Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.8K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 410
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
1 945
ER
Общий
4.64%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 831 поста
Смотреть все посты
Пост от 02.07.2026 16:49
1
0
0
የአርሰናል የቀድሞ ተጫዋች ሳንቲ ካዞርላ ራሱን ከእግር ኳስ ዓለም አገለለ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው የአርሰናል የቀድሞ ተጫዋች ሳንቲ ካዞርላ ራሱን ከእግር ኳስ ዓለም ማግለሉን ይፋ አድርጓል፡፡

የመድፈኞቹ የቀድሞ ተጫዋች ሳንቲ ካዞርላ በ41 ዓመቱ ጫማውን መስቀሉን በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡

ተጫዋቹ ያለፉትን ሦስት የውድድር ዓመታት በልጅነት ክለቡ ሪያል ኦቬዶ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

ሳንቲ ካዞርላ በተጨዋችነት ዘመኑ ለአርሰናል፣ ቪያሪያል፣ ማላጋ እና አል ሳድ ለመሳሰሉ ክለቦች ተጫውቶ አሳልፏል፡፡
Пост от 02.07.2026 13:50
1
0
0
ቶተንሃም ሆትስፐር ማቲያስ ፈርናንዴስን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር ማቲያስ ፈርናንዴስን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር ፖርቹጋላዊውን የመሀል ሜዳ ተጫዋች ለማስፈረም የክለቡ የዝውውር ክብረ ወሰን የሆነ ሒሳብ 85 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ አድርጓል፡፡

የ21 ዓመቱ ተጫዋች በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለዌስትሃም ዩናይትድ በሊጉ ሁሉንም ጨዋታዎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ማቲያስ ፈርናንዴስ በሰሜን ለንደኑ ክለብ ቆይታው 18 ቁጥር ማሊያ የሚለብስ ይሆናል፡፡
Пост от 02.07.2026 09:40
353
0
2
ፖርቹጋል ከክሮሺያ ፤ ስፔን ከኦስትሪያ…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው 23ኛው የዓለም ዋንጫ የ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

በዚህ መሰረትም የአንድ ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ስፔን ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከኦስትሪያ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

ምድቧን በበላይነት እየመራች ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለችው ስፔን ለዋንጫው ቅድመ ግምት ካገኙ ብሔራዊ ቡድኖች መካከል አንዷ ናት፡፡

ተጋጣሚዋ ኦስትሪያ በበኩሏ ከምድቧ በአራት ነጥብ ሁለተኛ ሆና ጥሎ ማለፉን መቀላቀሏ ይታወሳል፡፡

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሸናፊ ወደ ሩብ ፍጻሜ ለመግባት በሚደረገው ፍልሚያ ከፖርቹጋል እና ክሮሺያ አሸናፊ ጋር ይጫወታል፡፡

የጥሎ ማለፍ ጨዋታው ሲቀጥል ሌሊት 8 ሰዓት ላይ ፖርቹጋል ከክሮሺያ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ከየምድባቸው ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ጥሎ ማለፉን መቀላቀላቸው አይዘነጋም፡፡

የጨዋታው አሸናፊ ወደ ሩብ ፍጻሜ ለመግባት ከስፔን እና ኦስትሪያ አሸናፊ ጋር የሚገናኝ ይሆናል፡፡

በሌላ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ስዊዘርላንድ ከአልጄሪያ ነገ ጠዋት 12 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡
Пост от 02.07.2026 06:15
1
0
0
አሜሪካ16ቱን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32 ሀገራት ጥሎ ማለፍ ጨዋታ አሜሪካ ቦሲኒያ ሔርዞጎቪናን 2 ለ 0 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቅላለች።

የአሜሪካን የማሸነፊያ ግቦች ፎላሪን ባሎገን እና ማሊክ ቲልማን አስቆጥረዋል።

አዘጋጇ ሀገር አሜሪካ በቀጣዩ ዙር ሩብ ፍጻሜውን ለመቀላቀል ቤልጂዬምን የምትገጥም ይሆናል።
Пост от 01.07.2026 20:13
413
0
1
ፋሲል ከነማ ኢትዮጵያ መድንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 38ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ታምራት እያሱ ከመረብ አዋህዷል፡፡


ቀደም ሲል ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረጉ ጨዋታዎች መቐለ 70 እንደርታ ነገሌ አርሲን 3 ለ 0 እንዲሁም ድሬዳዋ ከተማ አርባ ምንጭ ከተማን 2 ለ 1 ማሸነፋቸው ይታወቃል።
Пост от 01.07.2026 17:17
1
0
0
መቐለ 70 እንደርታ እና ድሬዳዋ ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 38ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ ነገሌ አርሲን 3 ለ 0 አሸንፏል።

በዛሬው ዕለት ቀን 9 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታን ግቦች መሃሪ አምሃ፣ ብርሃኑ አዳሙ እና ፍሬዘር ካሳ አስቆጥረዋል።

እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ አርባ ምንጭ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል።

በጨዋታው የድሬዳዋ ከተማን ግቦች አስራት ቱንጆ እና አብዲሳ ጀማል ሲያስቆጥሩ፤ የአርባ ምንጭ ከተማን ብቸኛ ግብ መሪሁን መስቀለ ከመረብ አገናኝቷል።
Пост от 01.07.2026 07:11
1
0
0
ፈረንሳይ እና ሜክሲኮ 16ቱን ተቀላቀሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ፈረንሳይ እና ሜክሲኮ ተጋጣሚዎቻቸውን በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቅለዋል።

ሌሊት 6 ሰዓት ላይ ከስዊድን ጋር ጨዋታዋን ያደረገችው ፈረንሳይ በኪሊያን ምባፔ (2) እና ባርኮላ ግቦች 3 ለ 0 አሸንፋለች።

ውጤቱን ተከትሎ ፈረንሳይ 16ቱን የተቀላቀለች ሲሆን፥ ወደ ሩብ ፍጻሜ ለማለፍ ፓራጓይን ትገጥማለች።

በሌላ ጨዋታ አዘጋጇ ሀገር ሜክሲኮ ኢኳዶርን 2 ለ ዐ በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀል ችላለች።

ሜክሲኮ ሩብ ፍጻሜውን ለመቀላቀል ከእንግሊዝ እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ አሸናፊ ጋር ትገናኛለች።
Смотреть все посты