Каталог каналов Мои подборки Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.0K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 755
Сегодня
-12
Просмотров на пост
Всего
1 814
ER
Общий
4.43%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 035 постов
Смотреть все посты
Пост от 15.04.2026 18:15
217
0
1
ሀላባ ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አደገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀላባ ከተማ ወደ 2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ።

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2018 የውድድር ዘመን ምድብ ለ 20ኛ ሳምንት ጨዋታ ዛሬ በሀላባ ከተማ እና ደሴ ከተማ መካከል ሀዋሳ ላይ ተደርጓል።

በዚህም ጨዋታ ሀላባ ከተማ ደሴ ከተማን 1 ለ 0 በማሸነፍ ነጥቡን 38 አድርሶ አንድ ጨዋታ እየቀረው በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል።
Пост от 15.04.2026 17:36
142
0
1
ኢትዮጵያ መድን እና ባሕር ዳር ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን እና ባሕር ዳር ከተማ አቻ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ አማኑኤል ኤርቦ የኢትዮጵያ መድንን ግብ ሲያስቆጥር÷ አደም አባስ ደግሞ የባሕር ዳር ከተማን የአቻነት ግብ ከመረብ አሳርፏል።

በተመሳሳይ ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው የሀዋሳ ከተማ እና ምድረ ገነት ሽረ ጨዋታ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 ተለያይተዋል።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማን ከመቻል የሚያገናኘው ጨዋታ ይደረጋል።
Пост от 15.04.2026 15:26
492
0
3
በግራንድ ፕሪክስ ዓለም አቀፍ ውድድር ለመሳተፍ አትሌቶች ወደ አዲስ አበባ እየገቡ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ በሚካሄደው የግራንድ ፕሪክስ ውድድር ለመሳተፍ የተለያዩ ሀገራት አትሌቶች ወደ መዲናዋ እየገቡ ይገኛሉ፡፡

በዛሬው ዕለትም በውድድሩ ለመሳተፍ አሜሪካውያን አትሌቶች ክርስቶፈር እና ሻንቴል አዲስ አበባ መግባታቸውን የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ቀደም ሲል የፓሪስ ኦሎምፒክ 200 ሜትር ሻምፒዮኗ አትሌት ጋቢ ቶማስ በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር ላይ እንደምትሳተፍ ያስታወቀች ሲሆን÷ በቀጣዮቹ ቀናት ወደ መዲናዋ እንደምትባ ይጠበቃል፡፡

የነሐስ ደረጃ የተሰጠው የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን ውድድር የፊታችን ቅዳሜ ሚያዚያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡
Пост от 15.04.2026 14:50
577
0
2
በአዲስ አበባ ስታዲየም የመሮጫ ትራክ አትሌቶች ልምምድ ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ስታዲየም ከ8 ዓመት በኋላ የመሮጫ ትራክ ተጠናቅቆ ዛሬ በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ዓለም አቀፍ ውድድር ለሚሳተፉ አትሌቶች ክፍት በመደረግ ልምምድ ጀምረዋል።

ባለፉት ዓመታት በእድሳት ምክንያት ከአገልግሎት ውጪ የነበረው ስታዲየሙ በአዲስ መልክ እድሳት ተደርጎለት ለውድድር እና ልምምድ ክፍት ተደርጓል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የፊታችን ቅዳሜ የሚደረገውን የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ የአንድ ቀን ውድድር ስኬታማ እንዲሆን የመሮጫ መም እድሳት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ማድረጉን የኢትዮጵያ አቲሌትክስ ፌዴሬሽን መረጃ አመልክቷል።
Пост от 15.04.2026 09:34
867
0
1
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ኢትዮጵያ መድን ከባሕር ዳር ከተማ ጋር ይገናኛል።

በተመሳሳይ ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሀዋሳ ከተማ ከምድረ ገነት ሽረ እንዲሁም አመሻሽ 12 ሰዓት በዚሁ ስታዲየም ድሬዳዋ ከተማ ከመቻል ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
Изображение
Пост от 15.04.2026 00:16
1 267
0
1
ሊቨርፑል እና ባርሴሎና ከአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሰናበቱ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ተደርገዋል፡፡

ምሽት 4 ሰዓት ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ የፈረንሳዩን ክለብ ፒኤስጂን አስተናግዶ 2 ለ 0 ተሸንፏል።

በዚህም ቡድኖቹ በፓርክ ደ ፕሪንስ ያደረጉትን የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ፒኤስጂ 2 ለ 0 በማሸነፉ በድምር ውጤት 4 ለ 0 በመርታት ወደ ግማሽ ፍጻሜ ገብቷል።

በተመሳሳይ ሰዓት አትሌቲኮ ማድሪድ በሜዳው ዋንዳ ሜትሮፖሊታኖ ከባርሴሎና ጋር ባደረገው ጨዋታ 2 ለ 1 ቢሸነፍም፤ የመጀመሪያውን ዙር የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ 2 ለ 0 በማሸነፉ በድምር ውጤት 3 ለ 2 አሸንፎ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 14.04.2026 20:30
1 120
0
2
ፋሲል ከነማ ወላይታ ድቻን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ወላይታ ድቻን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ታምራት ኢያሱ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በአቤል ያለው ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረጉ በሌሎች የሊጉ ጨዋታዎች ኢትዮ ኤሌክትሪክ አዳማ ከተማን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ኢትዮጵያ ቡና እና ሀድያ ሆሳዕና 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ቡናን ግቦች ዘላለም አባተ እና ራምኬል ጀምስ ሲያስቆጥሩ የሀድያ ሆሳዕናን ግቦች ደግሞ ኢዮብ ዓለማየሁ እና ብሩክ በየነ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
Смотреть все посты