Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.8K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 449
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 300
ER
Общий
4.96%
Суточный
3.7%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 760 постов
Смотреть все посты
Пост от 26.06.2026 21:25
1
0
0
ሪያል ማድሪድ ከዳኒ ሴባዮስ ጋር ተለያየ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ ከስፔናዊው ተጫዋች ዳኒ ሴባዮስ ጋር መለያየቱን ይፋ አድርጓል።

ዳኒ ሴባዮስ ከፈረንጆቹ 2017 ጀምሮ በሪያል ማድሪድ ለሰባት የውድድር ዘመናት ቆይቷል።

የ29 ዓመቱ ተጫዋች ለሪያል ማድሪድ 215 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን 16 ዋንጫዎችን አሳክቷል።

ክለቡ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ ዳኒ ሴባዮስ በሎስብላንኮቹ ቤት በነበረው ቆይታ ላሳየዉ ቁርጠኝነት እና ትጋት ምስጋናውን አቅርቦ ሪያል ማድሪድ ሁልጊዜም የእሱ ቤት መሆኑን ገልጿል።

ሪያል ማድሪድ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ከሌላኛው ስፔናዊ ተጫዋች ዳኒ ካርቫሀል ጋር መለያየቱ ይታወሳል።
Пост от 26.06.2026 18:18
342
0
2
ኢትዮጵያ ቡና መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና መቐለ 70 እንደርታን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲም በተደረገው ጨዋታ ቢኒያም ጌታቸው (ሁለት) እና ቫይን ዋቹንክዋ ለቡናማዎቹ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡

ቀደም ሲል በተካሄዱ የሊጉ ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 እንዲሁም ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 26.06.2026 17:24
1
0
0
ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ፍፁም ጥላሁን አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ይገናኛሉ፡፡

አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና መቐለ 70 እንደርታን 2 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ቡናን ግቦች ዲቫይን ዋችኩዋ (በፍጹም ቅጣት ምት) እና ቢኒያም ጌታቸው ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
Пост от 26.06.2026 15:32
1
0
0
ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የነገሌ አርሲን የማሸነፊያ ግቦች በረከት ወልዴ (በፍጹም ቅጣት ምት) እና ሀቢብ ከማል አስቆጥረዋል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከመቐለ 70 እንደርታ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

የቅዱስ ጊዮርጊስን የመሪነት ግብ ፍፁም ጥላሁን አስቆጥሯል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ይገናኛሉ፡፡
Пост от 26.06.2026 13:22
193
0
1
አርሰናል ለጉማሬሽ ያቀረበው የዝውውር ጥያቄ ውድቅ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሻምፒዮኑ አርሰናል ለብራዚላዊው የኒውካስል ዩናይትድ አማካይ ብሩኖ ጉማሬሽ ያቀረበው የዝውውር ጥያቄ ውድቅ ተደረገ፡፡

መድፈኞቹ የ28 ዓመቱን ተጫዋች ለማስፈረም ከ60 ሚሊየን ፓውንድ ያነሰ የዝውውር ሂሳብ ማቅረባቸው ተገልጿል።

ኒውካስል ዩናይትድ የዝውውር ሂሳቡ በቂ አይደለም በማለት ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ብሩኖ ጉማሬሽ በፈረንጆቹ 2020 ኒውካስል ዩናይትድን የተቀላቀለ ሲሆን በሊጉ 150 ጨዋታዎችን አድርጎ 30 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

የመሀል ሜዳ ተጫዋቹ በ2026 የዓለም ዋንጫ ሀገሩ ብራዚልን እያገለገለ ይገኛል።
Пост от 26.06.2026 11:42
336
0
2
የዓለም ዋንጫው ተጠባቂ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

በምድብ ዘጠኝ ያደረጓቸውን ሁለቱንም ጨዋታዎች በማሸነፍ አስቀድመው 32ቱን የተቀላቀሉት ፈረንሳይ እና ኖርዌይ ምድቡን በበላይነት ለማጠናቀቅ ይፋለማሉ፡፡

በዘንድሮው ዓለም ዋንጫ ለሀገራቸው በተመሳሳይ አራት ግቦችን ያስቆጠሩት ኪሊያን ምባፔ እና ኧርሊንግ ሀላንድ ምሽት 4 ሰዓት በሚደረገው ጨዋታ ይጠበቃሉ፡፡

በዚሁ ምድብ በተመሳሳይ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ኢራቅን የምትገጥመው አፍሪካዊቷ ሀገር ሴኔጋል የምሽቱን ጨዋታ የምታሸንፍ ከሆነ ምርጥ ሦስተኛ በመሆን 32ቱን ለመቀላቀል የተሻለ እድል አላት፡፡

እስካሁን አላፊው ብሔራዊ ቡድን ባልታወቀበት ምድብ ስምንት ስፔን ከዩራጓይ እንዲሁም ኬፕ ቨርዴ ከሳዑዲ አረቢያ ሌሊት 9 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

አራት ነጥቦችን በመሰብሰብ ምድብ ሰባትን እየመራች የምትገኘው ግብጽ ነገ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ ከኢራን ጋር የምትጫወት ሲሆን፥ ቤልጂየም ከኒውዚላንድ በተመሳሳይ ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

እስካሁን ሜክሲኮ፣ አሜሪካ፣ካናዳ፣ ጀርመን፣ አርጄንቲና፣ ፈረንሳይ፣ ኖርዌይ፣ ኮሎምቢያ፣ ስዊዘርላንድ፣ ቦሲኒያ ሄርዞጎቪና፣ ብራዚል፣ ሞሮኮ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኤኳዶር፣ ኮትዲቯር፣ ኔዘርላንድስ፣ ጃፓን፣ ስዊድን፣ አውስትራሊያ ከምድባቸው ማለፋቸውን አረጋግጠዋል፡፡
Пост от 25.06.2026 10:50
1 014
0
1
የዓለም ዋንጫ የምድብ 3ኛ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ዋንጫ የምድብ 3ኛ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

ምሽት 5 ሰዓት ላይ አስቀድማ ማለፏን ያረጋገጠችው ጀርመን ከኢኳዶር ጋር ጨዋታዋን የምታደርግ ይሆናል፡፡

ሁለቱንም የምድብ ጨዋታዎች ድል ያደረገችው ጀርመን በስድስት ነጥብ ምድቡን እየመራች ትገኛለች፡፡

ተጋጣሚዋ ኢኳዶር በበኩሏ ካደረገቻቸው ሁለት ጨዋታዎች አንድ ነጥብ ብቻ በመያዝ በምድቡ 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡

በዚሁ ምድብ በተመሳሳይ ሰዓት ኩራሳኦ ከኮትዲቫር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ኮትዲቫር ሦስት ነጥብ በመሰብሰብ በምድቡ 2ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች ሲሆን÷ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ መድረክ የተገኘችው ኩራሳኦ በአንድ ነጥብ የምድቡ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡

በሌላ ጨዋታ መሰናበቷን አስቀድማ ያወቀችው ቲኒዚያ ሌሊት 8 ሰዓት ላይ ከኔዘላንድስ ትጫወታለች፡፡

ኔዘርላንድስ አራት ነጥብ በመሰብሰብ ምድቡን ስትመራው አፍሪካዊቷ ሀገር ቱኒዚያ ያለምንም ነጥብ ከመድረኩ ላለመሰናበት በጨዋታው የምታደርገው ፉክክር ይጠበቃል፡፡

በዚሁ ምድብ በተመሳሳይ ሰዓት ጃፓን ከስዊድን የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡

ጃፓን በአራት ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጣ 2ኛ ደረጃ ላይ ስትቀመጥ ተጋጣሚዋ ስዊድን ደግሞ በሦስት ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡

በወንድማገኝ ጸጋዬ
Смотреть все посты