Телеграм канал 'WALTA TV'

WALTA TV


44'979 подписчиков
4'851 просмотров на пост

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc

Детальная рекламная статистика будет доступна после прохождения простой процедуры регистрации


Что это дает?
  • Детальная аналитика 5'568'916 каналов
  • Доступ к 1'533'798'153 рекламных постов
  • Поиск по 5'767'552'608 постам
  • Отдача с каждой купленной рекламы
  • Графики динамики изменения показателей канала
  • Где и как размещался канал
  • Детальная статистика по подпискам и отпискам
Telemetr.me

Telemetr.me Подписаться

Аналитика телеграм-каналов - обновления инструмента, новости рынка.

Найдено 13607 постов

235 ሰዎችን የሚይዘው አሳንሰር (ሊፍት)
#ቴክኖ_ቅምሻ

በፊንላንድ ሊፍት ኩባንያ ኮን በ2022 በህንድ ሙምባይ በሚገኘው ጂዮ ወርልድ ሴንተር ህንፃ ውስጥ በዓለማችን የመጀመሪያ የሆነውን 235 ሰዎችን የሚይዘው አሳንሰር (ሊፍት) ገጥሞታል።

ይህ ትልቁ የመንገደኞች ሊፍት የስቲዲዮ አፓርታማ ያክላል የተባለ ሲሆን 16 ቶን የሚመዝንና በ9 የብረት ኬብሎች የተደገፈ ነው፡፡ አሳንሰሩ ሰዎችን ከማጓጓዝ በተጨማሪ ለሰርግና ለአርት ኤግዚብሽን ማሳያ እንዲሆን ተደርጎ የተሰራ ሲሆን 25.78 ስኩየር ሜትር ስፋት ያለውና ለተመልካች ውብ የሆነ እይታና የአትክልት ቦታ ያካተተ ነው።

አሳንሰሩ 18 ትላልቅ ፑሊዎች፣ 9 የብረት ኬብሎች እና በብረት ዓምዶች ላይ የተስተካከሉ ሀዲዶችን ባቀፈ አዲስ የፑሊ ጨረር ሲስተም ላይ የተሰራ ነው ተብሏል።

የዓለማችን ትልቁ የመንገደኞች አሳንሰር (ሊፍት) ልዩ ባለ አራት ፓነል የመስታወት በር፣ የመስታወት ግድግዳዎች ፓኖራሚክ እይታዎችን እና ክሪስታል-የተጣበበ ጣሪያን ያሳያል። በአምስት ፎቆች መካከል ብቻ የሚጓዝ ቢሆንም በሴኮንድ 1 ሜትር ፍጥነት በመጓዝ ሪከርድ ሰባሪው ሊፍትም ሆኗል።

ሊፍቱ ውስጥ ተጓዦች ሲደክማቸው አረፍ የሚሉበት 2 ምቹ ሶፋዎችም አሉት፡፡

የኮን ማኔጂንግ ዳይሬክተር ኢሚት ጎሳይን የዓለማችንን ትልቁን የህዝብ ማመላለሻ አሳንሰር (ሊፍት) ለደንበኞቻችን ችግር ፈች የሆነ ፕሮጀክት በመስራታችን ኩራት ይሰማናል ብለዋል፡፡
👇
https://shorturl.at/rT679
👍 12
👏 3
Изображение
በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በመምከር ከብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

የተከበራችሁ የሀገራችን ሕዝቦች፣
ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትነት ታሪኳ፣ የፖለቲካ ልዩነቶችን፣ አለመግባባቶችን እና ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ፣ በንግግር፣ በውይይት እና በሕጋዊ አግባብ የመፍታት ልምምድ የላትም። እንደ አለመታደል ሆኖ ፖለቲካችን የዜሮ ድምር ፖለቲካ ነው። በሀገራችን የተለመደው በጉልበት አሸንፎ ሥልጣን የያዘ ኃይል፣ በጉልበት ተሸንፎ ሥልጣን እስኪለቅ ድረስ ሁሉንም ጠቅልሎ የሚቆጣጠርበት እና የፈቀደውን የሚያደርግበት የፖለቲካ ባህል ነው።

የለውጡ መንግሥት ወደ ሥልጣን የመጣው በጉልበት አይደለም። ይሄም አዲስ የፖለቲካ ባህል ነው። ይሄን አዲስ የፖለቲካ ምእራፍ የሚያጸና ሌላ ሰላማዊ የፖለቲካ ባህል ደግሞ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሕዝብ ይሁንታ አግኝቶ መንግሥት በመመሥረት አሳይቷል። ከዚህም በመሻገር ልዩ ልዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላትን በመንግሥት ኃላፊነት በመመደብ፣ ኢትዮጵያ የጋራ ቤት መሆንዋን አስመስክሯል።

ሰላማዊ የፖለቲካ ሽግግር ብቻውን ግብ አይደለም። ሌሎች ግቦችን ለማሳካት መሣሪያ እንጂ። የኢትዮጵያ ችግር የአሁኑን አካሄድ በማስተካከል ብቻ አይፈታም። በታሪክ ውስጥ የወረስናቸውን ስብራቶች መጠገንም የግድ ይለናል። እነዚህን የታሪክ ስብራቶች ለመጠገን ሦስት ዓይነት መፍትሔዎች ተቀምጠዋል።
👇👇
https://shorturl.at/pBFO4
👍 16
👎 3
Изображение

የመኖሪያ ቤት ተደርምሶ ባደረሰው አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ሚያዝያ 16/2016 (አዲስ ዋልታ) በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኝ የመኖሪያ ቤት ተደርምሶ በጀርባ በሚገኝ ሌላ መኖሪያ ቤት ላይ በማረፉ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው የተከሰተው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ጠሮ መስጊድ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ መሆኑን የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አይዳ አወል ለአዲስ ዋልታ ዲጂታል ሚዲያ ገልጸዋል።

በግንባታ ላይ የነበረው የግለሰብ መኖሪያ ቤት ተደርምሶ በጀርባ በሚገኝ ሌላ መኖሪያ ቤት ላይ በማረፉ በቤቱ ውስጥ ለነበሩ ሰባት ነዋሪዎች ሕይወት ማለፍ ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።

አደጋው ሌሊት ከ10፡30 በኋላ የተከሰተ መሆኑን የገለጹት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ እስካሁን የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ጠቁመዋል።

አደጋ ለደረሰባቸው የቤተሰብ አባላት መጽናናትን ተመኝተው ኅብረተሰቡ ላይ መሰል አደጋዎች እንዳይደርሱ በህንፃ ግንባታዎች ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡

በአድማሱ አራጋው

😢 12
👍 9
Изображение

የጨረታ ማስታወቂያ

የጉምሩክ ኮሚሽን ተሽከርካሪዎች፣ ጥሬ ዕቃዎች፣ ተንቀሳቃሽ እና የሚገጠሙ ፎርክ ሊፍቶች፣ የዳይፐር ማምረቻ ማሽኖች እና መለዋወጫዎች፣ የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶች እንዲሁም በሼድ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ዕቃዎችን በሙሉ ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

የጨረታ መነሻ ዋጋው 315 ሚልዮን 671 ሺሕ 341 ብር ከ14 ሣንቲም ነው።

ተጨማሪ መረጃ ሐዋሳ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በስልክ ቁጥር 0462125396 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

👍 19
🙏 2
Изображение

በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ አርሰናል ከቼልሲ ዛሬ ምሽት ይጫወታሉ

ሚያዚያ 15/2016 (አዲስ ዋልታ) በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርሰናል በኤምሬትስ ስታዲዬም ከቼልሲ ጋር ወሳን ጨዋታ ያካሂዳሉ።

አርሰናል በ33 ጨዋታዎች በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በ74 ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን በተመሳሳይ 74 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘነው ሊቨርፑል በጎል ክፍያ ነው የሚለያዩት።

ለአርሰናል የዛሬ ምሽቱ ጨዋታ የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር በጥንቃቄ እንደሚጫወት ሲጠበቅ በጥሩ መነቃቃት ላይ የሚገኘው ቸልሲ ዘንድሮ ከታላላቆቹ የሊጉ ቡድኖች ጋር ጠንክሮ በመታየቱ የምሽቱን ጨዋታ አጓጊ ያደርገዋል።

ቼልሲ 31 ጨዋታዎችን አድርጎ በ47 ነጥብ 9ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ ካሸነፈ ደረጃውን ወደ 7ኛ ከፍ ሊያደርግ የሚችልበት እድል ያገኛል።

👍 22
Изображение

#ከተሞቻችን
ዓዲግራት

በ14ኛው ክፍለ ዘመን እንደተቆረቆረች የሚነገርላት ታሪካዊቷ የዓዲግራት ከተማ ከመዲናችን አዲስ አበባ በስተሰሜን አቅጣጫ 1ሺሕ 38 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡

የአመለሸጋ ሕዝብ መገኛ፣ የአብሮነት ማሳያና በእንግዳ አክባሪነቷ ተምሳሌት የሆነች ከተማ ናት፡፡

ከተማዋ ከባሕር ጠለል በላይ 2 ሺሕ 457 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኝ ሲሆን ደጋማ የአየር ፀባይ አላት፡፡

ለከተማዋ ስያሜ የሆነውና "ዓዲግራት" የሚለው ቃል ትግርኛ ሲሆን ትርጓሜውም "የእርሻ መሬት ሀገር" እንደ ማለት ነው።

በ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደተገነባ የሚነገርለት "ደብረ ዳሞ" እና የ"ጉንዳ ጉንዶ" ገዳማት በዓዲግራት አካባቢ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች ናቸው፡፡

የከተማዋ ተወላጆች ከየአሉበት ተሰባስበው ከወላጆቻቸው ጋር የመስቀል እና የአረፋ በዓላትን በድምቀት የሚያከበሩባት ከተማ ነች።

ሙሉውን ለማንበብ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0AJQXDKAqaHh6RecyrUZ85bL8CvqapPPVVEJrhjcTUR4XzYDDCKNa1SBB5HEkEGQgl

👍 17
🙏 1
Изображение
#አጀንዳ+
👉አሸባሪ መረጃዎች፣ ከፋፋይ ዜናዎች፣ አፍራሽ ፕሮፓጋንዳ በኢትዮጵያ እና ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን ይዳስሳል

ዛሬ ምሽት 3:00 ሰዓት ይጠብቁን!
https://www.youtube.com/watch?v=Brdybxke900
👍 19
😢 2
Изображение
አትሌት ዘርፌ ወንድማገኝ ለአምስት ዓመታት ከአትሌቲክስ ውድድር ታገደች

ሚያዝያ 14/2016 (አዲስ ዋልታ) ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዘርፌ ወንድማገኝ የተከለከለ አበረታች መድኃኒት በመጠቀሟ ለአምስት ዓመታት ከአትሌቲክስ ውድድር ታገደች፡፡

አትሌቲክስ ኢንቴግሪቲ ዩኒት ይፋ ባደረገው መረጃ የ21 ዓመቷ የመካከለኛ ርቀት አትሌት ሁለት የተከለከሉ ንጥረ-ነገሮች መውሰዷን አምናለች ብሏል።

አትሌቷ ሦስት ጊዜ ምርመራ የተደረገላት ሲሆን በሁለቱ የተከለከለ አበረታች መድኃኒት መጠቀሟ ተረጋግጧል፡፡

የዓለም አትሌቲክስ አካል የሆነው አትሌቲክስ ኢንቴግሪቲ ዩኒት ባወጣው መግለጫ አትሌቷ ቴስቶስቴሮን የተባለውን እና ኢፒኦ የተሰኘውን አትሌቶች በደማቸው ውስጥ የበለጠ ኃይል እንዲያገኙ የሚያደርገውን ንጥረ ነገር መውሰዷን አምናለች ብሏል፡፡

ዋዳ የተሰኘው ዓለም አቀፉ የፀረ-አበረታች መድኃኒት ተቋም በ2023 ባወጣው ዝርዝር መሠረት አትሌቷ የወሰደችው ንጥረ-ነገር ሕግን የሚጥስ መሆኑ ተዘግቧል።

ከባለፈው ዓመት ኅዳር ወር ጀምሮ እገዳ ተጥሎባት ምርመራ ላይ የቆየች ሲሆን ዛሬ በይፋ መቀጣቷን አትሌቲክስ ኢንቴግሪቲ ዩኒት አስታውቋል፡፡

አትሌቷ ውሳኔውን በመቃወም ይግባኝ መጠየቅ እንደምትችልም በመግለጫው ላይ ተጠቁሟል፡፡

በሐብታሙ ገደቤ
👍 14
👏 3
😢 2
Изображение
ስለፕላስቲክ ብክለት መረጃዎች ምን ይላሉ?

#አዲስ_ዋልታ
👍 3
Изображение

60 ሺሕ ቻይናዊያንን ያፈናቀለው ከባድ ጎርፍ

ከሰሞኑ በተለያዩ ሀገራት የሚከሰቱ ኃይለኛ የጎርፍ አደጋዎች ሕይወት የሚቀጥፉ፣ ሃብትና ንብረት የሚያወድሙ በአጠቃላይ ከባድ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሆነዋል። አውራ ጎዳናዎችና መኖሪያ ቤቶች በጎርፍ ተጥለቀለቁ የሚሉ ዜናዎች በተደጋጋሚ እየተሰሙ ነው። ይህን መሰል የጎርፍ አደጋ ዛሬ በቻይና ተከስቶ ዜጎችን ከቀያቸው አፈናቅሏል።

በቻይና ከፍተኛ የሕዝብ ብዛት በሚስተዋልበት የጓንግዶንግ የባህር ዳርቻ ግዛት ለቀናት የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በተከሰተው ጎርፍ ወደ 60 ሺሕ የሚጠጉ ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው መፈናቀላቸው ተሰምቷል። 11 ሰዎች የጠፉ ሲሆን እስካሁን በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት አለመድረሱ ተገልጿል።

በመንግስት ሚዲያዎች እና በበይነ መረብ ላይ የተሰራጩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በጎርፍ የተጥለቀለቀ ሰፊ መሬት ላይ የነፍስ አድን ሰራተኞች በጀልባዎች በጥልቅ እና ሰፊ ውሃ ላይ ሲንሳፈፉ ያሳያሉ።

ትላልቅ ወንዞች ሞልተው በዳርቻቸው ጎረፍ ይፈሳል። የሀገሪቱ የሚቲዎሮሎጂ ባለስልጣናት አደገኛውን ሁኔታ እና ከፍተኛውን የውሃ መጠን በቅርበት እየተከታተሉ መፍትሄ የሚሉትን ሁሉንም እየሞከሩ ናቸው ተብሏል።
ሙሉውን ለማንበብ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ👇👇
https://shorturl.at/bsDNX

👍 12
ከአበባ የተሰራው የመጀመሪያው አልማዝ

ቻይና በዓለም የመጀመሪያ የሆነውን ከአበባ የተሰራ አልማዝ አበረከተች።

አልማዝ በተፈጥሮ ከሚገኙ እጅግ ውድ ማዕድናት መካከል አንዱ ነው፡፡ በተፈጥሮ ከሚገኙ ነገሮችም እጅግ ጠንካራው ነው፡፡ ይሁን እንጂ የቻይና ሳይንቲስቶች ፔኦኒ ከተሰኘ ቀይ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ በላብራቶሪ ውሰጥ ይህን በተፈጥሮ የሚገኝ ውድ ማዕድን መስራት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡

ይህ አልማዝ ሎያንግ ታይም ፕሮሚስ የተሰኘ በቻይና ሎያንግ ከተማ ውሰጥ የሚገኝ ድርጅት የሰራው ሲሆን አልማዙን ከአበባው በሚገኝ የካርቦን ንጥረነገሮች በመጠቀም እንደተሰራ ገልጸዋል፡፡

አልማዙ ከከተማው የፔኦኒ አባባ ማእከል በተገኙ አበቦች የተሰራ ሲሆን ድርጅቱ የተሰራውን 3 ካራት አልማዝ መልሶ ለአበባ ማእከሉ አበርክቷል፡፡

የአምራች ድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አልማዙ 41 ሺሕ ዶላር የሚጠጋ ዋጋ እንዳለው ጠቅሰው አልማዙን ለማምረት ባዮ ጄኒክ ካርቦን ኤክስትራክሽን የተሰኘ ከፍተኛ ሙቀትና ግፊት የሚጠቀም ቴክኖሎጂ እንደሚጠቀሙ ገልጸዋል፡፡

ይህ በቴክኖሎጂ በመታገዝ የሚሰራ አልማዝ በተፈጥሮ ከሚገኘው አልማዝ ጋር በአካልና በኬሚካል ስሪታቸው አንድ አይነት ሲሆኑ የሚለዩትም በዋጋቸውና ለመሰራት በሚፈጁበት ጊዜ ነው ተብሏል፡፡

ሰው ሰራሽ አልማዞቹ በወራት የሚፈጠሩ ሲሆን በተፈጥሮ የሚገኝ አልማዝ ግን ለመፈጠር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዓመታትን ይፈጃሉ፡፡ በተጨማሪም በላብራቶሪ ውስጥ የሚሰሩት አልማዞች ዋጋቸው በተፈጥሮ ከሚገኙት አነስ ያለ ነው መባሉን ከብሪዚ ስክሮል ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
👍 17
Изображение
ጀጎል የምስራቅ አፍሪካው አውራ ግንብ
#ሀገሬ

ሀገራችን ድንቅና ውብ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ መስህቦች እንዲሁም ታሪካዊ ቅርሶችና ባህላዊ እሴቶች ባለቤት ናት። እነዚህ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች የውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ቀልብ በመግዛት ይታወቃሉ። ምርጥ የቱሪዝም መዳረሻ ከመሆን ባሻገርም የዓለም ቅርስ ሆነው የተመዘገቡ ብዙ ናቸው፡፡

ከእነዚህ የሀገራችን ውብ ቅርሶች በምሥራቁ የሀገራችን ክፍል የሚገኘው የጀጎል ግንብ አንዱ ሲሆን የግንባታው መሀንዲሶች በወቅቱ የነበሩ አባቶች ናቸው። የጀጎል ግንብ የሀረሪ ህዝብ የኪነ ህንፃ ችሎታውን የሚያስመሰክር የታሪክ እና የጥበብ ውጤትም ነው፡፡

የሀረር ከተማ መለያና የዓለም ቅርስ የሆነው የጀጎል ግንብ የተገነባው በ16ኛው ክፍለ ዘመን በአሚር ኑር ቢን ሙጃሂድ መሆኑን ታሪክ ያስረዳል።

ጀጎል በሀገር በቀል ዕውቅ የፈጠራ ባለቤቶች የተገነባ የሀገረሰብ ጥበብ ውጤት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በዘመኑ አባቶች ያለምንም ቴክኖሎጂ እገዛ ነበር ግንቡን ያበጃጁት። ከፋብሪካ ውጤቶች ነፃ የሆነና በአካባቢያቸው የሚገኘውን ጥሬ ዕቃ በመጠቀም የገነቡት የዚህ ግንብ ቆይታው ደግሞ የአባቶችን የጥበብ ከፍታን ያሳየ ነው። በዘመኑ በምስራቅ አፍሪካ በግንብ የታጠረች የመጀመሪያዋ ድንቅ ከተማ ሀረር እንደሆነች መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የግንባታው ዓላማም ከተማዋን ከጠላት ለመከላከል እንደሆነ ይነገራል፡፡
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid02VCyxBNeQPPKMBqs55dzGPXpj5j7YSUapF4h1uHe9Hjcdh2yQMPZx7PMT4KiFvtH8l
👍 13
👏 6
🙏 2
Изображение

በኬንያ በተካሄደው የ5 ሺሕ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ

ሚያዝያ 13/2016 (አዲስ ዋልታ) ትላንት ማምሻውን በኬኒያ በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ኮንቲኔንታል ቱር ጎልድ ውድድር  በ5 ሺሕ ሜትር በሁለቱም ፆታዎች  ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸንፈዋል።

በሴቶች የ5 ሺሕ ሜትር ውድድር አትሌት ማርታ አለማየው ርቀቱን 15 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ ከ54 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በአንደኝነት ስትጨርስ፣ ለምለም ንብረት  15 ደቂቃ ከ20 ሰከንድ ከ99 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት ውድድሩን በመጨረስ 3ኛ ሆና አጠናቃለች። ሌላዋ አትሌት ሽቶ ጉሚ ውድድሩን በአራተኝነት አጠናቃለች።
 
በሌላ በኩል በወንዶች የ5 ሺሕ ሜትር ውድድር አብዲሳ ፈፍሳ ርቀቱን 13 ደቂቃ ከ34 ሰከንድ ከ77 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ አሸናፊ መሆኑን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

👍 36
👏 2
😢 1
Изображение

አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ በዲያመንድ ሊግ 1 ሺሕ 500 ሜትር ውድድር አሸነፈች

ሚያዚያ 12/2016 (አዲስ ዋልታ) በቻይና ዝያሜን እየተካሄደ ባለው ዲያመንድ ሊግ አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ 3:50:30 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን ማሸነፍ ችላለች።

በተያያዘ የ2024 የዲያመንድ ሊግ ውድድር አትሌት ለሜቻ ግርማ በ5 ሺሕ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸንፏል።

አትሌት ለሜቻ ግርማ በውድድሩ ርቀቱን በቀዳሚነት ለማጠናቀቅ 12:58.96 ስዓት ፈጅቶበታል።

ውድድሩ ለ6 ወራት የሚቆይ ሲሆን አራት አህጉራት በ15 ከተሞች የሚካሄድ ይሆናል።

👍 33
🙏 7
Изображение

የጉራጌ ሕዝብ በአንድነት ውስጥ የሚገኘውን ጸጋ ከሕይወት ልምዱ የተገነዘበ ነው - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ሚያዝያ 12/2016 (አዲስ ዋልታ) የጉራጌ ሕዝብ በአንድነት ውስጥ የሚገኘውን ጸጋ ከሕይወት ልምዱ የተገነዘበ ሕዝብ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

የለውጡን መንግስት የሚደግፍ ሕዝባዊ ሰልፍ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር የጉራጌ ሕዝብ ስለአንድነት እና አብሮነት አበክሮ ያስተማረና በተግባር ያሳየ አንድነት ኃይል ነው ብሎ የሚያምን መሆኑን አንስተዋል።

ስለሰላም ሳናስብ፤ ስለሰላም ሳንናገር ሰላምን ልንጎናጸፍ አንችልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጉራጌ ስለሰላም የሚያስተምር፤ በሰላም የሚኖር ሰላምን የሚያስተጋባ ሕዝብ መሆኑንም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያን ለመከፋፈል በየዕለቱ ገንዘባቸውን፣ ዕውቀታቸውንና ጉልበታቸውን ለሚያጠፉ ለአትዮጵያ ጠላቶች ጉራጌ አንድነት ኃይል ነው ብሎ ስለሚያምን ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ልንማር ይገባል ብለዋል።

አክለውም የኢትዮጵያ አንድነትን ጠብቀን ለትውልድ ማሻገር እንድንችል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

👍 36
👏 3
Изображение
Изображение

Найдено 13607 постов