Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.7K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 547
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
1 745
ER
Общий
4.43%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 675 постов
Смотреть все посты
Пост от 15.06.2026 17:28
83
0
1
አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የአርባምንጭ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች አቡዱልራህማን መሐመድና ቴዎድሮስ አጨ አስቆጥረዋል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ሀዋሳ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

የነገሌ አርሲን የማሸነፊያ ግቦች አለኝታ ማርቆስ እና ሮሆቦት ስላሎ አስቆጥረዋል፡፡

ሀዋሳ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገውን ግብ ደግሞ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል።

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡
Пост от 15.06.2026 13:08
830
0
3
ሪያል ማድሪድ ኩኩሬላን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ ማርክ ኩኩሬላን ከቼልሲ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ስፔናዊው የግራ መስመር ተጫዋች በሪያል ማድሪድ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2032 ድረስ የሚያቆየውን ውል ነው የተፈራረመው፡፡

ሪያል ማድሪድ ለ27 ዓመቱ ተጫዋች 55 ሚሊየን ዩሮ እና እየታየ የሚጨመር 5 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ የሚከፍል ይሆናል፡፡

ኩኩሬላ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ በ2022 ከብራይተን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

ተጫዋቹ በቼልሲ በነበረው ቆይታ የኮንፈረንሰ ሊግ እና የዓለም ክለቦች ዋንጫዎችን ማሸነፉ አይዘነጋም፡፡
👍 2
Пост от 15.06.2026 11:01
470
0
1
በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የምትሳተፈው ኬፕ ቨርዴ ከስፔን…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

በምድብ 8 የመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን የምታደርገው አፍሪካዊቷ ኬፕ ቨርዴ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ከስፔን ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

የአንድ ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ስፔን በኦፕታ ቅድመ ትንተና መሰረት የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ እንደምታነሳ ቅድመ ግምት አግኝታለች፡፡

በዚሁ ምድብ የሚገኙት ሳዑዲ አረቢያ እና ዩራጋይ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በምድብ 7 የተደለደሉት ቤልጂየም ከግብፅ ምሽት 4 ሰዓት እንዲሁም ኢራን ከኒውዚላንድ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡
Пост от 15.06.2026 10:01
615
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ነገሌ አርሲ ከሀዋሳ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ነገሌ አርሲ በዛሬው ጨዋታ ነጥብ የሚጥል ከሆነ ሲዳማ ቡና ቀሪ 3 ጨዋታዎች እያሉት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይገናኛሉ፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከምድረ ገነት ሽረ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Пост от 14.06.2026 20:03
1 057
0
2
ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወገኔ ገዛኸኝ የኢትዮጵያ መድንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል፡፡

ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 3 ለ 0 አሸንፈዋል።
👍 2
Пост от 14.06.2026 17:11
961
0
2
ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ለሲዳማ ቡና የማሸነፊያ ግቦቹን ያሬድ ባየህ እና ብርሃኑ በቀለ ሲያስቆጥሩ÷ ኢትዮጵያ ቡናን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ ዘላለም አባተ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ሌላኛው የዕለቱ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ፍፁም ጥላሁን፣ ሀብታሙ ጉልላት እና የአብስራ ጎሳዬ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ መድን ከድሬ ዳዋ ከተማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
👍 2
Пост от 14.06.2026 15:32
981
0
2
አትሌት ማሞ ሐጫሉ እና ማኅሌት ካሳሁን የቦቆጂ ታላቁ ሩጫን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለ5ኛ ጊዜ በቦቆጂ በተደረገው 12 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር በወንዶች አትሌት ማሞ ሐጫሉ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አሸንፏል።

በውድድሩ አትሌት አማን ቃዲ እና አትሌት አልዬ ቃሲም ተከታትለው በመግባት ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።

በሴቶች የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ አትሌቷ ማኅሌት ካሳሁን ስታሸንፍ÷ አትሌት ኪያ ፍስሃ ከአሰላ አትሌቲክስ ማሠልጠኛ ሁለተኛ፣ አትሌት ድርቤ ኢርኮ ሶስተኛ ወጥተዋል።

መነሻና መድረሻውን በቦቆጂ ስታዲየም ባደረገው ከ15 ዓመት በታች የአዳጊዎች ሻምፕዮና በሴቶች ዓባይ ከተማ በወንዶች ደግሞ ካሊድ ሱልጣን ማሸነፍ ችለዋል።

በውድድሩ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ቢያ ጨምሮ የተለያዩ የመንግሥት ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በዳዊት መሐሪ
👍 5
👎 1
Смотреть все посты