Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
12.0K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
39 213
Сегодня
-10
Просмотров на пост
Всего
1 999
ER
Общий
4.85%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 11 965 постов
Смотреть все посты
Пост от 13.02.2026 15:30
1 216
0
2
ማይክል ካሪክ የወሩ ምርጥ አሰልጣኝ ተብሎ ተመረጠ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማይክል ካሪክ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2025/26 የውድድር ዓመት የጥር ወር ምርጥ አሰልጣኝ ተብሎ ተመርጧል፡፡

አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ማንቼስተር ዩናይትድን እየመራ በጥር ወር ያደረጋቸውን ሁለት ጨዋታዎች አሸንፏል፡፡

በጥር ወር ማንቼስተር ዩናይትድ የሊጉ መሪ አርሰናል እና ማንቼስተር ሲቲን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

በሌላ በኩል የብሬንትፎርዱ የፊት መስመር ተጫዋች ኢጎር ቲያጎ የጥር ወር ምርጥ ተጫዋች በመሆን ተመርጧል፡፡

ኢጎር ቲያጎ በውድድር ዓመቱ ለሁለተኛ ጊዜ የፕሪሚየር ሊጉ የወሩ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን አሸንፏል።
Пост от 13.02.2026 00:55
1 723
0
2
አርሰናል እና ብሬንትፎርድ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሐ ግብር የሊጉ መሪ አርሰናል ከብሬንትፎርድ ጋር 1 ለ 1 አቻ ተለያይቷል፡፡

በጨዋታው የባለሜዳውን ቡድን ብሬንትፎርድ ግብ ሊውስ ፖተር ሲያስቆጥር፥ የአርሰናልን ግብ ኖኒ ማዱዌኬ ከመረብ አሳርፏል።
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 12.02.2026 21:18
1 932
0
2
ራሂም ስተርሊንግ ፌይኖርድን ተቀላቀለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ራሂም ስተርሊንግ እስከ ውድድር ዓመቱ መጨረሻ በሚያቆይ ውል የኔዘርላንዱን ክለብ ፌይኖርድ ተቀላቅሏል፡፡

እንግሊዛዊው የመስመር አጥቂ በቼልሲ የሚያቆየው ቀሪ የ18 ወራት ውል ቢኖረውም ባሳለፍነው ጥር ወር በስምምነት ውሉን ማቋረጡ ይታወሳል፡፡

የ31 ዓመቱ ራሂም ስተርሊንግ በቀድሞው የማንቼስተር ዩናይትድ እና አርሰናል አጥቂ ሮበን ቫንፔርሲ የሚሰለጥነውን ፌይኖርድ መቀላቀሉን ቢቢሲ ስፖርት ዘግቧል፡፡
Изображение
Пост от 12.02.2026 09:31
2 268
0
2
አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማስፋት…

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ምሽት 5 ሰዓት ላይ አርሰናል ከብሬንትፎርድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል አራቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ በአንዱ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል፡፡

ትናንት ምሽት ማንቼስተር ሲቲ ፉልሃምን በማሸነፍ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሦስት ያጠበበ ሲሆን አርሰናል ልዩነቱን ወደ 6 ከፍ ለማድረግ ይፋለማል፡፡

ትናንት ምሽት በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ፣ ሊቨርፑል፣ አስቶንቪላ እና በርንሌይ ተጋጣሚዎቻቸውን ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡
Изображение
Пост от 11.02.2026 01:12
2 154
0
2
ማንቼስተር ዩናይትድ እና ዌስትሃም ዩናይትድ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ እና ዌስትሃም ዩናይትድ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል።

በጨዋታው ዌስትሃምን መሪ ያደረገችውን ግብ ሶቼክ ሲያስቆጥር፥ የማንቼስተር ዩናይትድን የአቻነት ግብ ሼሽኮ 96ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፏል።

ቀደም ብለው በተደረጉ የዛሬ ምሽት ጨዋታዎች ቼልሲ እና ሊድስ ዩናይትድ 2 ለ 2 አቻ የተለያዩ ሲሆን፥ ኒውካስል ዩናይትድ ቶተንሃም ሆትስፐርን እንዲሁም ቦርንማውዝ ኤቨርተንን በተመሳሳይ 2 ለ 1 አሸንፈዋል።
Изображение
Изображение
Изображение
👍 3
Пост от 11.02.2026 00:30
2 059
0
2
ቼልሲ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር አቻ ተለያየ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር 2 ለ 2 አቻ ተለያይቷል።

በስታምፎርድ ብሪጅ በተደረገው ጨዋታ የቼልሲን ግቦች ዦአዎ ፔድሮ እና ኮል ፓልመር ሲያስቆጥሩ፥ ንሜቻ እና ኦካፎር የሊድስ ዩናይትድን ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 10.02.2026 09:31
2 479
0
6
ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ 5ኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት…

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

ምሽት 5 ሰዓት 15 ላይ ዌስትሃም ዩናይትድ በሜዳው ማንቼስተር ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡

በሊጉ ያለፉትን አራት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው ማንቼስተር ዩናይትድ 5ኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

ወራጅ ቀጠና ላይ የሚገኘው ዌስትሃም ዩናይትድ በበኩሉ ተከታታይ ሁለተኛ ጨዋታውን ለማሸነፍ ይፋለማል።

ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ምሽት 4 ሰዓት 30 ላይ ቼልሲ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

በሊጉ ያለፉትን አራት ተከታታይ ጨዋታዎች ያሸነፈው ቼልሲ አሸናፊነቱን ለማስቀጠል ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር ከኒውካስል ዩናይትድ እንዲሁም ኤቨርተን ከቦርንማውዝ በተመሳሳይ ምሽት 4 ሰዓት 30 ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡

ፕሪሚየር ሊጉን አርሰናል በ56 ነጥቦች ሲመራ፥ ማንቼስተር ሲቲ በ6 ነጥቦች ዝቅ ብሎ ይከተላል።

አስቶን ቪላ በ47፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ44፣ ቼልሲ በ43 እንዲሁም ሊቨርፑል በ39 ነጥብ ከ3 እስከ 6 ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
👏 1
Смотреть все посты