Каталог каналов Каналы в закладках Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.0K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 977
Сегодня
-34
Просмотров на пост
Всего
1 886
ER
Общий
4.11%
Суточный
3.2%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 18 954 постов
Смотреть все посты
Пост от 05.04.2026 17:10
172
0
2
ነገሌ አርሲ አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ነገሌ አርሲ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የነገሌ አርሲን ግቦች ዳዊት ተፈራ እና ርሆቦት ሶላሎ አስቆጥረዋል፡፡

አዳማ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ዳዋ ሆቴሳ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በሌላ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1 ለ 0 እየመራ የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቅቋል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እየተካሄደ በሚገኘው ጨዋታ ሀዋሳ ከተማን መሪ ያደረግቸውን ግብ ያሬድ ብሩክ ከመረብ አሳርፏል፡፡
Пост от 05.04.2026 16:33
69
0
1
ሀገር አቀፍ የባህል ስፖርቶች ውድድርና የባህል ስፖርቶች ፌስቲቫል ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 23ኛው የባህል ስፖርቶች ውድድርና 19ኛው የባህል ስፖርቶች ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት ተጠናቅቋል፡፡

"የባህል ስፖርቶች ልማት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ለአንድ ሳምንት በሀረር ከተማ ሲካሄድ ቆይቷል፡፡

የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ሕይወት መሐመድ በፍጻሜ መርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የባህል ስፖርቶች ውድድሮችና የባህል ፌስቲቫል ወንድማማችነትና እህትማማችነት የተረጋገጠበት ነው ብለዋል፡፡

በባህል ስፖርቶች ውድድር የኦሮሚያ ክልል በ61 ነጥቦች የአጠቃላይ ስፖርት ውድድሮች አሸናፊ ሆኗል።

በ19ኛው የባህል ስፖርቶች ፌስቲቫል ደግሞ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሸናፊ ሲሆን፥ ኦሮሚያና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሁለተኛ እና ሦስተኛ በመሆን አጠናቅቀዋል።

24ኛው የባህል ስፖርቶች ውድድርና 20ኛው የባህል ፌስቲቫል በሲዳማ ክልል የሚካሄድ ይሆናል፡፡

በተሾመ ኃይሉ
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 05.04.2026 16:30
20
0
1
"በቀጣዮቹ አስር ዓመታት አሸናፊ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት እንደ ሀገር ከተያዘው የ15 ዓመት በታች የታዳጊዎች የእግር ኳስ ፕሮጀክት ውስጥ በአዲስ አበባ ከተማ ተመልምለው በመሰልጠን ላይ የሚገኙትና ተስፋ የተጣለባቸው ታዳጊዎች በአዲስ ስፖርት ፓርክ ውስጥ ልምምዳቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ" - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Пост от 05.04.2026 14:47
399
0
1
ለአትሌቶች የተሰጠው እውቅና ተተኪዎችን የሚያበረታታ ነው - ቀነኒሳ በቀለ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መንግስት ለአንጋፋ አትሌቶች የሰጠው እውቅና ተተኪ አትሌቶችን የሚያበረታታ ነው አለ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትናንትናው ዕለት መርቀው በከፈቱት የአዲስ ስፖርት ፓርክ አትሌት ቀነኒሳ በቀለን ጨምሮ 15 የኦሊምፒክ ጀግኖች የክብር ሐውልት እንደቆመላቸው ይታወቃል፡፡

አትሌቱ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው መልዕክት፥ ለአንጋፋ አትሌቶች የተሰጠው እውቅና ተተኪዎችን የሚያበረታታ መሆኑን ተናግሯል፡፡

እንደዚህ አይነት የስፖርት ማዕከላትን በኢትዮጵያ ማየት የዘወትር ህልሙ እንደነበር የገለፀው አትሌቱ፥ ምኞቴ እውን ሆኖ በመመልከቴ ደስተኛ ነኝ ብሏል፡፡

በፓርኩ ውስጥ የክብር ሐውልት ተሰርቶላቸው እውቅና ከተሰጣቸው አትሌቶች አንዱ በመሆኑ ኩራት እንደተሰማው ገልጿል፡፡

ፓርኩ የኦሎምፒክ ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳ፣ የፕሮፌሽናል እግር ኳስ፣ የቅርጫት ኳስ እና የቴኒስ ሜዳዎች እንዲሁም የመሮጫ መም ያካተተ መሆኑን አንስቷል፡፡

የስፖርት ፓርኩ እውን እንዲሆን እና ለአትሌቶቹ ክብር እንዲሰጥ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርቧል፡፡
👍 7
Пост от 05.04.2026 08:48
722
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ እና ነገሌ አርሲ ይገናኛሉ።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ሀዋሳ ከተማ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
Изображение
Пост от 04.04.2026 21:17
987
0
2
ቼልሲ ፖርትቬልን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኤፍ ኤ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ቼልሲ ፖርትቬልን 7 ለ 0 አሸንፏል።

ምሽት 1 ሰዓት ከ15 ላይ በተደረገው ጨዋታ የቼልሲን ግቦች ሀቶ፣ ጆአፔድሮ፣ ጋብሬል (በራስ ላይ)፣ አዳራብዮ፣ ሳንቶስ እና ኤስቴቫኦ ከመረብ አሳርፈዋል።

ቀደም ብሎ በተደረገው በኤፍ ኤ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 4 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል።

የሩብ ፍጻሜ ጨዋታው ቀጥሎ ሲካሄድ ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ሳውዝሃምፕተንን ይገጥማል።
Пост от 04.04.2026 20:13
964
0
1
ሲዳማ ቡና መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሲዳማ ቡና መቐለ 70 እንደርታን 1 ለ 0 አሸንፏል።

አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የሲዳማ ቡናን የማሸነፊያ ግብ አቤል ያለው ከመረብ አገናኝቷል።

እንዲሁም ቀን 10 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ኢትዮጵያ መድንን የገጠመው ኢትዮጵያ ቡና በቢንያም ጌታቸው ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል።

ቀደም ብለው በተደረጉ ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 ሲያሸንፍ ወላይታ ድቻ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 0 ለ 0 አቻ ተለያይተዋል።
👍 2
Смотреть все посты