Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.7K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 545
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
1 826
ER
Общий
4.27%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 698 постов
Смотреть все посты
Пост от 17.06.2026 12:12
224
0
2
በዓለም ዋንጫ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የተጋራው ሊዮ ሜሲ..

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በስድስት የዓለም ዋንጫ ውድድሮች በመጫወት ክብረወሰን ያስመዘገበው ሊዮኔል ሜሲ በ16 ግቦች የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን ክብረ ወሰን ተጋርቷል፡፡

በፈረንጆቹ 2006 በጀርመን ዓለም ዋንጫ በ18 አመቱ ሀገሩን ወክሎ መጫወት የጀመረው የሮዛሪዮው ተወላጅ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ የዘንድሮውን ጨምሮ በስድስት የዓለም ዋንጫዎች ተሳትፏል፡፡

ትናንት ምሽት አርጀንቲና አልጀሪያን 3 ለ 0 ባሸነፈችበት የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ ሦስቱንም ግቦች በማስቆጠር ሀትሪክ የሰራው ሜሲ የዓለም መነጋገሪያ ሆኗል፡፡

ለሀገሩ አርጀንቲና እስካሁን 200 ጨዋታዎችን ያደረገው የ38 አመቱ ኮከብ በጀርመናዊው ሚሮስላቭ ክሎስ ተይዞ የነበረውን የምንጊዜም የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰን ተጋርቷል፡፡

የ2022ቱ የኳታር ዓለም ዋንጫ አሸናፊው ሜሲ አሁንም የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋች መሆኑን ከማስመስከር ባሻገር ሀገሩ በዘንድሮውም ዓለም ዋንጫ ለአሸናፊነት እንድትታጭ አስችሏል፡፡

የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ጅማሮ በሀትሪክ ያሳመረው ሊዮ ሜሲ በቀጣይ ጨዋታዎች ክብረ ወሰኑን የግሉ የማድረግ ሰፊ እድል አለው፡፡

የ26 አመቱ ፈረንሳዊ ኪሊያን ምባፔ ትናንት ምሽት ሀገሩ ሴኔጋልን ባሸነፈችበት ጨዋታ ያስቆጠራቸውን ሁለት ግቦች ጨምሮ 14 ግቦችን ከመረብ ያሳረፈ ሲሆን፥ ክብረ ወሰኑን የግሉ ለማድረግ ከሜሲ ጋር ተፋጧል፡፡

ሊዮኔል ሜሲ በተጨማሪም በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ ሦስት ግቦችን ያሰቆጠረ በእድሜ አንጋፋው ተጫዋች በመሆን ተጨማሪ ክብረ ወሰን የግሉ አድርጓል፡፡

በአቤል ነዋይ
Пост от 17.06.2026 11:41
237
0
1
ፖርቹጋል ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ..

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሀገር ፖርቹጋል የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ዛሬ ምሽት ታደርጋለች፡፡ ፖርቹጋል ምሽት 2 ሰዓት ላይ ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ጋር በሂውስተን ስታዲየም በምታደርገው ጨዋታ የማሸነፍ ቅድመ ግምት ተሰጥቷታል፡፡ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ተሳትፎውን የሚያደርገው ፖርቹጋላዊ ኮከብ በጨዋታው ልዩነት ፈጣሪ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በአውሮፓ የተለያዩ ክለቦች ቁልፍ…

https://www.fanamc.com/archives/316942
Пост от 16.06.2026 19:26
1
0
0
ሩበን አሞሪም የኤሲሚላን አሰልጣኝ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማንቼስተር ዩናይትድ የቀድሞ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የኤሲሚላን አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ፡፡

አሰልጣኙ በጣሊያኑ ክለብ ኤሲሚላን እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆያቸውን ውል ነው የተፈራረሙት፡፡

የ41 ዓመቱ አሰልጣኝ ማንቼስተር ዩናይትድን ለ14 ወራት ማሰልጠን ቢችሉም በውጤት ማጣት ምክንያት መሰናበታቸው አይዘነጋም፡፡

ኤሲሚላን በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በሴሪ ኤው 5ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
Пост от 16.06.2026 18:12
1
0
0
ወላይታ ድቻ ባሕር ዳር ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ሁለት ግቦች ያሬድ ዳርዛ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ የተገናኙት ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና መቐለ 70 እንደርታ ያለምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ የተገናኙት ሸገር ከተማ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡
Пост от 16.06.2026 13:11
1 070
0
1
ሪያል ማድሪድ የአንቶኒዮ ሩዲገርን ውል አራዘመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የተከላካዩን አንቶኒዮ ሩዲገር ውል ለተጨማሪ አንድ ዓመት ማራዘሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ጀርመናዊው ተጫዋች ሩዲገር በሎስብላንኮዎቹ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2027 ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡

አንቶኒዮ ሩዲገር ከምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ በፈረንጆቹ 2022 ሪያል ማድሪድን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡
Пост от 16.06.2026 10:55
216
0
1
ፈረንሳይ ከሴኔጋል…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

በምድብ 9 ላይ የምትገኘው የሁለት ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ፈረንሳይ ከአፍሪካዊቷ ሀገር ሴኔጋል ጋር ምሽት 4 ሰዓት ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

በዚሁ ምድብ የሚገኙት ኢራቅ እና ኖርዌይ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በምድብ 10 የተደለደሉት አርጀንቲና እና አልጄሪያ ደግሞ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡
Пост от 16.06.2026 10:37
1 162
0
1
ቱኒዚያ በዓለም ዋንጫ ከአንድ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ አዲስ አሰልጣኝ ሾመች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ እየተሳተፈች የምትገኘው ቱኒዚያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ከተሸነፈች በኋላ አዲስ አሰልጣኝ ሾመች፡፡

ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር በስዊድን የደረሰባትን የ5 ለ 1 ሽንፈት ተከትሎ አሰልጣኝ ሳብሪ ላሞቺን ከኃላፊነት አሰናብታለች፡፡

በምትካቸውም የ57 ዓመቱን ፈረንሳዊ አሰልጣኝ ሄርቬ ሬናርድን የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ አድርጋ ሾማለች፡፡

ሄርቬ ሬናርድ በአሰልጣኝነት ዘመናቸው ቱኒዚያ 5ኛ አፍሪካዊ ብሔራዊ ቡድናቸው ሲሆን፥ ከዚህ ቀደም ዛምቢያ፣ አንጎላ፣ ኮት ዲቯር እና ሞሮኮን ማሰልጠናቸው ይታወሳል፡፡

ምድብ 6 ላይ የምትገኘው ቱኒዚያ በቀጣይ ከጃፓን እና ኔዘርላንድስ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
Смотреть все посты