Телеграм канал 'WALTA TV'

WALTA TV


45'016 подписчиков
4'443 просмотров на пост

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc

Детальная рекламная статистика будет доступна после прохождения простой процедуры регистрации


Что это дает?
  • Детальная аналитика 5'579'095 каналов
  • Доступ к 1'533'798'153 рекламных постов
  • Поиск по 5'804'326'135 постам
  • Отдача с каждой купленной рекламы
  • Графики динамики изменения показателей канала
  • Где и как размещался канал
  • Детальная статистика по подпискам и отпискам
Telemetr.me

Telemetr.me Подписаться

Аналитика телеграм-каналов - обновления инструмента, новости рынка.

Найдено 13614 постов

ቲክ ቶክ ይሸጣል?

የቻይናው የቲክ ቶክ እናት ካምፓኒ ባይትዳንስ ቲክ ቶክን ለመሸጥ ምንም እቅድ እንደሌለው አስታውቋል።

አሜሪካ ቲክቶክ እንዲሸጥ ወይም በአሜሪካ ውስጥ እንዲታገድ የሚያስገድድ ሕግ ማውጣቷን ተከትሎ የቲክ ቶክ እናት ካምፓኒ ቢዝነሱን የመሸጥ ፍላጎት እንደሌለው እየተናገረ ነው።

የአሜሪካን ውሳኔ ተከትሎ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ቲክ ቶክ “ሕገ-መንግስታዊ አይደለም” ያለውን ይህንን ሕግ እስከ ፍርድ ቤት ድረስ በመሄድ እንደሚቃወም ገልጿል።

ባይትዳንስ መግለጫውን ያወጣው “ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ” በተሰኘ ድረ-ገጽ ላይ ኩባንያው በአሜሪካ ውስጥ የቲክ ቶክ ኦፕሬሽን ከሚሰጠው ስልተ ቀመር (አልጎሪዝም) ውጭ ሊሸጥ የሚችለውን እየመረመረ ነበር የሚል መረጃ ከወጣ በኋላ ነው።

ኩባንያው ባይትዳንስ ቲክ ቶክን እንደሚሸጥ አድርገው የውጭ ሚዲያዎች የሚዘግቡት ከእውነት የራቀ፤ የውሸት ወሬ ነው ሲል ማጣጣሉን ቢቢሲ ዘግቧል።

የሽያጭ ወይም የእገዳ እርምጃውን የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ረቡዕ እለት መፈረማቸው ይታወሳል…
ሙሉ መረጃውን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ👇👇
https://waltainfo.com/am/%e1%89%b2%e1%8a%ad-%e1%89%b6%e1%8a%ad-%e1%8b%ad%e1%88%b8%e1%8c%a3%e1%88%8d/

👍 13
Изображение

ጠ/ሚ ዐቢይ የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ድጋፍ ለኢትዮጵያ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንዳለው ገለጹ

ሚያዝያ 18/2016 (አዲስ ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን የሚሰጠው ድጋፍ ለኢትዮጵያ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንዳለው ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ከሆኑት ማርክ ሱዝማን እና ቡድናቸው ጋር መወያታቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም ደስታ እንደተሰማቸው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን በግብርና፣ ጤና፣ በሥርዓተ-ምግብ፣ በአካታች የፋይናንስ ሥርዓት እና በሌሎች ዘርፎች የሚሰጠው ጠቃሚ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ዕድገት ከፍ ያለ አስተዋጽዖ እንዳለውም ጠቅሰዋል፡፡

ይህን ትብብር በማላቅ እና በአዳዲስ ዘርፎች በመተባበር እንሰራለን ሲሉም አረጋግጠዋል።

👍 13
👏 2
Изображение

ጃትሮፋ - ነዳጅ ለጋሹ ዛፍ

ጃትሮፋ - ነዳጅ ለጋሹ ዛፍ ቆላማ በሆኑ ጥቂት አካባቢዎች ላይ የሚበቅል የዛፍ አይነት ነው።

ጃትሮፋ ለአማራጭ የኃይል አቅርቦት የሚውል ሲሆን እንደ መደበኛው ዲዝል ከድፍድፍ ነዳጅ ዘይት የሚገኝ ሳይሆን ከእጽዋትና ከእንስሳት ተዋጽኦ (ዘይትና ሞራ) የሚመረት ለባዮ ዲዝል ምርት ግብዓት የሚሆን ነው።

በሀገራችን ኢትዮጵያ እንደ ወላይታ ሶዶ፣ ባቲ፣ መተማ፣ ኮምቦልቻ እና በመሳሰሉ ጥቂት ቆላማ አካባቢዎች ላይ ይገኛል።

በአንዳንድ የዓለም ሀገራት በገጠራማው አካባቢ የሚኖረው ማኅበረሰብ የዛፉን ፍሬ ለምግብ ማብሰያ እንደከሰል እና ለሳሙና መስሪያነት ይገለገሉበታል።

በወርልድ ቪዥን ስር የኤፍ ኤም ኤን አር (FMNR) አድቫይዘር የሆኑት ጌታቸው ታምሩ ከአዲስ ዋልታ ዲጂታል ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቆይታ የጃትሮፋ ዛፍን ጠቀሜታ አብራርተዋል።
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid02fmetKkYfaMsbWcomMsQCXvrCSpTz5R8pyawfbTE6Bf8MM9G79qpY8eDToremBweUl

👍 12
😢 1
Изображение
የገንዘብ ሚኒስትሩ ከአሜሪካ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ

ሚያዝያ 17/2016 (አዲስ ዋልታ) የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከተለያዩ የአሜሪካ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

የ2024 የዓለም ባንክ እና አይኤም ኤፍ ስብሰባዎች ጎን ለጎን በሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የሚመራው ልዑክ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት አምባሳደር ሞሊ ፊ፣ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክል ሀመር እና የአሜሪካ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ግምጃ ቤት ምክትል ፀሐፊ ጄይ ሻምባህ ጋር ተወያይቷል፡፡

ውይይቱ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ እንዲሁም የሀገሪቱን የማክሮ ኢኮኖሚ ማዕቀፍ ለማሻሻል በሚደረጉ ማሻሻያዎች ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል።

ሁለቱ ወገኖች በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ በኩል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የሚያገግምበትን ሁኔታ ለመፍጠር፣ ሀገራዊ ትስስር እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ለማስፈን በሚያስፈልገው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ላይ መወያየታቸውን በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡
👍 21
🙏 6
👎 1
Изображение

አጓጊው ደሞ አዲስ መጪው እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ #በቀጥታ ስርጭት ለእናንተ ለተመልካቾቻችን ተወዳዳሪዎቹን ይዞላችሁ ይቀርባል።

በቀጥታ ስርጭትም ዳኞችና ተወዳዳሪዎች በተመልካቾች ድምፅ ይዳኛሉ።  በዕለቱም የተሰጣቸውን ኮድ በማስቀደም በ8970 SMS ድምጽ ይስጡ!

ያሬድ አበበ - B1
ታረቀኝ ረጃው - B3
እንግዳው አስፋው - B5
ኃይለኢየሱስ ታደገ - B6

#ደሞ_አዲስ #አዲስ_ዋልታ #music #idol

እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን 🎼

👍 6
🙏 2
👎 1
Изображение

“የሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አልዳባቢያን በመቀበሌ ደስታ ተሰምቶኛል። በውይይታችን ወቅት በቀጣናዊ የሰላም እና መረጋጋት፣ የኢኮኖሚ ትብብር፣ የሰው ኃይል ልውውጥ እና በሌሎች የጋራ ፍላጎት ጉዳዮችን አንስተናል።” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

👍 18
🙏 2
👎 1
Изображение
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

ሚያዝያ 17/2016 (አዲስ ዋልታ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 31ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
በዚህም፡-

1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የወጪ ንግድ የቀረጥ ማበረታቻ ሥርዓት አዋጅን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ለኢንደስትሪ ልማትና ኢንቨስትመንት የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳደግ፣ በወጪ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች በማበረታታት ረገድ የታዩ ውስንነቶችን ለመቅረፍ እና የዘርፉን ተዋንያን የሚያበረታታ ሥርዓት በመዘርጋት ተወዳዳሪነት ማላቅ ይቻል ዘንድ ረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም ረቂቅ ማሻሻያ አዋጁ ላይ ከተወያያ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ህብረት ስራ ኮሚሽን ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚያስከፍለውን የአገልግሎት ክፍያ ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ኮሚሽኑ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ማስፋት፣ የአገልግሎቶቹን የጥራት ደረጃ ማሻሻል፣ ብሎም የተጠቃሚውን ማህበረሰብ አቅም ባገናዘበ መልኩ አገልግሎት ለመስጠት ያወጣውን ወጪ በከፊል መሸፈን የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
👇👇
https://shorturl.at/rsJV1
👍 10
👏 1
😢 1
Изображение
ውበት የሚያበቃበት ቀን የለውም የምትለው የ60 ዓመቷ ቁንጅና ተወዳዳሪ

የ60 ዓመቷ የሕግ ባለሙያ እና ጋዜጠኛ አሌጃንድራ ማሪሳ ሮድሪጉዝ በቅርቡ የሚስ ቦነስ አይረስን ውድድር በማሸነፍ ለሚስ አርጀንቲና የቁንጅና ውድድር ብቁ ሆናለች። ውበት የሚያበቃበት ቀን የለውም የምትለው አሌጃንድራ ማሪሳ የ2024 ሚስ ዩኒቨርስ አሸናፊ ለመሆንም ቆርጣ ተነስታለች።

እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 1958 ጀምሮ በውድድሩ መሳተፍ የሚችሉት ከ18 እስከ 28 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሴቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ባለፈው ዓመት ግን የዕድሜ ገደቡ ተነሳ። ይህ ለአርጀንቲናዊቷ የ60 ዓመት ቆንጆ “ሁኔታው ለእኔ ተመቸኝ” የሚያስብል ሆነና ተሳተፈች።

አርጀንቲናዊቷ ተወዳዳሪ ከበርካታ ወጣት ቆነጃጅት ሴቶች ጋር ተወዳድራ የሚስ ቦነስ አይረስን ማዕረግ ካሸነፈች በኋላ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ አነጋጋሪ ሆናለች።

ውድድሩን ማሸነፏን ተከትሎ በመድረክ ላይ ንግግር ስታደርግ ለሁሉም ሴቶች ውበት እድሜ እንደሌለው እና እንቅፋቶችን ማፍረስ እንደምንችል ማሳየት እፈልጋለሁ ብላለች።
👇
https://shorturl.at/pxBGX
👍 19
Изображение
አየር መንገዱ ወደ ካሜሩን ዱዋላ ከተማ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ ወደ 11 አሳደገ

ሚያዝያ 17/2016 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካሜሩን የንግድና የኢኮኖሚ ማዕከል ወደ ሆነችው ዱዋላ ከተማ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ ወደ 11 ማሳደጉን ገለጸ።

በዚህም ከግንቦት 26/2016 ዓ.ም ጀምሮ በረራውን ወደ 11 ከፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት ወደ ከተማዋ 7 ጊዜ ሳምንታዊ በረራዎችን እያደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል።
👍 11
😢 2
Изображение

"የአፍሪካ ዋንጫን በ2029 ወይንም በ2031 ለማዘጋጀት እየሰራን ነው" የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጄላ መርዳሳ - አሁን 👇

https://shorturl.at/hOT48

👍 22
👎 2
Изображение
235 ሰዎችን የሚይዘው አሳንሰር (ሊፍት)
#ቴክኖ_ቅምሻ

በፊንላንድ ሊፍት ኩባንያ ኮን በ2022 በህንድ ሙምባይ በሚገኘው ጂዮ ወርልድ ሴንተር ህንፃ ውስጥ በዓለማችን የመጀመሪያ የሆነውን 235 ሰዎችን የሚይዘው አሳንሰር (ሊፍት) ገጥሞታል።

ይህ ትልቁ የመንገደኞች ሊፍት የስቲዲዮ አፓርታማ ያክላል የተባለ ሲሆን 16 ቶን የሚመዝንና በ9 የብረት ኬብሎች የተደገፈ ነው፡፡ አሳንሰሩ ሰዎችን ከማጓጓዝ በተጨማሪ ለሰርግና ለአርት ኤግዚብሽን ማሳያ እንዲሆን ተደርጎ የተሰራ ሲሆን 25.78 ስኩየር ሜትር ስፋት ያለውና ለተመልካች ውብ የሆነ እይታና የአትክልት ቦታ ያካተተ ነው።

አሳንሰሩ 18 ትላልቅ ፑሊዎች፣ 9 የብረት ኬብሎች እና በብረት ዓምዶች ላይ የተስተካከሉ ሀዲዶችን ባቀፈ አዲስ የፑሊ ጨረር ሲስተም ላይ የተሰራ ነው ተብሏል።

የዓለማችን ትልቁ የመንገደኞች አሳንሰር (ሊፍት) ልዩ ባለ አራት ፓነል የመስታወት በር፣ የመስታወት ግድግዳዎች ፓኖራሚክ እይታዎችን እና ክሪስታል-የተጣበበ ጣሪያን ያሳያል። በአምስት ፎቆች መካከል ብቻ የሚጓዝ ቢሆንም በሴኮንድ 1 ሜትር ፍጥነት በመጓዝ ሪከርድ ሰባሪው ሊፍትም ሆኗል።

ሊፍቱ ውስጥ ተጓዦች ሲደክማቸው አረፍ የሚሉበት 2 ምቹ ሶፋዎችም አሉት፡፡

የኮን ማኔጂንግ ዳይሬክተር ኢሚት ጎሳይን የዓለማችንን ትልቁን የህዝብ ማመላለሻ አሳንሰር (ሊፍት) ለደንበኞቻችን ችግር ፈች የሆነ ፕሮጀክት በመስራታችን ኩራት ይሰማናል ብለዋል፡፡
👇
https://shorturl.at/rT679
👍 17
👏 4
Изображение
በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በመምከር ከብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

የተከበራችሁ የሀገራችን ሕዝቦች፣
ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትነት ታሪኳ፣ የፖለቲካ ልዩነቶችን፣ አለመግባባቶችን እና ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ፣ በንግግር፣ በውይይት እና በሕጋዊ አግባብ የመፍታት ልምምድ የላትም። እንደ አለመታደል ሆኖ ፖለቲካችን የዜሮ ድምር ፖለቲካ ነው። በሀገራችን የተለመደው በጉልበት አሸንፎ ሥልጣን የያዘ ኃይል፣ በጉልበት ተሸንፎ ሥልጣን እስኪለቅ ድረስ ሁሉንም ጠቅልሎ የሚቆጣጠርበት እና የፈቀደውን የሚያደርግበት የፖለቲካ ባህል ነው።

የለውጡ መንግሥት ወደ ሥልጣን የመጣው በጉልበት አይደለም። ይሄም አዲስ የፖለቲካ ባህል ነው። ይሄን አዲስ የፖለቲካ ምእራፍ የሚያጸና ሌላ ሰላማዊ የፖለቲካ ባህል ደግሞ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሕዝብ ይሁንታ አግኝቶ መንግሥት በመመሥረት አሳይቷል። ከዚህም በመሻገር ልዩ ልዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላትን በመንግሥት ኃላፊነት በመመደብ፣ ኢትዮጵያ የጋራ ቤት መሆንዋን አስመስክሯል።

ሰላማዊ የፖለቲካ ሽግግር ብቻውን ግብ አይደለም። ሌሎች ግቦችን ለማሳካት መሣሪያ እንጂ። የኢትዮጵያ ችግር የአሁኑን አካሄድ በማስተካከል ብቻ አይፈታም። በታሪክ ውስጥ የወረስናቸውን ስብራቶች መጠገንም የግድ ይለናል። እነዚህን የታሪክ ስብራቶች ለመጠገን ሦስት ዓይነት መፍትሔዎች ተቀምጠዋል።
👇👇
https://shorturl.at/pBFO4
👍 20
👎 3
Изображение

የመኖሪያ ቤት ተደርምሶ ባደረሰው አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ሚያዝያ 16/2016 (አዲስ ዋልታ) በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኝ የመኖሪያ ቤት ተደርምሶ በጀርባ በሚገኝ ሌላ መኖሪያ ቤት ላይ በማረፉ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው የተከሰተው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ጠሮ መስጊድ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ መሆኑን የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አይዳ አወል ለአዲስ ዋልታ ዲጂታል ሚዲያ ገልጸዋል።

በግንባታ ላይ የነበረው የግለሰብ መኖሪያ ቤት ተደርምሶ በጀርባ በሚገኝ ሌላ መኖሪያ ቤት ላይ በማረፉ በቤቱ ውስጥ ለነበሩ ሰባት ነዋሪዎች ሕይወት ማለፍ ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።

አደጋው ሌሊት ከ10፡30 በኋላ የተከሰተ መሆኑን የገለጹት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ እስካሁን የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ጠቁመዋል።

አደጋ ለደረሰባቸው የቤተሰብ አባላት መጽናናትን ተመኝተው ኅብረተሰቡ ላይ መሰል አደጋዎች እንዳይደርሱ በህንፃ ግንባታዎች ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡

በአድማሱ አራጋው

😢 14
👍 11
Изображение

የጨረታ ማስታወቂያ

የጉምሩክ ኮሚሽን ተሽከርካሪዎች፣ ጥሬ ዕቃዎች፣ ተንቀሳቃሽ እና የሚገጠሙ ፎርክ ሊፍቶች፣ የዳይፐር ማምረቻ ማሽኖች እና መለዋወጫዎች፣ የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶች እንዲሁም በሼድ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ዕቃዎችን በሙሉ ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

የጨረታ መነሻ ዋጋው 315 ሚልዮን 671 ሺሕ 341 ብር ከ14 ሣንቲም ነው።

ተጨማሪ መረጃ ሐዋሳ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በስልክ ቁጥር 0462125396 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

👍 19
🙏 2
Изображение

በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ አርሰናል ከቼልሲ ዛሬ ምሽት ይጫወታሉ

ሚያዚያ 15/2016 (አዲስ ዋልታ) በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርሰናል በኤምሬትስ ስታዲዬም ከቼልሲ ጋር ወሳን ጨዋታ ያካሂዳሉ።

አርሰናል በ33 ጨዋታዎች በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በ74 ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን በተመሳሳይ 74 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘነው ሊቨርፑል በጎል ክፍያ ነው የሚለያዩት።

ለአርሰናል የዛሬ ምሽቱ ጨዋታ የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር በጥንቃቄ እንደሚጫወት ሲጠበቅ በጥሩ መነቃቃት ላይ የሚገኘው ቸልሲ ዘንድሮ ከታላላቆቹ የሊጉ ቡድኖች ጋር ጠንክሮ በመታየቱ የምሽቱን ጨዋታ አጓጊ ያደርገዋል።

ቼልሲ 31 ጨዋታዎችን አድርጎ በ47 ነጥብ 9ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ ካሸነፈ ደረጃውን ወደ 7ኛ ከፍ ሊያደርግ የሚችልበት እድል ያገኛል።

👍 22
Изображение

#ከተሞቻችን
ዓዲግራት

በ14ኛው ክፍለ ዘመን እንደተቆረቆረች የሚነገርላት ታሪካዊቷ የዓዲግራት ከተማ ከመዲናችን አዲስ አበባ በስተሰሜን አቅጣጫ 1ሺሕ 38 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡

የአመለሸጋ ሕዝብ መገኛ፣ የአብሮነት ማሳያና በእንግዳ አክባሪነቷ ተምሳሌት የሆነች ከተማ ናት፡፡

ከተማዋ ከባሕር ጠለል በላይ 2 ሺሕ 457 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኝ ሲሆን ደጋማ የአየር ፀባይ አላት፡፡

ለከተማዋ ስያሜ የሆነውና "ዓዲግራት" የሚለው ቃል ትግርኛ ሲሆን ትርጓሜውም "የእርሻ መሬት ሀገር" እንደ ማለት ነው።

በ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደተገነባ የሚነገርለት "ደብረ ዳሞ" እና የ"ጉንዳ ጉንዶ" ገዳማት በዓዲግራት አካባቢ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች ናቸው፡፡

የከተማዋ ተወላጆች ከየአሉበት ተሰባስበው ከወላጆቻቸው ጋር የመስቀል እና የአረፋ በዓላትን በድምቀት የሚያከበሩባት ከተማ ነች።

ሙሉውን ለማንበብ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0AJQXDKAqaHh6RecyrUZ85bL8CvqapPPVVEJrhjcTUR4XzYDDCKNa1SBB5HEkEGQgl

👍 18
🙏 1
Изображение
#አጀንዳ+
👉አሸባሪ መረጃዎች፣ ከፋፋይ ዜናዎች፣ አፍራሽ ፕሮፓጋንዳ በኢትዮጵያ እና ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን ይዳስሳል

ዛሬ ምሽት 3:00 ሰዓት ይጠብቁን!
https://www.youtube.com/watch?v=Brdybxke900
👍 19
😢 2
Изображение

Найдено 13614 постов