Каталог каналов Мои подборки Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.1K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 668
Сегодня
-17
Просмотров на пост
Всего
1 654
ER
Общий
3.8%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 115 постов
Смотреть все посты
Пост от 19.04.2026 20:34
460
0
2
ማንቼስተር ሲቲ አርሰናልን በማሸነፍ ነጥቡን አጠበበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ተጠባቂ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ አርሰናልን 2 ለ 1 አሸንፏል።

በሜዳው ኢትሃድ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ የሊጉን መሪ አርሰናልን ያስተናገደው ማንቼስተር ሲቲ ቼሪኪ እና ሃላንድ ባስቆጠሯቸው ግቦች ነጥቡን ወደ ሶስት ለማጥበብ ያስቻለውን ድል አስመዝግቧል።

የአርሰናልን ብቸኛ ግብ ካይ ሀቨርት ከመረብ ጋር አገናኝቷል።

አንድ ቀሪ ጨዋታ ያለው ማንቼስተር ሲቲ ነጥቡን 67 በማድረስ በ70 ነጥብ ሊጉ እየመራ ከሚገኘው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሶስት አጥብቧል።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
👍 5
Пост от 19.04.2026 20:15
292
0
1
መቻል እና ሀዋሳ ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ የተገናኙት መቻል እና ሀዋሳ ከተማ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም የተካሄደው የነገሌ አርሲ እና ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታ 1 ለ 1 ተጠናቅቋል።

ለነገሌ አርሲ ኪቲካ ጅማ፤ ለሀድያ ሆሳዕና ደግሞ ተመስገን ብርሃኑ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሲዳማ ቡና ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ፤ ኢትዮጵያ ቡና እና አርባምንጭ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት መለያየታቸው ይታወቃል።
Пост от 19.04.2026 19:22
655
0
1
ማንቼስተር ሲቲ እና አርሰናል በአቻ ውጤት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ እና አርሰናል 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ወደ እረፍት አምርተዋል፡፡

በኢትሃድ ስታዲየም እየተደረገ ባለው ጨዋታ ሪያን ቼርኪ የግል ብቃቱን ተጠቅሞ ማንቼስተር ሲቲን መሪ ሲያደርግ ካይ ሀቨርት የበረኛውን ጂያንሉጂ ዶናሩማ ስህተት ተጠቅሞ አርሰናልን አቻ አድርጓል፡፡

እስከ እረፍት በተደረገው ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ 62 በመቶ የኳስ ቅብብል በማድረግ የጨዋታ ብልጫ መውሰድ ችሏል፡፡
Изображение
Изображение
Пост от 19.04.2026 17:15
857
0
1
ሲዳማ ቡና ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 9 ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ሲዳማ ቡና አቤል ያለው ባስቆጠራቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።

የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ እየተካሄደ ሲሆን ቀን 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም መጫወት የጀመሩት ነገሌ አርሲ እና ሀድያ ሆሳዕና ያለምንም ግብ ወደ እረፍት አምርተዋል።

ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና እና አርባምንጭ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት መለያየታቸው ይታወቃል።
Пост от 19.04.2026 09:59
1 192
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በአዲስ አበባ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ እንዲሁም ቀን 10 ሰዓት ላይ ነገሌ አርሲ ከሀድያ ሆሳዕና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡና ከድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ መቻል ከሀዋሳ ከተማ ይገናኛሉ፡፡
👍 2
Пост от 19.04.2026 09:08
1 140
0
2
ማንቼስተር ሲቲ ከአርሰናል - የሳምንቱ ተጠባቂ ፍልሚያ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ የሊጉን መሪ አርሰናልን ያስተናግዳል፡፡

በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡትን ቡድኖች የሚያገናኘው ጨዋታ የሳምንቱ ተጠባቂ መርሐ ግብር ነው፡፡

ማንቼስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማጥበብ የሚያደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡

አንድ ቀሪ ጨዋታ ያለው ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሦስት ዝቅ ማድረግ ይችላል፡፡

በሊጉ ከሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች የአቻ ውጤት በኋላ ቼልሲን በማሸነፍ ወደ ድል የተመለሰው ማንቼስተር ሲቲ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

በጨዋታው ሩበን ዲያስ በጉዳት ምክንያት ለማንቼስተር ሲቲ ግልጋሎት እንደማይሰጥ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አረጋግጠዋል፡፡

ያለፉትን ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ 2ኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል በዚህ የውድድር ዓመት ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ይፋለማል፡፡

በሊጉ ባሳለፍነው ሳምንት በቦርንማውዝ ሽንፈት ያስተናገደው አርሰናል ወደ ድል ለመመለስ የሚያደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡

የካራባኦ ካፕ ዋንጫን በማንቼስተር ሲቲ የተነጠቀውና ከኤፍ ኤ ዋንጫ ውድድር የተሰናበተው አርሰናል በቀሪ ሁለት ውድድሮች ዋንጫውን ለማሳካት ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ቡካዮ ሳካ ከዛሬ ምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ ውጪ መሆኑን አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ተናግረዋል፡፡

በወንድማገኝ ጸጋዬ
Изображение
Пост от 18.04.2026 20:17
1 158
0
1
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፏል።

የወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ነፃነት ገብረመድህን እና ፍሬው ሰለሞን አስቆጥረዋል።

ቀደም ብሎ ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ መቐለ 70 እንደርታ ፋሲል ከነማን 3 ለ 0 አሸንፏል።

ጨዋታው የመቐለ 70 እንደርታን ማሸነፊያ ግቦች ቦና አሊ (2) እና ሚሊዮን ወልዴ ከመረብ አሳርፈዋል።
Смотреть все посты