Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.4K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 110
Сегодня
-28
Просмотров на пост
Всего
1 732
ER
Общий
4.24%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 436 постов
Смотреть все посты
Пост от 17.05.2026 21:37
1
0
0
ኒውካስል ዌስትሃምን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛው ሳምንት እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኒውካስል ዩናይትድ ዌስትሃምን 3 ለ 1 አሸንፏል።

ከሰሜን ለንደኑ ቡድን ቶተንሃም ጋር እየተፎካከረ የሚገኘው ዌስትሃም በፕሪሚየር ሊጉ የመቆየት ዕድሉን ያጠበበ ሽንፈት በኒውካስል ዩናይትድ አስተናግዷል።

ዊሊያም ኦሱላ (ሁለት) እና ኒክ ዋልትማደ የኒውካስልን ግቦች ሲያስቆጥሩ፥ ታቲ ካስቴላኖስ የዌስትሃምን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።

በዚህ መሰረት ቶተንሃም ማክሰኞ ዕለት ከቼልሲ የሚያደርገውን ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ ዌስትሃም ዩናይትድ መውረዱን የሚያረጋግጥ ይሆናል።

ቀደም ብለው በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ኖቲንግሃም ፎረስትን 3 ለ 2፣ ሰንደርላንድ እና ኤቨርተንን 3 ለ 1፣ ሊድስ ዩናይትድ ብራይተንን 1 ለ 0 አሸንፈዋል።

እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከክሪስታል ፓላስ 2 ለ 2 እንዲሁም ወልቭስ ከፉልሃም 1 ለ 1 ተለያይተዋል።
Пост от 17.05.2026 19:59
341
0
1
ኢትዮጵያ 2ኛውን የብር ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጋና አክራ እየተካሄደ ባለው 24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 2ኛውን የብር ሜዳሊያ አገኘች።

በጦር ውርወራ ወንዶች አትሌት ኦታጌ ኦባንግ ሁለተኛ በመውጣት በውድድሩ ለኢትዮጵያ 13ኛውን ሜዳሊያ አስገኝቷል።

በ400 ሜትር መሰናክል ሴቶች አትሌት ባንቻየሁ ተሰማ 5ኛ፤ አትሌት ደራርቱ እኖታ 6ኛውን ደረጃ ይዘው አጠናቅቀዋል።

በወርቅነህ ጋሻሁን
Пост от 17.05.2026 19:33
274
0
1
በ24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6ኛውን የነሐስ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጋና አክራ እየተካሄደ ባለው 24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6ኛውን የነሐስ ሜዳሊያ አገኘች።

በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል በአትሌት አልማዝ ዮሐንስ ርቀቱን 9:33:46 በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ 3ኛ በመውጣት የነሐስ ሜዳሊያ አግኝታለች።

በውድድሩ የተሳተፈችው ሌላኛዋ አትሌት ወሰኔ አሰፋ ደግሞ በ9:41:76 በሆነ ሰዓት በመግባት 4ኛ ደረጃ ይዛ አጠናቅቃለች።

በወርቅነህ ጋሻሁን
Пост от 17.05.2026 19:06
412
0
1
ሰንደርላንድ እና ሊድስ ዩናይትድ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሰንደርላንድ እና ሊድስ ዩናይትድ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል።

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የተካሄደው የሰንደርላንድ እና ኤቨርተን ጨዋታ በሰንደርላንድ 3 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

በጨዋታው የሰንደር ላንድ ግቦችን ኢንዞ ለፌ፣ ብራያን ብሮቤይ እና ዊልሰን ኢሲዶር ሲያስቆጥሩ÷ ሜርሊን ሮህል የኤቨርተንን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።

በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገው የሊድስ ዩናይትድ እና ብራይተን ጨዋታ በሊድስ 1 ለ 0 አሸናፊነት ሲጠናቀቅ÷ ዶሚኒክ ካልቨርት ሊዊን የማሸነፊያዋን ግብ አስቆጥሯል።

እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በተደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ብሬንትፎርድ ከክሪስታል ፓላስ 2 ለ 2፤ ወልቭስ ከፉልሃም 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል።
👍 1
Пост от 17.05.2026 17:09
590
0
1
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 0 በማሸነፍ የ2018 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆኗል።

የ2018 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ፍፃሜውን አግኝቷል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ እስከ ሊጉ መጨረሻ ጨዋታ በነጥብ እኩል ሆነው ዛሬ በተገናኙበት ጨዋታ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

በጨዋታው ረድኤት አስረሳኸኝ እና እሙሽ ዳንኤል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።

ውጤቱን ተከትሎ ነጥቡን 69 ያደረሰው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2018 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ መሆን ችሏል።

በዚህም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ለተከታታይ 6ኛ ጊዜ እና በአጠቃላይ ለ9 ጊዜ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል።

በሊጉ የኢትዮ ኤሌክትሪክ ተጫዋች ዳግማዊት ሰለሞን በ24 ግቦች ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆና አጠናቅቃለች።

በእንዳልካቸው ወዳጄ
👏 1
Пост от 17.05.2026 16:30
741
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ ኖቲንግሃም ፎረስትን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ ኖቲንግሃም ፎረስትን 3 ለ 2 አሸንፏል።

ቀን 8:30 ላይ በኦልድ ትራፎርድ በተደረገው ጨዋታ የዩናይትድን ግቦች ሉክ ሻው፣ ማቲዎስ ኩንሃ እና ብራያን ምቤሞ አስቆጥረዋል።

የኖቲንግሃም ፎረስትን ከመሸነፍ ያልታደጋቸውን ግቦች ደግሞ ሞራቶ እና ጊብስ ዋይት ከመረብ አሳርፈዋል።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ብሬንትፎርድ ከክሪስታል ፓላስ፣ ሊድስ ዩናይትድ ከብራይተን፣ ወልቭስ ከፉልሃም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

እንዲሁም ምሽት 1፡30 ላይ ላለመውረድ እየተፋለመ የሚገኘው ዌስትሃም ኒውካስልን ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ይገጥማል።
Пост от 17.05.2026 15:17
871
0
1
ቼልሲ ዣቢ አሎንሶን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ ስፔናዊውን አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶን የክለቡ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን ይፋ አድጓል።

የ44 ዓመቱ አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ በቼልሲ ቤት ከፈረንጆቹ ሐምሌ 1 ቀን 2026 እስከ 2030 ለ4 ዓመታት ለመቆየት ተስማምቷል።

ከዚህ ቀደም የስፔኑ ሪያል ማድሪድ እና የጀርመኑ ባየር ሌቨርኩሰን አሰልጣኝ የነበረው አሎንሶ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጠንካራ ተፎካካሪ እንደሚሆን ይጠበቃል።

አሰልጣኙ ቼልሲን ወደሚቀጥለው የስኬት ምዕራፍ ያሸጋግረዋል የሚል ሙሉ እምነት ተጥሎበት ወደ ምዕራብ ለንደኑ ቡድን መምጣቱ ተገልጿል።

አሰልጣኙ በሰጠው የመጀመሪያ አስተያየትም ቼልሲ በዓለም እግር ኳስ ውስጥ ካሉ ታላላቅ ክለቦች አንዱ ነው፤ የዚህ ታላቅ ክለብ ዋና አሰልጣኝ መሆን ለእኔ ታላቅ ክብር ነው ብሏል።

በክለቡ በከፍተኛ ደረጃ በቋሚነት መወዳደር እና ለዋንጫዎች መፋለም የሚችል ጠንካራ ቡድን የመገንባት ፍላጎት እንዳለውም ተናግሯል።
Смотреть все посты