Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
12.1K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
38 350
Сегодня
-38
Просмотров на пост
Всего
2 060
ER
Общий
4.82%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 12 054 постов
Смотреть все посты
Пост от 21.03.2026 20:03
300
0
1
ፉልሃም በርንሌይን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ31ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ፉልሃም በርንሌይን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡

የፉልሃምን የማሸነፊያ ግቦች ጆሹዋ ኪንግ፣ ሃሪ ዊልሰን እና ራሁል ሂሚኔዝ አስቆጥረዋል፡፡

በርንሌይን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ፍሌሚንግ ከመረብ አሳርፏል፡፡

አስቀድሞ በተደረገ የሊጉ ጨዋታ ብራይተን ሊቨርፑልን 2 ለ 1 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

የሊጉ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ ምሽት 2 ሰዓት 30 ላይ ኤቨርተን ከቼልሲ እንዲሁም ምሽት 5 ሰዓት ላይ ሊድስ ዩናይትድ ከብሬንትፎርድ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Пост от 21.03.2026 17:46
811
0
2
ሊቨርፑል በብራይተን ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 31ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ብራይተን ሊቨርፑልን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

የብራይተንን የማሸነፊያ ግቦች ዳኒ ዌልቤክ ሲያስቆጥር ሊቨርፑልን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ሚሎስ ኬርኬዝ ከመረብ አሳርፏል፡፡

የሊጉ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ ፉልሃም ከበርንሌይ ምሽት 12 ሰዓት እንዲሁም ኤቨርተን ከቼልሲ ምሽት 2 ሰዓት 30 ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ምሽት 5 ሰዓት ላይ ደግሞ ሊድስ ዩናይትድ ከብሬንትፎርድ ይገናኛሉ፡፡
👍 1
Пост от 21.03.2026 16:49
940
0
2
አትሌት ንግስት ጌታቸው ወደ ፍፃሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፖላንድ ቶሩን እየተካሄደ በሚገኘው 21ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌት ንግስት ጌታቸው ወደ ፍፃሜ አልፋለች፡፡

በሴቶች 800 ሜትር ግማሽ ፍፃሜ ላይ የተወዳደረችው አትሌት ንግስት ጌታቸው 1 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ ከ46 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት ሁለተኛ በመውጣት ለፍጻሜ በቅታለች፡፡

አትሌት ንግስት በሻምፒዮናው መክፈቻ ላይ በተካሄደው ውድድር በአንደኝነት ወደ ግማሽ ፍፃሜ ማለፏን የሚታወስ ነው።

የሴቶች 800 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ነገ ምሽቱ 3 ሰዓት 53 ላይ የሚካሄድ ይሆናል።
Изображение
Пост от 21.03.2026 16:33
860
0
2
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመጀመሪያ ጊዜ በሰዓት መመዝገቢያ ማሽን በመታገዝ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመጀመሪያ ጊዜ በሰዓት መመዝገቢያ ማሽን በመታገዝ ይካሄዳል፡፡

55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመጋቢት 15 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በአደይ አበባ ስታዲየም እንደሚካሄድ ተገልጿል።

በሻምፒዮናው 9 ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮችን ጨምሮ ከ36 ክለቦች የተወጣጡ ከ1 ሺህ በላይ አትሌቶች እንደሚሳተፉ ተመላክቷል፡፡

በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑ አትሌቶች የሜዳሊያ እና የገንዘብ ሽልማት የሚበረከት ሲሆን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በምታስተናግደው የዋን ደይ ሚቲንግ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተጠቁሟል፡፡

በሻምፒዮናው የሰዓት መመዝገቢያ ማሽን ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል፡፡

በዚህም በውድድሩ የሚመዘገቡ ሰዓቶች ዓለም አቀፍ ተቀባይነትን እንደሚያገኙ ነው የተገለጸው፡፡

በሌዊ በለጠ
Изображение
👍 2
Пост от 21.03.2026 09:49
1 166
0
2
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ 4 ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ31ኛ ሳምንት መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በቀጣይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎን ለማግኘት ፉክክር እያደረገ የሚገኘው ሊቨርፑል ወደ አሜሪካን ኤክስፕሬስ ስታዲየም አቅንቶ ቀን 9 ሰዓት ከ30 ላይ ብራይተንን ይገጥማል።

በተመሳሳይ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎን ለማግኘት ፉክክር እያደረገ የሚገኘው ቼልሲ ከሜዳው ውጪ ከኤቨርተን ጋር ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ ይጫወታል።

አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ፉልሃም በርንሌይን ሲያስተናግድ፤ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ደግሞ ሊድስ ዩናይትድ ብሬንትፎርድን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ይካሄዳል።

በዕለቱ ይካሄዳል ተብሎ መርሐ ግብር ወጥቶለት የነበረው የማንቼስተር ሲቲ እና ክሪስታል ፓላስ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በነገው ዕለት ከአርሰናል ጋር በሚያደርገው የካራባዎ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ምክንያት ለሌላ ጊዜ ተዛውሯል።

ፕሪሚየር ሊጉን አርሰናል በ70 ነጥብ እየመራ ሲሆን አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ያለው ማንቼስተር ሲቲ በዘጠኝ ነጥብ ዝቅ ብሎ በ61 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ማንቼስተር ዩናይትድ በ55 ነጥብ 3ኛ ደረጃን ሲይዝ፤ ዎልቭስ በ17 ነጥብ የሊጉ ግርጌ ላይ ይገኛል።
👍 10
Пост от 19.03.2026 22:03
1 634
0
1
የአርሰናል የአራት ዋንጫ ጉዞ የመጀመሪያ ፈተና..

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል ለአራት ዋንጫዎች እያደረገ ባለው ጉዞ የመጀመሪያ ፈተናውን በመጪው እሁድ በካራባኦ ዋንጫ ፍጻሜ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ይጀምራል፡፡

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ በ9 ነጥብ በመብለጥ እየመራ የሚገኘው አርሰናል በካራባኦ ካፕ የፍጻሜ ፍልሚያ የሚጠብቀው ሲሆን፥ በሻምፒየንስ ሊግ እና ኤፍ ኤ ካፕ ለሩብ ፍጻሜ ማለፍ ችሏል፡፡

የሚኬል አርቴታው ቡድን ከ22 ዓመታት ጥበቃ በኋላ የሊጉን ዋንጫ ለማሳካት ከየትኛውም ጊዜ በላይ የተቃረበ ሲሆን፥ በሻምፒየንስ ሊግ ሩብ ፍጻሜ ከስፖርቲንግ ሊዝበን ጋር የደርሶ መልስ ጨዋታ ይጠብቀዋል፡፡

አርሰናል በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ከሻምፒየንሺፑ ክለብ ሳውዛምፕተን ጋር መደልደሉም አይዘነጋም፡፡

መድፈኞቹ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያውን እንዲሁም በታሪካቸው ለሦስተኛ ጊዜ የካራባኦ ዋንጫን ለማሳካት በመጪው እሁድ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በዌምብሌይ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር የፍጻሜ ጨዋታ ያደርጋሉ፡፡

በዚህም የሰሜን ለንደኑ ክለብ በመጪው እሁድ በሚያደርገው ጨዋታ የአራት ዋንጫዎች (ኳድራፕል) ጉዞውን በድል ይጀምር ይሆን የሚለው ከወዲሁ ይጠበቃል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
👍 13
🙏 2
Пост от 19.03.2026 19:51
1 748
0
1
የሻምፒየንስ ሊግ የሳምንቱ ምርጦች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር በሳምንቱ አጋማሽ በተደረጉ የሻምፒየንስ ሊግ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ የመልስ ጨዋታዎች ምርጥ 11 ተጫዋቾችን ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም መሰረት በግብ ጠባቂነት የፒኤስጂው ሳቮኖቭ ተመርጧል - ፒኤስጂ በስታምፎርድ ብሪጅ ቼልሲን 3 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ ጠባቂው ዘጠኝ ኢላማቸውን የጠበቁ ኳሶችን መመለስ ችሏል፡፡

የ3 ለ 0 ሽንፈቱን ቀልብሶ ቦዶ ግሊምትን በድምር ውጤት 5 ለ 3 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለው ስፖርቲንግ ሊዝበን ሦስት ተጫዋቾችን ማስመረጥ የቻለ ብቸኛ ክለብ ነው፡፡

አራሆ፣ ጎንካሎ ኢናሲዮ እና ትሪንካኦ ከስፖርቲንግ በኩል ሲመረጡ፥ ከሊቨርፑል ኮናቴ እና ሶቦዝላይ በምርጥ 11 ስብስቡ ውስጥ መካተት ችለዋል፡፡

ራፊኒሃ ከባርሴሎና፣ ቪኒሺየስ ጁኒየር ከሪያል ማድሪድ፣ ዴክለን ራይስ ከአርሰናል፣ ዣቪ ሲሞንስ ከቶተንሃም ሆትስፐር እንዲሁም ስታኒሲች ከባየርን ሙኒክ ተካትተዋል፡፡
Изображение
👍 5
Смотреть все посты