Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
11.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
39 415
Сегодня
-3
Просмотров на пост
Всего
2 051
ER
Общий
3.84%
Суточный
3.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 11 915 постов
Смотреть все посты
Пост от 30.01.2026 21:20
533
0
1
ሌላው የአዲስ አበባ ገጽታ - ውብ፣ ምቹና ማራኪ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች
Пост от 30.01.2026 20:30
678
0
0
ወላይታ ድቻ እና አዳማ ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ18ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወላይታ ድቻ እና አዳማ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የወላይታ ድቻን ግብ ቴዎድሮስ ሀ/ማርያም ሲያስቆጥር፤ ለአዳማ ከተማ ደግሞ አቤኔዘር ሲሳይ አስቆጥሯል።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን እና ምድረ ገነት ሽረ ያለምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል።
Пост от 30.01.2026 17:54
957
0
1
የባካሪ ሳኛ ጉብኝት ለስፖርት ቱሪዝም ሚናው ከፍተኛ ነው - ሰላማዊት ካሳ

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርሰናል የቀድሞ ተከላካይ ባካሪ ሳኛ በኢትዮጵያ ያደረገው ጉብኝት ለስፖርት ቱሪዝም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል አሉ የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ፡፡

ሚኒስትሯ በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረገ ከሚገኘው ባካሪ ሳኛ ጋር ተገናኝተው የኢትዮጵያ ቆይታውን በተመለከተ ተወያይተዋል።

በውይይቱ በአዲስ አበባ በየአካባቢው የተገነቡት የስፖርት ማዘውተሪያዎች እና ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን አንስተናል ብለዋል፡፡

ባካሪ ሳኛ በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ እና የአንድነት ፓርክን ጨምሮ ልዩ ልዩ ስፍራዎችን መጎብኘቱን ጠቅሰው፤ በከተማዋ የተመለከታቸው መዳረሻዎች ቀደም ሲል ስለ ኢትዮጵያ የነበረውን አመለካከት እንደቀየሩለት መመስከሩን ተናግረዋል።

በተለይም ስፖርት ወዳድ የሆኑት ኢትዮጵያውያን ያደረጉለት የሞቀ አቀባበል እንዳስደሰተው መግለጹን ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል።

እንደ ባካሪ ሳኛ አይነት ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸውን ኮኮቦች ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ መሳብ ለስፖርት ቱሪዝም ያለው ሚና ከፍተኛ ነው በማለት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
Пост от 30.01.2026 17:05
888
0
0
ሀዋሳ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ18ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የሀዋሳ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ተባረክ ሄፋሞ እና ጌታነህ ከበደ አስቆጥረዋል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ደግሞ ኢትዮጵያ መድን እና ምድረ ገነት ሽረ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ወላይታ ድቻ እና አዳማ ከተማ ይገናኛሉ፡፡
👏 2
Пост от 30.01.2026 10:48
1 327
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ምድረ ገነት ሽረ እና ኢትዮጵያ መድን ይጫወታሉ።

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በሊጉ 29 ነጥብ በመሰብሰብ 3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሀዋሳ ከተማ በ26 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ ከተቀመጠው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ይገናኛል።

አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ደግሞ ወላይታ ድቻ እና አዳማ ከተማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

የሊጉን ደረጃ ሰንጠረዥ ሲዳማ ቡና በ33 ነጥብ ሲመራ÷ መቻልና ሀዋሳ ከተማ እኩል 29 ነጥብ በመሰብሰብ በግብ ልዩነት 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
Пост от 29.01.2026 21:22
1 248
0
1
በመዲናዋ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ላቀፉ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ ይሰጣል

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በመዲናዋ የተለያዩ አካባቢዎች በተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ተተኪ ስፖርተኞችን ላቀፉ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ ይሰጣል አለ የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን አጠቃቀም በሚመለከት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።

የቢሮው ኃላፊ በላይ ደጀን በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በከተማዋ ጥራታቸውን ጠብቀው የተገነቡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች አጠቃቀም ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡

የስፖርት ማዘውተሪያዎቹ በቀጣይ የሚያስፈልጋቸውን የእድሳት ወጪ ለመሸፈን እንዲችሉ የጤና ቡድኖችና ልምምድ የሚሰሩ ክለቦች በየደረጃው በክፍያ እንዲጠቀሙ ይደረጋል ብለዋል።

በተለይም አዳጊና ተተኪ ስፖርተኞችን ላቀፉ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ እንደሚሰጥ ገልጸው፥ በገንዘብ መጠቀም የሚችሉና የማይችሉትን በመለየት በቀጣይ ተጠቃሚነት ላይ ተጨማሪ መመሪያ ተግባራዊ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡

አቅም የሌላቸው ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች በነጻ እንዲጠቀሙ ይደረጋል ያሉት ኃላፊው፥ ከከተማ አስተዳደሩ ደንብና መመሪያ ውጪ የሚሰሩ የማዘውተሪያ ተቋማት ላይ አስፈላጊውን ቁጥጥር በማድረግ ርምጃ እንደሚወሰድ ተናግረዋል።

ግንባታቸው ተጠናቅቆ ርክክብ ያልተደረገባቸውና በተለያዩ ምክንያቶች አገልግሎት መስጠት ያልጀመሩ ማዘውተሪያዎችን በአፋጣኝ ወደ አገልግሎት ለማስገባት ይሰራል ነው ያሉት፡፡

ተጨማሪ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ፍላጎትና ጥያቄዎች መኖራቸውን ገልጸው፥ ደረጃቸውን የጠበቁ ተጨማሪ የማዘውተሪያ ስፍራዎችን የመገንባት ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክተዋል፡፡

በእንዳልካቸው ወዳጄ
👍 1
Пост от 29.01.2026 20:01
1 440
0
2
ሀገሩን በኦሊምፒክ የመወከል ህልም ያለው የጅምናስቲክ ተወዳዳሪ…

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጅምናስቲክ ስፖርት ተወዳዳሪው የጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ድሪባ ቶሌራ በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል ላይ ስኬታማ ጊዜን እያሳለፈ ይገኛል፡፡

በስፖርት ፌስቲቫሉ በትናንትናው ዕለት ፍፃሜውን ባገኘው የጅምናስቲክ ውድድር አስተናጋጁ ጅማ ዩኒቨርሲቲ በ76 ነጥብ 1ኛ በመሆን የቡድን ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል::

የዩኒቨርሲቲው የሲቪል ምህንድስና 2ኛ ዓመት ተማሪ የሆነው ድሪባ ቶሌራ በተወዳደራባቸው የጅምናስቲክ የስፖርት አይነቶች አራት የወርቅና አንድ የብር ሜዳልያዎችን አሳክቷል፡፡

በተጨማሪም ከቡድን አጋሮቹ ጋር በመሆን ዩኒቨርስቲውን የዋንጫ ባለቤት ማድረግ ችሏል፡፡

በተወዳደረበት የጅምናስቲክ ውድድር ባገኘው ስኬት መደሰቱን ገልጾ፥ በቀጣይ በኦሊምፒክና በሌሎች ውድድሮች ሀገሩን የመወከል ህልም እንዳለው ተናግሯል፡፡

ከተሳትፎም ባሻገር በዓለምአቀፍ መድረክ ለሀገሬ ሜዳልያ የማስገኘት ፍላጎት አለኝ የሚለው ተማሪ ድሪባ፥ ለዚህም አቅሙን በተሻለ ስልጠና ማገዝ የሚችልበት እድል እንዲመቻችለት ጠይቋል፡፡

የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በ15 የስፖርት አይነቶች በጅማ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት በድምቀት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በተስፋሁን ከበደ
Смотреть все посты