Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 512
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 063
ER
Общий
5.19%
Суточный
4.1%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 893 постов
Смотреть все посты
Пост от 10.07.2026 01:02
1
0
0
ፈረንሳይ ሞሮኮን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።

በቦስተን ጁሌት ስታዲየም በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የፈረንሳይን ግቦች ኪሊያን ምባፔ እና ኦስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል።

በመጀመሪያው አጋማሽ ፍጹም ቅጣት ምት የሳተው ምባፔ በዚህ ዓለም ዋንጫ ከሊዮኔል ሜሲ እኩል 8 ግቦች በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን በጋራ እየመራ ይገኛል።

ፈረንሳይ በሦስት ተከታታይ የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ላይ የፍጻሜ ተፋላሚ ለመሆን በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትገናኛለች፡፡
Пост от 09.07.2026 16:29
1
0
0
ኒውካስል ዩናይትድ ሻን ስቱርን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኒውካስል ዩናይትድ ሻን ስቱርን
ከአያክስ አምስተርዳም ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ኒውካስል ዩናይትድ ለ18 ዓመቱ ኔዘርላንዳዊ አማካይ 20 ሚሊየን ፓውንድ እና እየታየ የሚጨመር 3 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ በማድረግ ተጫዋቹን የግሉ አድርጓል፡፡

ሻን ስቱርን በእንግሊዙ ክለብ ኒውካስል ዩናይትድ ቤት ለአምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

ተጫዋቹ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለአያክስ አምስተርዳም 24 ጨዋታዎችን አድርጎ አንድ ግብ ብቻ አስቆጥሯል፡፡

ኒውካስል ዩናይትድ ቀደም ሲል በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ባዙማን ቱሬን ከሆፈንሄይም ማስፈረሙ አይዘነጋም፡፡

በሌላ በኩል ኒውካስል ዩናይትድ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት አንቶኒ ጎርደን ለባርሴሎና እንዲሁም ሳንድሮ ቶናሊን ለቶተንሃም ሆትስፐር አሳልፎ መስጠቱ ይታወቃል፡፡

በተጨማሪም ኒውካስል ዩናይትድ ብራዚላዊውን የቡድኑን አምበል ብሩኖ ጎማሬሽን የሚያጣበት ዕድል ሰፊ መሆኑ በስፋት እየተዘገበ ሲሆን ተጫዋቹ ክለቡን መልቀቅ እንደሚፈልግም አሳውቋል፡፡

በዚህም ክለቡ ቡድኑን ለማጠናከር በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል፡፡

በመልካም ፈቃዱ
Пост от 09.07.2026 13:15
144
0
1
ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 0 በማሸነፍ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል፡፡

በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ የወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ኮንኮኒ ሀፊዝ እና በየነ ባንጃ አስቆጥረዋል፡፡

ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡

የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ዋንጫ ማሳካት የሚችልበትን ዕድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡
Пост от 09.07.2026 10:01
732
0
3
ፈረንሳይ ከሞሮኮ - የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ይጀምራሉ፡፡

ዛሬ ምሽት የሁለት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊ ፈረንሳይ ከአፍሪካዊቷ ሀገር ሞሮኮ ጋር የምታደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ፈረንሳይ በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ፓራጓይን እንዲሁም ሞሮኮ አዘጋጇን ሀገር ካናዳን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡

በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለግማሽ ፍጻሜ በመድረስ ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር የሆነችው ሞሮኮ በድጋሚ ግማሽ ፍጻሜውን ለመቀላቀል ብርቱ ፉክክር እንደምታደርግ ይጠበቃል፡፡

ሞሮኮ በ2022 የኳታር የዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ግማሽ ፍጻሜ መግባቷ የሚታወስ ሲሆን፥ በወቅቱ በፈረንሳይ 2 ለ 0 መሸነፏ አይዘነጋም፡፡

በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ 7 ግቦችን በማስቆጠር ለወርቅ ጫማው እየተፋለመ የሚገኘው ፈረንሳዊው ኮከብ ኪሊያን ምባፔ በጨዋታው ልዩነት ፈጣሪ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም ማይክል ኦሊሴ፣ ኦስማን ዴምቤሌ በፈረንሳይ በኩል እንዲሁም ብራሂም ዲያዝ እና አዘዲን ኦናሂ በሞሮኮ በኩል የሚጠበቁ ተጫዋቾች ነው፡፡

ምሽት 5 ሰዓት ላይ በቦስተን ጁሌት ስታዲየም የሚደረገውን የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ አርጀንቲናዊው ዳኛ ፋኩንዶ ቴሎ ይመሩታል፡፡

የፈረንሳይ እና ሞሮኮ አሸናፊ በቀጣይ በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር የሚገናኝ ይሆናል፡፡
Пост от 08.07.2026 20:37
32
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ አንድሬይ ሳንቶስን ከቼልሲ ለማስፈረም ከስምምነት ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን የቼልሲ አማካይ አንድሬይ ሳንቶስ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሷል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ ለ22 ዓመቱ ተጫዋች ዝውውር 50 ሚሊየን ፓውንድ ለቼልሲ እንደሚከፍል ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ሳንቶስ በ2023 ከብራዚሉ ክለብ ቫስኮ ደ ጋማ ሰማያዊዎቹን መቀላቀሉ ታወሳል፡፡
Пост от 08.07.2026 19:01
561
0
2
ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከፖርቹጋል አሰልጣኝነታቸው ተነሱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር መለያየታቸውን የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል፡፡

ፖርቹጋል በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ላይ በስፔን ተሸንፋ ከውድድሩ መሰናበቷ ለአሰልጣኙ ከቡድኑ ጋር መለያየት ምክንያት ሆኗል፡፡

ፖርቹጋል በዓለም ዋንጫው ከኮሎምቢያ እና ዴሞክራቲክ ኮንጎ ጋር አቻ ስትለያይ ኡዝቤኪስታን እና ክሮሽያን ማሸነፍ ችላለች፡፡

የ52 ዓመቱ አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ በ2025 ከፖርቹጋል ጋር የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ዋንጫን ማሸነፋቸው ይታወሳል።

አሰልጣኙ በተደጋጋሚ የ41 ዓመቱን ተጫዋች ክሪስቲያኖ ሮናልዶን በቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ማካተታቸው ለትችት የዳረጋቸው ሲሆን፤ በዚህ ምክንያት ለስንብት ሳይበቁ እንዳልቀረ ተነግሯል፡፡

የቤልጂየም ወርቃማ ትውልድን በማባከን የሚወቀሱት ማርቲኔዝ፤ ከፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ጋርም ተመሳሳይ ውድቀት በማስመዝገብ ተሰናብተዋል፡፡
Пост от 07.07.2026 20:02
556
0
2
ሜሲ ፍጹም ቅጣት ምት በሳተበት ጨዋታ ግብጽ አርጀንቲናን 1 ለ 0 እየመራች ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ግብጽ አርጀንቲናን 1 ለ 0 እየመራች የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቅቃለች፡፡

የግብጽን የመሪነት ግብ ያሰር ኢብራሂም 15ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በጨዋታው አርጀንቲና የፍጹም ቅጣት ምት አግኝታ የነበረ ቢሆንም ሊዮኔል ሜሲ ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡

ሜሲ በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ለሁለተኛ ጊዜ የፍጹም ቅጣት ምት የሳተ ሲሆን፥ በዓለም ዋንጫ ታሪክ በርካታ የፍጹም ቅጣት ምቶችን (4) በመሳት ብቸኛው ተጫዋች ሆኗል።

ሜሲ በእግር ኳስ ሕይወቱ በአጠቃላይ 34 የፍጹም ቅጣት ምቶችን ስቷል፡፡
Смотреть все посты