Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.4K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 144
Сегодня
-27
Просмотров на пост
Всего
1 735
ER
Общий
4.3%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 414 постов
Смотреть все посты
Пост от 16.05.2026 20:35
1
0
0
በሻንጋይ ዳይመንድ ሊግ አትሌት ብርቄ ሐየሎም አሸነፈች

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሻንጋይ የ2026 የዳይመንድ ሊግ የሴቶች 1ሺህ 500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ሐየሎም አሸነፈች፡፡

አትሌት ብርቄ ርቀቱን 3 ደቂቃ ከ55 ሰከንድ ከ56 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በቀዳሚነት አጠናቅቃለች፡፡

አትሌቷ የውድድሩን ክብረወሰን በማሻሻልና የወቅቱን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ነው ያሸነፈችው፡፡

አትሌት ፅጌ ዱጉማ 3 ደቂቃ ከ55 ሰከንድ ከ71 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 2ኛ ደረጃን ይዛ ውድድሯን ማጠናቀቅ ችላለች፡፡

በርቀቱ የተካፈለችው ሌላኛዋ አትሌት ወርቅነሽ መሰለ 3 ደቂቃ ከ57 ሰከንድ ከ56 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 4ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን ጨርሳለች፡፡

በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር ደግሞ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ2ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ውድድራቸውን ማጠናቀቅ ችለዋል፡፡
Пост от 16.05.2026 19:38
268
0
1
የ2025/26 የኤፍ ኤ ዋንጫ ሻምፒዮን - ማንቼስተር ሲቲ
Пост от 16.05.2026 18:58
545
0
2
ማንቼስተር ሲቲ የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲ ቼልሲን በማሸነፍ የ2025/26 የውድድር ዓመት የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በዌምብሌይ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ የማንቼስተር ሲቲን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ አንቷን ሴሜንዮ አስቆጥሯል፡፡

ከ2023 በኋላ የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን ያሳካው ማንቼስተር ሲቲ በመድረኩ ለስምንተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡
👍 4
Пост от 16.05.2026 16:36
878
0
1
የኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ አሰላለፍ ይፋ ሆነ

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ተፋላሚ ቡድኖች አሰላለፍ ይፋ ሆኗል፡፡

የ2025/26 የውድድር ዓመት የኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ በማንቼስተር ሲቲ እና ቼልሲ መካከል ይደረጋል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ ጀምስ ትራፎርድ፣ ማቲያስ ኑኔስ፣ ኩሳኖቭ፣ ማርክ ጉኢ፣ ኒኮ ኦሬሊ፣ ሮድሪ፣ ቤርናርዶ ሲልቫ፣ አንቷን ሴሜኒዮ፣ ኦማር ማርሙሽ፣ ጀርሚ ዶኩ እና ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድን በመጀመሪያ አሰላፍ ውስጥ አካትቷል፡፡

ሳንቼዝ፣ ፎፋና፣ ኮልዊል፣ ሀቶ፣ ጉስቶ፣ ሬስ ጀምስ፣ ካይሴዶ፣ ኩኩሬያ፣ ፈርናንዴዝ፣ ፓልመር እና ጇ ፔድሮ በቼልሲ በኩል በመጀመሪያ አሰላፍ ውስጥ የተካተቱ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

የኤፍ ኤ የፍጻሜ ጨዋታ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በዌምብሌይ ስታዲየም መደረግ ይጀምራል፡፡
👍 4
👎 1
Пост от 16.05.2026 11:20
1 074
0
2
ኢትዮጵያ በ20 ኪሎ ሜትር ርምጃ ውድድር በሁለቱም ጾታ የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ20 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር በሁለቱም ጾታ በቀዳሚነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያዎችን አግኝታለች።

በሴቶች አትሌት ውብዓለም ሽጉጤ ውድድሩን በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ፤ አትሌት ሕይወት አምባው 4ኛ እንዲሁም አትሌት ማሬ ቢተው 8ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቅቀዋል፡፡

በወንዶች አትሌት ምስጋናው ዋቁማ ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ማስገኘት የቻለ ሲሆን፤ አብዱልሰላም አብዱልዋሂብ 3ኛ ደረጃን በመያዝ የነሐስ ሜዳሊያ ለሀገሩ አምጥቷል።

በወርቅነህ ጋሻሁን
Пост от 16.05.2026 09:28
1 132
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ሀዋሳ ከተማ እና አርባምንጭ ከተማ ይገናኛሉ።

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ፋሲል ከነማ እና አዳማ ከተማ ይጫወታሉ።
Пост от 16.05.2026 00:03
1 419
0
2
አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን በማሸነፍ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።

ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ስታዲየም ሊቨርፑልን ያስተናገደው አስቶን ቪላ ሮጀርስ፣ ዋትኪንስ (ሁለት) እና ማክጊን ባስቆጠሯቸው ግቦች ድል አድርጓል።

የሊቨርፑልን ግቦች ቫን ዳይክ ከመረብ አሳርፏል።

በዚህም አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ ሁለተኛ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።

ሊቨርፑል በ59 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
Смотреть все посты