Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 514
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 050
ER
Общий
5.28%
Суточный
4.1%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 882 постов
Смотреть все посты
Пост от 08.07.2026 20:37
32
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ አንድሬይ ሳንቶስን ከቼልሲ ለማስፈረም ከስምምነት ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን የቼልሲ አማካይ አንድሬይ ሳንቶስ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሷል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ ለ22 ዓመቱ ተጫዋች ዝውውር 50 ሚሊየን ፓውንድ ለቼልሲ እንደሚከፍል ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ሳንቶስ በ2023 ከብራዚሉ ክለብ ቫስኮ ደ ጋማ ሰማያዊዎቹን መቀላቀሉ ታወሳል፡፡
Пост от 08.07.2026 19:01
561
0
2
ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከፖርቹጋል አሰልጣኝነታቸው ተነሱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር መለያየታቸውን የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል፡፡

ፖርቹጋል በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ላይ በስፔን ተሸንፋ ከውድድሩ መሰናበቷ ለአሰልጣኙ ከቡድኑ ጋር መለያየት ምክንያት ሆኗል፡፡

ፖርቹጋል በዓለም ዋንጫው ከኮሎምቢያ እና ዴሞክራቲክ ኮንጎ ጋር አቻ ስትለያይ ኡዝቤኪስታን እና ክሮሽያን ማሸነፍ ችላለች፡፡

የ52 ዓመቱ አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ በ2025 ከፖርቹጋል ጋር የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ዋንጫን ማሸነፋቸው ይታወሳል።

አሰልጣኙ በተደጋጋሚ የ41 ዓመቱን ተጫዋች ክሪስቲያኖ ሮናልዶን በቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ማካተታቸው ለትችት የዳረጋቸው ሲሆን፤ በዚህ ምክንያት ለስንብት ሳይበቁ እንዳልቀረ ተነግሯል፡፡

የቤልጂየም ወርቃማ ትውልድን በማባከን የሚወቀሱት ማርቲኔዝ፤ ከፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ጋርም ተመሳሳይ ውድቀት በማስመዝገብ ተሰናብተዋል፡፡
Пост от 07.07.2026 20:02
556
0
2
ሜሲ ፍጹም ቅጣት ምት በሳተበት ጨዋታ ግብጽ አርጀንቲናን 1 ለ 0 እየመራች ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ግብጽ አርጀንቲናን 1 ለ 0 እየመራች የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቅቃለች፡፡

የግብጽን የመሪነት ግብ ያሰር ኢብራሂም 15ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በጨዋታው አርጀንቲና የፍጹም ቅጣት ምት አግኝታ የነበረ ቢሆንም ሊዮኔል ሜሲ ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡

ሜሲ በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ለሁለተኛ ጊዜ የፍጹም ቅጣት ምት የሳተ ሲሆን፥ በዓለም ዋንጫ ታሪክ በርካታ የፍጹም ቅጣት ምቶችን (4) በመሳት ብቸኛው ተጫዋች ሆኗል።

ሜሲ በእግር ኳስ ሕይወቱ በአጠቃላይ 34 የፍጹም ቅጣት ምቶችን ስቷል፡፡
Пост от 07.07.2026 18:14
1
0
0
አርጀንቲና ከግብጽ - ኮሎምቢያ ከስዊዘርላንድ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው ሩብ ፍጻሜውን የሚቀላቀሉ ሁለት ተጨማሪ ብሔራዊ ቡድኖች የሚታወቁባቸው የጥሎ ማለፍ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ፡፡

ምሽት 1 ሰዓት ላይ የሦስት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊ አርጀንቲና ከአፍሪካዊቷ ሀገር ግብጽ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

አርጀንቲና በ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ የተሳተፈችውን ኬፕ ቨርዴን በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀሏ ይታወሳል፡፡

ተጋጣሚዋ ግብጽ በበኩሏ አውስትራሊያን በመለያ ምት በማሸነፍ ነበር 16ቱን የተቀላቀለችው፡፡

7 ግቦችን በማስቆጠር ከኪሊያን ምባፔ እና ኧርሊንግ ብራውት ሀላንድ ጋር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃውን እየመራ የሚገኘው ሊዮኔል ሜሲ በዛሬው ጨዋታ ልዩነት ፈጣሪ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

በሌላ መርሐ ግብር ስዊዘርላንድ ከኮሎምቢያ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡

ስዊዘርላንድ በ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አልጄሪያን እንዲሁም ኮሎምቢያ ሌላኛዋን አፍሪካዊት ሀገር ጋናን በመርታት 16ቱን መቀላቀላቸው አይዘነጋም፡፡

ዛሬ ምሽት የሚደረጉ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች አሸናፊ ሀገራት በሩብ ፍጻሜው እርስ በእርስ የሚገናኙ ይሆናል፡፡

ፈረንሳይ፣ ሞሮኮ፣ እንግሊዝ፣ ኖርዌይ፣ ስፔን እና ቤልጂየም እስካሁን ድረስ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀሉ ብሔራዊ ቡድኖች ናቸው፡፡
Пост от 07.07.2026 00:06
1
0
0
ስፔን ፖርቹጋልን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ስፔን ፖርቹጋልን 1 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቅላለች።

የስፔንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ሜሪኖ ከመረብ አሳርፏል።
Пост от 06.07.2026 14:39
1
0
0
ጆርዳን ሄንደርሰን ከዓለም ዋንጫ ውጪ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው ተጫዋች ጆርዳን ሄንደርሰን ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ ሆኗል፡፡

የብሬንትፎርዱ አማካኝ ትላንት ምሽት እንግሊዝ ሜክሲኮን 3 ለ 2 ባሸነፈችበት ጨዋታ የማስታወቂያ ቦርድ ለመዝለል ሲሞክር ወድቆ መጎዳቱ ተመላክቷል፡፡

በዚህም ተጫዋቹ ቀዶ ጥገና እንደሚያስፈልገው እና እንግሊዝ በቀጣይ ከምታደርጋቸው ከዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ውጪ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

ከጉዳቱ በኋላ ሄንደርሰን ወደ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን÷ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ማረፊያ አለመመለሱም ነው የተገለጸው፡፡

የ36 ዓመቱ ተጫዋች በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ 6 ደቂቃ ብቻ ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ግልጋሎት ሰጥቷል፡፡
Пост от 06.07.2026 14:36
1 440
0
1
ትችት እያስተናገደ የሚገኘው አወዛጋቢው የባሎጉን ቀይ ካርድ መሻር…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፊፋ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ፎላሪን ባሎጉን የቀይ ካርድ ቅጣት እንዲነሳ መወሰኑን ተከትሎ ከፍተኛ ትችት እያስተናገደ ይገኛል፡፡

አዘጋጇ ሀገር አሜሪካ ቦሲኒያን 2 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏን ባረጋገጠችበት የ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ባሎጉን 64ኛው ደቂቃ ላይ በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ መሰናበቱ ይታወሳል፡፡

ፊፋ ባሎጉን የተመለከተውን ቀጥታ ቀይ ካርድ በማንሳት በትናንትናው ዕለት ያሳለፈው አወዛጋቢ ውሳኔ ከተለያዩ አካላት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡

የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ውሳኔውን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ የሚመለከታቸው ኃላፊዎች ደንቡን ተግባራዊ ማድረግ አለባቸው ሲል አሳስቧል፡፡

እግርኳስ የሚመራው በደንብ መሆኑን የገለጸው ማህበሩ ቀይ ካርድ ግዴታ እንጂ ፍላጎት አይደለም ያለው ማህበሩ የውድድር ህጎች ተግባራዊ ካልሆኑ ውድድሩ ታማኝነቱን እንደሚያጣ አመልክቷል፡፡

እንዲህ ዓይነት ውሳኔ ምሳሌ ሊፈጥር እንደሚችል በመግለፅ በተመሳሳይ ሁኔታዎች እኩል አያያዝ ካልተተገበረ ውድድሩን ይጎዳል ሲል በመግለጫው አመልክቷል።

የሊቨርፑል የቀድሞ አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ቀይ ካርዱ መነሳቱን ተከትሎ በሰጡት አስተያየት፥ የፊፋው ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስለ እግርኳስ ሀሳብ የላቸውም ሲሉ ተችተዋል፡፡

የቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሩዲ ጋርሽያ በተመሳሳይ ፍሎሪን ባሎጉን የተመለከተው ቀይ ካርድ በመነሳቱ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡

አዘጋጇ ሀገር አሜሪካ ወደ ሩብ ፍጻሜው ለመግባት ዛሬ ሌሊት 9 ሰዓት ላይ ከቤልጂየም ጋር ትጫወታለች፡፡
Изображение
Смотреть все посты