Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 516
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 161
ER
Общий
5.63%
Суточный
4.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 914 постов
Смотреть все посты
Пост от 12.07.2026 21:12
1
0
0
አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ በኒውዮርክ በተካሄደ የ15 ኪ.ሜ ውድድር አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኒውዮርክ በተካሄደው የ15 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ አሸነፈች፡፡

አትሌቷ 47 ደቂቃ ከ29 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሯን በበላይነት አጠናቅቃለች፡፡

አትሌት ጽጌ የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ነው ውድድሩን በቀዳሚነት ያጠናቀቀችው፡፡

ሌላኛዋ በርቀቱ የተሳተፈችው ኢትዮጵያዊት አትሌት መልክናት ውዱ 47 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት 2ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን አጠናቅቃለች፡፡
Пост от 12.07.2026 16:56
1
0
0
አራቱ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚዎች…

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ 48 ሀገራት በተሳተፉበት የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ውድድር 44 ሀገራት ተሰናብተው አራት ሀገራት ብቻ ቀርተዋል፡፡

የሦስት ጊዜ የመድረኩ ባለክብር አርጀንቲና፣ የሁለት ጊዜ ሻምፒዮኗ ፈረንሳይ እንዲሁም በተመሳሳይ አንድ ጊዜ ዋንጫውን ከፍ ማድረግ የቻሉት እንግሊዝ እና ስፔን ለሌላ ክብር ተቃርበዋል፡፡

በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ፈረንሳይ ከስፔን እንዲሁም እንግሊዝ ከአርጀንቲና በግማሽ ፍጻሜው ይገናኛሉ፡፡

ፈረንሳይ ሰሜን አፍሪካዊቷን ሀገር ሞሮኮ 2 ለ 0 በመርታት እንዲሁም ስፔን ቤልጂየምን 2 ለ 1 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ወደ ፍጻሜው ለማለፍ በመጪው ማክሰኞ ምሽት በቴክሳስ ዳላስ ስታዲየም (ኤቲ ኤንድ ቲ) የሚያደርጉት ጨዋታ ከወዲሁ ይጠበቃል፡፡

በሌላ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ አርጀንቲና ከእንግሊዝ የፊታችን ረቡዕ ምሽት በአትላንታ ይገናኛሉ፡፡

በሩብ ፍጻሜው እንግሊዝ ኖርዌይን እንዲሁም አርጀንቲና ስዊዘርላንድን በጭማሪ ደቂቃ ግቦች በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜው መድረሳቸው ይታወቃል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መገናኘታቸውን ተከትሎ ብዙዎች አርጀንቲና ሻምፒዮን በሆነችበት የ1986 የዓለም ዋንጫ "የእግዜር እጅ" በመባል የምትታወቀውንና ዲያጎ ማራዶና በእንግሊዝ ላይ በእጅ ያስቆጠራትን ግብ እያስታወሷት ይገኛሉ፡፡

44 ሀገራት ተሰናብተው አራት ሀገራት በቀሩበት የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ማን ባለክብር ይሆናል የሚለው ከወዲሁ ተጠባቂ ነው፡፡
Пост от 12.07.2026 16:11
1
0
0
አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ተሰናበቱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝነት ተሰናብተዋል፡፡

ሴኔጋል በ2026 የዓለም ዋንጫ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ በቤልጂየም ተሸንፋ ከውድድሩ መሰናበቷ ይታወሳል፡፡

አሰልጣኙ በዓለም ዋንጫው ያሳዩት ደካማ ጉዞ ለስንብታቸው ምክንያት መሆኑን የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ገልጿል።

የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት በአሰልጣኙ ስንብትና ቀጣይ ውሳኔዎች ዙሪያ በነገው ዕለት ማብራሪያ እንደሚሰጡ ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።

አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ ተጫዋቾቻቸው ጨዋታውን አቋርጠው ከሜዳ እንዲወጡ ማድረጋቸውን ተከትሎ ከፍተኛ ትችት ማስተናገዳቸው አይዘነጋም፡፡
Пост от 12.07.2026 14:55
300
0
2
ፊፋ የዓለም ዋንጫ ተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር ወደ 64 ለማሳደግ እያጤነ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፊፋ በ2030 የዓለም ዋንጫ ተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር ወደ 64 ለማሳደግ እያጤነ መሆኑን ገለጸ፡፡ ከፈረንጆቹ 1998 እስከ 2022 ድረስ የዓለም ዋንጫ በ32 ተሳታፊ ሀገራት ሲካሄድ መቆቱ ይታወሳል፡፡ በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር ደግሞ የተሳታፊ ሀገራት ቁጥር ወደ 48 ከፍ…

https://www.fanamc.com/archives/318626
Изображение
Пост от 12.07.2026 02:57
216
0
1
እንግሊዝ ኖርዌይን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር እንግሊዝ ኖርዌይን 2 ለ 1 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።

ቡድኖቹ መደበኛውን 90 ደቂቃ 1 ለ 1 በማጠናቀቃቸው ወደ ተጨማሪ ሰዓት አምርተዋል።

በዚህም እንግሊዝ ሁለተኛ ግብ በማስቆጠሯ ለግማሽ ፍጻሜ በቅታለች።

እንግሊዝ በግማሽ ፍጻሜው ከአርጀንቲና እና ስዊዘርላንድ አሸናፊ ጋር ትፋለማለች።
Пост от 11.07.2026 14:55
387
0
2
እንግሊዝ ከኖርዌይ፤ አርጀንቲና ከስዊዘርላንድ …

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ቀጥለው ይካሄዳሉ።

ወደ መጠናቀቁ እየተቃረበ በሚገኘው 23ኛው የዓለም ዋንጫ ሁለት የግማሽ ፍፃሜ ተፋላሚዎች ለመለየት ዛሬ ኖርዌይ ከእንግሊዝ እንዲሁም አርጀንቲና ከስዊዘርላንድ ብርቱ ፍልሚያ ያደርጋሉ።

በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሩብ ፍፃሜ የበቃችው እና በውድድሩ አስደናቂ ብቃት እያስመለከተች የምትገኘው ኖርዌይ ለ11ኛ ጊዜ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዋን ከምታደርገው እንግሊዝ ጋር ትጫወታለች።

ጠንካራ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ጨዋታ ሌሊት 6:00 ላይ በሚያሚ ስታዲየም ይካሄዳል።

እንዲሁም አርጀንቲና በ39 ዓመቱ ሊዮኔል ሜሲ እየተመራች በካንሳስ ሲቲ ስታዲየም ከስዊዘርላንድ ጋር የምታደርገው ጨዋታ ንጋት 10:00 ላይ ይደረጋል።

በጨዋታው ከ72 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሩብ ፍፃሜው ያለፈችው ስዊዘርላንድ አዲስ ታሪክ ለመስራት የምታደርገው ፍልሚያ ለአርጀንቲና ከባድ ፈተና እንደሚሆን ይጠበቃል።
Пост от 11.07.2026 00:02
1
0
0
ስፔን ቤልጂየምን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን ቤልጂየምን 2 ለ 1 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።

የስፔንን ግቦች ፋቢያን ሩዪዝ እና ሚኬል ሞሪኖ አስቆጥረዋል።

ስፔን በግማሽ ፍጻሜው ከፈረንሳይ ጋር ትገናኛለች፡፡
Смотреть все посты