የድል ብስራት ህያው ምስክርም ጭምር ነው።

ጅግጅጋ በአራት ክፍለ ከተማ እና ሀያ ቀበሌዎች የተዋቀረች ስትሆን ክፍለ ከተማዎቿ ካራማርዳ፣ ዱዳሂዲ፣ ጋራብአሴ እና ቆርዴሬ ይባላሉ፡፡
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid02kXrPXbE7B9Zo2QiSZStaASibiaWH4tqHiUFMShGMcrqfnkZZ5YcUcwT7SffMBtP8l

👍 11
🙏 3
Изображение

የጽዱ ጤና ተቋማት ንቅናቄ ተጀመረ

ሚያዚያ 29/2016 (አዲስ ዋልታ) የጤና ሚኒስቴር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የ“ጽዱ ኢትዮጵያ” ንቅናቄ አካል የሆነውን የጽዱ ጤና ተቋማት ንቅናቄ አስጀምሯልለ።

“ፅዱ የጤና ተቋማት ለተሟላ ጤንነት” በሚል መሪ ሀሳብ ነው ንቅናቄው የተጀመረው።

ንቅናቄው ምቹ የጤና ተቋማትን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን የገለፁት የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ በዓለም የጤና ድርጅት (WHO) በፈረንጆች 2030 ለማሳካት ከታቀዱት እቅዶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል።

ንቅናቄው በተለይም የእናትና የህፃናትን ሞት ከመቀነስ አኳያ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።

ችግሩን በመቅረፍ ረገድ የጤና ተቋማት የአንበሳውን ድርሻ የሚወስዱ እንደመሆኑ መጠን በአለርት አህሪ የጤና መንደር እና በቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል የተጀመረው ይህ ንቅናቄ በተለያዩ የሀገራችን ክፍል በሚገኙ የጤና ተቋማት ላይም እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

በንቅናቄው ላይ የጤና ተቋማት እድሳት፣ የመፀዳጃ ቤት ግንባታ፣ ለአቅመ ደካሞች የተገነቡ ሶስት መኖሪያ ቤቶች የማስረከብ እቅድ ተካቷል።

በፈቲያ ሁሰን

👍 12
🙏 2
👎 1
👏 1
Изображение

የአዲስ ዋልታ የትንሳኤ በዓል ሁለተኛ ደረጃ አጋር

ፍል ውሃ አገልግሎት ድርጅት

👍 13
Изображение
ቅዱስ ጊዮርጊስ አሠልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታን በጊዜያዊነት አገደ

ሚያዝያ 28/2016 (አዲስ ዋልታ) የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ የዋናው ቡድን ዋና አሠልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታን ከማሰልጠን ተግባራቸው በጊዜያዊነት ማገዱ ተገለጸ፡፡

የስራ አመራር ቦርዱ ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የዋናውን ቡድን እንቅስቃሴ የገመገመ ሲሆን በዚህም አሠልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ የዋናው ቡድን ዋና አሠልጣኝ እና አሠልጣኝ ውብሸት ደሳለኝ የበረኞች አሠልጣኝ ተለዋጭ መመሪያ እስኪሰጥ ድረስ ከማሰልጠን ተግባራቸው ታግደው እንዲቆዩ ወስኗል።

በምትካቸውም አሠልጣኝ ደረጀ ተስፋዬ የዋናው ቡድን ምክትል አሠልጣኝ ዋና አሠልጣኝ ሆነው ከሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በጊዜያዊነት እንዲያሠለጥኑ ተወስኗል፡፡

አሠልጣኝ ሳምሶን ሙሉጌታ ደግሞ የወጣት ቡድኑ ዋና አሠልጣኝ ምክትል አሠልጣኝ ሆነው በጊዜያዊነት እንዲያሠለጥኑ መወሰኑን ከክለቡ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡
👍 11
Изображение

የአዲስ ዋልታ የትንሳኤ በዓል የወርቅ ደረጃ አጋር!

የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ

🙏 3
👍 1
Изображение

#አጀንዳ+

የኢትዮጵያ ፈተናዎች እና የትንሳዔዋ እንቅፋቶች፣ ስኬታማው የኢትዮጵያ የፈተና ውስጥ ጉዞ

https://youtu.be/ds401thssjw
ዛሬ ምሽት ይጠብቁን

👍 8
👎 2
በሀላባ ዞን በጎርፍ የተወሰዱ ሰዎችን ለማግኘት እየተደረገ ያለው ፍለጋ ቀጥሏል

ሚያዝያ 28/2016 (አዲስ ዋልታ) በሀላባ ዞን ሁለት ወረዳዎች በተከሰተው የጎርፍ አደጋ የአምስት ሰዎች ህይወት እንዳለፈና የሁለቱን አስክሬን ለማግኘት እየተደረገ ያለው ፍለጋ ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ገለጸ።

የሀላባ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ሐሩና አሕመድ ለአዲስ ዋልታ ዲጂታል ሚዲያ እንደገለጹት ከሁለት ቀናት በፊት ሚያዝያ 26/2016 ዓ.ም በዞኑ ዌራ ዲጆ እና አቶቲ ኡሎ ወረዳዎች በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ የጎርፍ አደጋ ተከስቷል።

በድንገት በተፈጠረው የጎርፍ አደጋ ከአምስት ሰዎች ህይወት ማለፍ በተጨማሪ 14 ፍየሎች መሞታቸውንና 30 ሄክታር ላይ የለማው ሰብል መውደሙን አመላክተዋል።

በተጨማሪም በቁሊቶ ከተማ በሚገኘው አጠቃላይ ሆስፒታል ጎርፍ በመግባት በህክምና መሳሪያዎች ላይ ባደረሰው ጉዳት በአገልግሎቱ ላይ መስተጓጎል መፍጠሩን ተናግረዋል።

ህይወት ካለፈባቸው አምስት ሰዎች ሦስቱ ልጆች ሲሆኑ ከ7 እስከ 12 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ እንደሆኑ ያመላከቱት ኃላፊው የሁለቱ ሰዎች አስክሬን እስካሁን አለመገኘቱን ጠቁመዋል።
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0T59YFUU9qVXZhrLLDLwJSew87kKuSwrxTaubYmKrv53wxGoqHDQmqeEzxEZbLdqrl
👍 16
😢 5
🙏 3
Изображение
ዳሞታ ተራራ - የወላይታ ሶዶ ውበት
#ሀገሬ

የዳሞታ ተራራ ከወላይታ ሶዶ ከተማ በስተሰሜን የሚገኝና በደን የተሸፈነ የብዘሃ ህይወት አለኝታ ነው። ተራራው ታሪካዊ፣ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ይዘት ያላቸው መስህብ ስፍራዎች የሚገኝበት ነው።

በሀገር በቀል ዕፅዋት የተሸፈነና አረንጓዴ ሸማ የለበሰው ይህ ተራራ በክፍታውና በግርማ ሞገሱ ወደ ከተማዋ የሚገቡትን ጎብኚዎች ቀልብ በመግዛትም ይታወቃል።

ተራራው የሚሸፍነው መሬት 12 ሺሕ 500 ሄክታር ሲሆን ከፍታው ከባህር ጠለል በላይ 3 ሺሕ ሜትር ነው። ዙሪያው 68 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት እንዳለውም ይነገራል።

የዳሞታ ተራራ በወላይታ ሕዝብ ዘንድ በዘርፈ ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው የሚታወቅ ታሪካዊ ስፍራ ሲሆን ከህዝቡ ታሪክና ባህል እንዲሁም ጀግንነት ጋር በማቆራኘትም ዳሞታን በሥነ ቃላቸው ያሞጋግሱታል በሙዚቃዎቻቸውም ታሪኩን ያወሣሉ።

ተራራው ከልምላሜው፣ ከዱር እንስሳትና ተፈጥሯዊ ብዝሃ ህይወት ማህደርነት ባሻገር በወላይታ ዞን የሚገኙ ወረዳዎች ስያሜዎቻቸውን ዳሞታን መነሻ አድርገው ይጠሩታል፡፡ ከእነዚህም ወረዳዎች ዳሞት ሶሬ፣ ዳሞት ወይዴ፣ ዳሞት ጋሌ እና ዳሞት ፑላሳ የሚጠቀሱ ሲሆን ለተለያዩ ቀቤሌዎችም የመጠሪያቸው መነሻ ነው የዳሞታ ተራራ፡፡
👇👇
https://shorturl.at/myIOZ
👍 17
👏 5
Изображение

በአጓጊው የ#ደሞ_አዲስ የግማሽ ፍጻሜ ውድድር በሕዝብ ድምጽ አራት ተወዳዳሪዎች በቀጥታ ወደ ቀጣዩ ዙር ሲያልፉ ሁለት ተወዳዳሪዎች ለመትረፍ ደርሰው አንዱ የቀጣዩን ዙር ተቀላቅሏል።

በዚህም መሰረት ማቲያስ ደርብ፣ እንግዳው አስፋው፣ ታረቀኝ ረጃው እና አብርሃም ኸይሩ ወደ ቀጣዩ ዙር በቀጥታ አልፈዋል።

ለመትረፍ በተሰኘው የውድድሩ ሕግ በሕዝብ ድምጽ አነስተኛ ድምጽ ያገኙት ኃ/ኢየሱስ ታደገ እና ዮሃንስ ወርቁ ስራቸውን አቅርበው በዳኞች ውሳኔ ዮሃንስ ወርቁ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል።

ኃ/ኢየሱስ ታደገ ደግሞ በዛሬው ደሞ አዲስ የውድድሩ ተሰናባች ሆኗል።

#ደሞ_አዲስ

#አዲስ_ዋልታ

👍 11
👏 2
Изображение

አጓጊው የደሞ አዲስ የቀጥታ ስርጭት የግማሽ ፍጻሜ ውድድር - አሁን 🔥 ወደ ቀጣይ ዙር የሚያልፉ ተወዳዳሪዎች በእናንተ ድምፅ ይወሰናሉ። ተወዳዳሪዎችን በአጭር የፁሑፍ መልዕክት 8970 ይዳኙ! 🎼🎹🥁🎤🎺🎷🎸🎻

#ደሞ_አዲስ

#አዲስ_ዋልታ
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/videos/813826543525101

👍 6
👏 5
🙏 1
Изображение
Изображение

Найдено 13691 пост