Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.0K
13.6K
205
108
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 569
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 340
ER
Общий
6.07%
Суточный
4.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 961 поста
Смотреть все посты
Пост от 19.07.2026 21:22
335
0
1
የ23ኛው ዓለም ዋንጫ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ23ኛው ዓለም ዋንጫ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት በኒውዮርክ ሜትላይፍ ስታዲየም እየተካሄደ ነው። ላለፉት 39 ቀናት በአሜሪካ፣ ካናዳና ሜክሲኮ ጣምራ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 23ኛው የዓለም ዋንጫ ስፔንና አርጀንቲና ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሚያደርጉት የፍጻሜ ጨዋታ ይጠናቀቃል። ከፍጻሜ ጨዋታው በፊትም የመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱ በሜትላይፍ ስታዲየም በተለያዩ ሁነቶች በደማቅ…

https://www.fanamc.com/archives/319094
Пост от 19.07.2026 13:04
1
0
0
ስፔን ከአርጀንቲና…ዓለም በጉጉት የሚጠብቀው የፍጻሜ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ፍጻሜውን ያገኛል፡፡

በፍጻሜ ጨዋታው በወጣት ተጫዋቾች የተደራጀው የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከአርጀንቲና አቻው ጋር ኒውዮርክ በሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም ይፋለማሉ፡፡

በአሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላፎንቴ የምትመራው ስፔን እስካሁን ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በአንዱም ሳትሸነፍ በተጋጣሚዎቿ ላይ 13 ግቦችን አስቆጥራለች፤ የተቆጠረባት ደግሞ አንድ ግብ ብቻ ነው፡፡

ስፔን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በፈረንጆቹ 2010 ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ ማሸነፏ የሚታወስ ሲሆን ÷ በድጋሚ በመድረኩ ለመንገስ ዛሬ በፍጻሜው ከአርጀንቲና ጋር የምታደርገው ፍልሚያ በጉጉት ይጠበቃል፡፡

አርጀንቲና እስካሁን ድረስ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በተጋጣሚዎቿ ላይ 19 ግቦችን ያስቆጠረች ሲሆን ÷ 7 ግቦች ደግሞ ተቆጥረውባታል፡፡

ኳታር ያዘጋጀችውን የ2022 የዓለም ዋንጫን ያነሳችው አርጀንቲና በተከታታይ ዋንጫውን ለማሸነፍ የምታደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡

ስፔን በታሪኳ ለ2ኛ ጊዜ እንዲሁም አርጀንቲና ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ለማሸነፍ የሚያደርጉት ትንቅንቅ በእግር ኳስ ቤተሰቡ ዘንድ በጉጉት ይጠበቃል፡፡

በፍጻሜ ተፋላሚዎቹ ተሸንፈው ጉዟቸው የተገታው እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ትናንት ምሽት 6 ሰዓት ላይ ባደረጉት ፍልሚያ እንግሊዝ 6 ለ 4 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡

https://www.fanamc.com/archives/319057
Пост от 18.07.2026 21:15
398
0
1
ቼልሲ ሞርጋን ሮጀርስን ለማስፈረም በቃል ደረጃ ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ እንግሊዛዊውን ሞርጋን ሮጀርስ ለማስፈረም ከአስቶን ቪላ ጋር በቃል ደረጃ መስማማቱ ተነግሯል፡፡

የ23 ዓመቱ አማካይ 117 ሚሊየን ፓውንድ በሆነ የዝውውር ዋጋ በቀጣይ ቀናት ለምዕራብ ለንደኑ ክለብ ፊርማውን እንደሚያኖር ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ሮጀርስ ለሰማያዊዎቹ ለስድስት ዓመታት የሚያቆይ ውል እንደሚፈርም የሚጠበቅ ሲሆን፥ ለተጨማሪ አንድ ዓመት በስታምፎርድ ብሪጅ የሚያቆይ አማራጭ በውሉ ተካትቷል፡፡

የህክምና ምርመራን ጨምሮ ቀሪ ጉዳዮችን የፊታችን ሰኞ ለማጠናቀቅ ቀጠሮ መያዙ ዘገባው አመልክቷል፡፡

ሻምፒዮኑ አርሰናል የሞርጋን ሮጀርስ ከፍተኛ ፈላጊ መሆኑ ሲገለጽ ቢቆይም ተጫዋቹ ቼልሲን ምርጫው ማድረጉ ነው የተገለጸው፡፡

በመልካም ፈቃዱ
Пост от 18.07.2026 11:05
102
0
1
ለዋንጫ የተገመተችው ፈረንሳይ ለደረጃ ትጫወታለች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2026 የዓለም ዋንጫ የደረጃ ጨዋታ በፈረንሳይ እና እንግሊዝ መካከል ይደረጋል፡፡

ለዋንጫው ተጠብቃ የነበረችው ፈረንሳይ ጉዞዋ በግማሽ ፍጻሜው በስፔን ተገትቶ የደረጃ ጨዋታ ለማድረግ ተገድዳለች፡፡

ፈረንሳይ በፈረንጆቹ 1998 እና 2018 የዓለም ዋንጫን ያሳካች ሲሆን፤ ለሦስተኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን የመሆን ሕልሟ በስፔን ብሔራዊ ቡድን ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

ፈረንሳይ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታውን አሸንፋ ቢሆን ለተከታታይ ሦስተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ በመገኘት ታሪክ የመስራት ዕድል ነበራት፡፡

ፈረንሳይ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከሴኔጋል፣ ኢራቅ፣ ኖርዌይ፣ ስዊድን፣ ፓራጓይ እና ከሞሮኮ ጋር ያደረገቻቸውን ጨዋታዎች ብታሸንፍም በግማሽ ፍጻሜው በስፔን ተሸንፋ ዋንጫ የማሳካት ጉዞዋ ከመንገድ ላይ ቀርቷል፡፡

በአሰልጣኝ ዲዴ ዴሻምፕ የምትመራው ፈረንሳይ እስከ ግማሽ ፍጻሜ ድረስ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች 16 ግቦችን ተጋጣሚዎቿ ላይ አስቆጥራ፤ የተቆጠረባት አራት ግብ ነው፡፡

አሰልጣኝ ዲዴ ዴሻምፕ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን እየመሩ የመጨረሻ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ሲሆን፤ ከዚህ ጨዋታ በኋላ ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር የሚለያዩ ይሆናል፡፡
https://web.facebook.com/share/p/1DGmo1Ha39/
Пост от 18.07.2026 10:58
1
0
0
ጋዜጣ ሲያነቡ ባገኙት የስራ ማስታወቂያ ወደ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነት የመጡት ሉዊስ ዴላፎንቴ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ወቅቱ የስፔን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ብሔራዊ ቡድኑን ወደ አሸናፊነት የሚያመጣ ሰው የሚፈልግበት ጊዜ ነበር፡፡

ግን በቂ ገንዘብ ስላልነበረው በክፍያ የማይደራደር እና በሚሰጠው እድል ተስማምቶ የሚሰራ አሰልጣኝ ለአዳጊ ቡድን እንፈልጋለን የሚል ማስታወቂያ በጋዜጣ አወጣ።

ወቅቱ ሉዊስ ዴላፎንቴ ከዲፖርቲቮ አላቬስ ጋር ተለያይተው ለ18 ወራት ያለ ስራ የተቀመጡበት ነበር።

ዴላፎንቴ በወቅቱ በፌዴሬሽኑ ውስጥ ይሰሩ የነበሩትን ኢኛኪ ሳኤዝን በስልክ ያነጋገሩ ሲሆን፤ ሳኤዝም ሀሳቡን ደግፈው ለእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ጥቆማ ሰጡ።

በወቅቱ የፌዴሬሽኑ የቅጥር ኃላፊ የነበሩት ጊኔስ መሌንዴዝ ከዴላፎንቴ ጋር ማድሪድ ውስጥ ከተወያዩ በኋላ ለ3 ወራት በሚቆይ አጭር የሙከራ ጊዜ ውል የእድሜ እርከን ቡድኑ አሰልጣኝ አድርገው ቀጠሯቸው።

ሉዊስ ዴላፎንቴ በጋዜጣ በወጣ ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ እግራቸው የስፔን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ደጅ ደረሰ።

የዴላፎንቴን የሕይወት ታሪክና ውጣ ውረድ በመጽሐፍ መልክ ያዘጋጀው ኤድዋርድ ቨርዱ በወቅቱ የነበረውን ሁነት ሲገልጽ፤ “እሱ የመጣው በጊዜያዊ ውል እና በብሔራዊ ቡድኑ ውስጥ ያለው ቆይታ በማንኛውም ሰዓት ሊያበቃ ይችላል በሚል ስሜት ነበር” ሲል የዴላፎንቴን የመጀመሪያ ቅጥር ያስታውሰዋል።
https://web.facebook.com/share/p/19Cdfj7kJK/
Пост от 17.07.2026 17:42
1 296
0
1
ሊቨርፑል የዶሚኒክ ሶቦዝላይን ውል አራዘመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል የመሐል ሜዳ ተጫዋቹን ዶሚኒክ ሶቦዝላይ ውል ለተጨማሪ ዓመታት ማራዘሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ዶሚኒክ ሶቦዝላይ በውሉ መሰረት በሊቨርፑል ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2031 ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡

ሶቦዝላይ በፈረንጆቹ 2023 ከጀርመኑ ክለብ አርቢ ሌፕዚሽ ቀዮቹን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

ተጫዋቹ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለሊቨርፑል በሁሉም ውድድሮች ባደረጋቸው 53 ጨዋታዎች 13 ግቦችን አስቆጥሮ 12 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡

ሶቦዝላይ ሊቨርፑል ለ2026/27 የውድድር ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታን ይዞ እንዲያጠናቀቅ ትልቅ ሚና ከነበራቸው ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው፡፡

ሶቦዝላይ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት የሊቨርፑል የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ መመረጡ ይታወሳል፡፡

ዶሞኒክ ስቦዝላይ ሊቨርፑልን ከተቀላቀለ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በሁሉም ውድድሮች 147 ጨዋታዎችን አድርጎ 28 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

የ25 ዓመቱ ተጫዋች በ2024/25 የውድድር ዓመት ከሊቨርፑል ጋር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አሳክቷል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 17.07.2026 14:24
341
0
2
ፔሌ በ1958ቱ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ የለበሰው ማሊያ 4 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላር ተሸጠ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞው የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ፔሌ በ1958ቱ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ የለበሰው ማሊያ 4 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላር ተሽጧል፡፡

በዚያ ዓለም ዋንጫ ብራዚል ስዊድንን በማሸነፍ የዋንጫው ባለቤት በሆነችበት የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ፔሌ ሁለት ግቦቸን አስቆጥሮ ነበር፡፡

በወቅቱ የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ሲያሳካ የ17 ዓመት ወጣት የነበረው ፔሌ የዓለም ዋንጫን ማሸነፍ የቻለ በዕድሜ ትንሹ ተጫዋች ነው፡፡

በአጠቃላይ ሦስት ጊዜ ከሀገሩ ብራዚል ጋር የዓለም ዋንጫን ማሳካት የቻለ ሲሆን፥ በዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ግብ ያስቆጠረ በዕድሜ ትንሹ ተጫዋች (17) በመሆን አሁንም ድረስ ክብረወሰኑን ይዞ ይገኛል።

በ1986 የዓለም ዋንጫ ላይ ዲያጎ ማራዶና በእንግሊዝ ላይ 'የእግዜር እጅ' በመባል የሚታወቀውን ግብ ሲያስቆጥር የለበሰው ማሊያ በ2022 በ7 ነጥብ 1 ሚሊየን ፓውንድ መሸጡ ይታወሳል፡፡

የፔሌ ማሊያ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ተጫዋች ማራዶና ቀጥሎ ከፍተኛ ዋጋ የወጣለት የእግር ኳስ ማሊያ ሆኗል።

በወንድማገኝ ጸጋዬ
Изображение
Изображение
Изображение
Смотреть все посты