Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.6K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 592
Сегодня
-5
Просмотров на пост
Всего
2 136
ER
Общий
4.81%
Суточный
3.8%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 601 поста
Смотреть все посты
Пост от 08.06.2026 10:33
531
0
3
በዓለም ዋንጫ የተለያዩ ሀገራትን የወከሉት አባትና ልጅ…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ልጅ ሉካ ዚዳን ሞሮኮን በመወከል በሰሜን አሜሪካ ሀገራት በሚሰናደው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ይሳተፋል፡፡

ከዚህ ቀደም አባቱ ዚነዲን ዚዳን ከፈረንሣይ ብሔራዊ ቡድን ጋር በመድረኩ ወርቃማ ጊዜያትን አሳልፏል፡፡

‎ዚዳን የሚለው ስም በእግር ኳሱ ዓለም እንዲናኝ ያደረገው ዚነዲን ዚዳን በፈረንሣይ ብሔራዊ ቡድን እጅግ የተሳካ ጊዜ ስለነበረው ነው፡፡

‌‎ሀገሩ ለመጀመሪያ ጊዜ አሰናድታ ሻምፒዮን በሆነችበት የ1998ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ኮከብ ከመሆኑም ባለፈ በ2006ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ የፍፃሜ ተፋላሚ ነበር።

‎በእግር ኳስ ታሪክ ከታዩ ምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ዚነዲን ዚዳን ልጅ ሉካ ዚዳን በአንጻሩ ከፈረንሳይ ይልቅ ለአያቶቹ ሀገር አልጄሪያ መጫወትን መርጧል፡፡

‎ሉካ ዚዳን በሰሜን አሜሪካ በሚካሄደው አለም ዋንጫ የበረሃ ቀበሮዎቹ ግብ ጠባቂ በመሆን እንደ አባቱ በዓለም ዋንጫው ተሳትፎ ያደርጋል፡፡

በሙባረክ ፈንታው
😢 1
Пост от 08.06.2026 10:05
396
0
0
https://www.youtube.com/live/OoF6QdbN7-I?si=AZ0I-qoIEgh2wN07
Пост от 07.06.2026 19:35
612
0
2
የኢራን የዓለም ዋንጫ ብሔራዊ ቡድን ሜክሲኮ ገባ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ በጥምር በሚያስተናግዱት የ2026 ዓለም ዋንጫ የሚሳተፈው የኢራን ብሔራዊ ቡድን ሜክሲኮ ገብቷል።

ብሔራዊ ቡድኑ ወደ ሜክሲኮ ያቀናው ከአሜሪካ ቪዛ አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ውዝግብ ውስጥ በመግባቱ ነው።

ብሔራዊ ቡድኑ በሜክሲኮዋ ቲጁዋና ከተማ ዛሬ ከሰዓት የደረሰ ሲሆን፤ ልምምዱን በቲጁዋና በማድረግ ለምድብ ጨዋታዎች ብቻ ወደ አሜሪካ ስታዲየሞች ያቀናል።

ቀደም ሲል የኢራን ብሔራዊ ቡድን 15 አመራሮች እና ድጋፍ ሰጭ አባላት የአሜሪካ ቪዛ መከልከላቸውን በመግለፅ፤ ጉዳዩ በስፖርት ላይ የተደረገ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት ነው ሲል አውግዟል፡፡

የኢራን የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ኃላፊ፣ ምክትላቸው እና የሚዲያ ዳይሬክተሩ የአሜሪካ ቪዛ ከተከለከሉት የኢራን ብሔራዊ ቡድን አባላት መካከል እንደሚገኙበት ታውቋል፡፡

የአሜሪካ ባለስልጣናት በበኩላቸው÷ ኢራን ከኒውዚላንድ ጋር ጨዋታዋን ከምታደርግበት 10 ቀን አስቀድሞ ለሁሉም የኢራን ተጫዋቾች እና የድጋፍ ሰጪ የቡድን አባላት ቪዛ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡

ኢራን አግባብነት የሌለው ክስ በማቅረብ አሸባሪዎችን ወደ አሜሪካ ለማስገባት እየሞከረች ነው ያሉት ባለሰልጣናቱ÷ በተለይም ከኢራን አብዮታዊ ዘብ ጋር ግንኙነት ያለው ማንኛውም የስፖርት ልዑካን ወደ ዋሽንግተን እንደማይገቡ ገልጸዋል፡፡

እንደ ቢቢሲ ዘገባ፤ በኢራን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ከተካተቱ ተጫዋቾች አብዛኛው ብሔራዊ ውትድርናን ያጠናቀቁ ናቸው፡፡

የዓለም ዋንጫው በፈረንጆቹ ሰኔ 11 የሚጀመር ሲሆን የዓለም ዋንጫው ሲጀመር አሜሪካ በታሪክ ጦርነት የገጠመቻትን ሀገር በእግር ኳስ ያስተናገደች ብቸኛ ሀገር እንድትሆን ያደርጋታል፡፡

በሚኪያስ አየለ
👍 1
Пост от 07.06.2026 09:16
197
0
1
በኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ጌታቸውና አትሌት መሰለች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ በተካሄደው 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር በወንዶች አትሌት ጌታቸው ማስረሻ ከሸገር ሲቲ እንዲሁም በሴቶች አትሌት መሰለች አለማየሁ ከአዲስ አበባ ፖሊስ አሸንፈዋል፡፡

በወንዶች ምድብ አትሌት ባለይልኝ ተሻገር ከኢትዮ ኤሌክትሪክ 2ኛ ሲወጣ አትሌት በላይ ጥላሁን ደግሞ ከአዲስ አበባ ፖሊስ 3ኛ ደረጃን ይዟል፡፡

በተመሳሳይ በሴቶች ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ዝማም ባራኪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለተኛ በመሆን አጠናቅቃለች፡፡

መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ አድርጎ በተከናወነው ውድድር በወንዶች 455 እና በሴቶች 183 በድምሩ 638 አትሌቶች ተሳትፈዋል፡፡

ውድድሩ በዴንማርክ ኮፐንሀገን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችን ለመምረጥና ተተኪዎንች ለማፍራት ያለመ ነው፡፡
Пост от 07.06.2026 08:25
297
0
1
19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡

መነሻና መድረውሻን መስቀል አደባባይ ባደረገው ውድድር በወንዶች 455፤ በሴቶች183 በድምሩ 638 አትሌቶች ተሳትፈዋል፡፡

ውድድሩ በዴንማርክ ኮፐንሀገን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችን ለመምረጥና ተተኪዎንች ለማፍራት ያለመ ነው፡፡

ከ1ኛ እስከ 6ኛ ደረጃ ይዘው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የገንዘብ፣ የሜዳልያና የዋንጫ ሽልማት እንደሚበረከተላቸው ተመላክቷል፡፡
Пост от 06.06.2026 19:58
127
0
1
ዋሊያዎቹ የማላዊ አቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታ የማላዊ ብሄራዊ ቡድንን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የዋሊያዎቹን የአሸናፊነት ግብ ፍጹም ጥላሁን አስቆጥሯል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች የመልስ ጨዋታቸውን በመጪው ማክሰኞ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም ያደርጋሉ፡፡
Пост от 06.06.2026 15:53
1
0
0
የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል በሮምና ሞስኮ...

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሳምንቱ በሮም እና በሞስኮ በተካሄዱ ውድድሮች ላይ በበላይነት አጠናቅቀዋል።

በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደውና በዓለም አትሌቲክስ የኤፍ ደረጃ በተሰጠው የ2026 የዝናሜንስኪ ወንድማማቾች መታሰቢያ የአትሌቲክስ ውድድር የኢትዮጵያ አትሌቶች የበላይነት በመያዝ ውድድሩን በታላቅ ድል ማጠናቀቅ ችለዋል።

በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ኃይሎም 1ኛ በመሆን ማጠናቀቅ ስትችል÷ አትሌት ሳሮን በርሃ ደግሞ 2ኛ ደረጃን ይዛለች።

አትሌት ደስታ ታደለ 5ኛ፣ አትሌት ሲፈን ዳገታ 8ኛ ፣ አትሌት በሻቱ ጌታ 9ኛ እና አትሌት ቤተልሔም ሙላት 15ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።

የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት ፈንታዬ ጫኔ በአንደኝነት ስታሸንፍ÷ አትሌት ቤተልሔም ኦላና 2ኛ ወጥታለች።

አትሌት ሰላማዊት ሻምበል 4ኛ እንዲሁም አትሌት ትርንጎ ታዳለ 6ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።

በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ብርቱካን ገዳሙ ፈጣን ፉክክር በተደረገበት የሩጫ መድረክ ርቀቱን 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።

በ800 ሜትር አትሌት ሀብታም ገበየሁ 6ኛ ደረጃን መያዝ ችላለች።

በወንዶች የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ አትሌት እዮብ ስመኝ በበላይነት ጨርሷል፡፡

በዚሁ ውድድር ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሽመልስ ንጉሴ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ፈፅሟል።

የወንዶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ዲንቃ ፍቃዱ 1ኛ በመሆን ሲያሸንፍ... 👇
https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid02sMcxhRPHmLEdS8w39VV21zKhPgdyz82qJEpA3kQWcYNHXg8q7c5frwVQpV9zQQEVl
Смотреть все посты