Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
12.0K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
38 558
Сегодня
-6
Просмотров на пост
Всего
2 138
ER
Общий
4.52%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 12 037 постов
Смотреть все посты
Пост от 14.03.2026 23:13
665
0
3
አርሰናል ኤቨርተንን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ኤቨርተንን 2 ለ 0 በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል፡፡

ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ በኢምሬትስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የአርሰናልን የማሸነፊያ ግቦች ቪክቶር ዮኬሬሽና ማክስ ዶውማን አስቆጥረዋል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 10 ማስፋት ችሏል።
👍 15
Пост от 14.03.2026 13:31
1
0
0
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የነበራቸውን የስራ ጉብኝት አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።

#PMOEthiopia
Пост от 14.03.2026 13:12
1 109
0
3
የፖሊስ ሰራዊት ከሰላም ተልዕኮው ጎን ለጎን የሀገርን ስም የሚያስጠሩ ስፖርተኞችን እያበረከተ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፖሊስ ሰራዊት ከሰላም ተልዕኮው ጎን ለጎን የሀገርን ስም የሚያስጠሩ ስፖርተኞችን በማፍራት የማይተካ ሚና እያበረከተ ነው አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፡፡

2ኛው የአዲስ አበባ ፖሊስ ስፖርት ውድድርና ፌስቲቫል "ተልዕኮን በጀግንነት፣ ስፖርትን በውጤት" በሚል መሪ ሀሳብ በዛሬው ዕለት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ተጀምሯል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ የፖሊስ ሰራዊት ከሰላም ጥበቃ ተልዕኮው ጎን ለጎን በዓለም አቀፍ መድረኮች የሀገራችንን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ የሚያደርጉ ዝነኛ ስፖርተኞችን በማፍራት ረገድ የማይተካ ሚና እያበረከተ ይገኛል ብለዋል፡፡

ይህ ተሳትፎ በቀጣይ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም ነው ከንቲባዋ የገለጹት፡፡

ውድድሩ በስድስት የስፖርት አይነቶች ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት በከተማዋ በሚገኙ የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
Пост от 14.03.2026 09:37
1 288
0
1
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

አርባ ምንጭ ከተማ ከኢትዮጵያ መድን ቀን 9 ሰዓት እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና ከአዳማ ከተማ ምሽት 12 ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሀዋሳ ከተማ ይገናኛሉ፡፡
Пост от 14.03.2026 09:27
951
0
1
የፕሪሚየር ሊጉ የዋንጫ ፉክክርና የዛሬ ወሳኝ ጨዋታዎች…


አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ30ኛ ሳምንት መርሐ ግብር በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝነት ያላቸው ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይደረጋሉ፡፡

የሊጉ መሪ አርሰናል በሜዳው ኤቨርተንን የሚያስተናግድ ሲሆን፥ ተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ ወደ ለንደን ስታዲየም አቅንቶ በወራጅ ቀጣና የሚገኘውን ዌስትሃም ዩናይትድ ይገጥማል፡፡

መድፈኞቹ ከኤቨርተን ጋር ባደረጓቸው ያለፉት አምስት የሊጉ ጨዋታዎች ሦስቱን ሲያሸንፉ፥ በሁለቱ ጨዋታዎች ነጥብ ተጋርተዋል፡፡

ባለፉት የሊጉ ሰባት ጨዋታዎች ሽንፈት ያላስተናገደው አርሰናል መሪነቱን ለማጠናከር ዛሬ ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ከኤቨርተን ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እያለው ከሊጉ መሪ አርሰናል በሰባት ነጥብ ዝቅ ብሎ 2ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ከሜዳው ውጪ ዌስትሃም ዩናይትድን ይገጥማል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ ሁሉንም በማሸነፍ የበላይነት አለው፡፡

ለቀጣይ ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ እየተፎካከረ የሚገኘው ቼልሲ ምሽት 2 ሰዓት ከ30 በስታምፎርድ ብሪጅ ኒውካስል ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ ያለፉት አምስት ግንኙነታቸው በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ድል ሲቀናቸው፥ ቀሪውን አንድ ጨዋታ በአቻ ውጤት አጠናቅቀዋል፡፡

በርንሌይ ከቦርንማውዝ፣ ሰንደርላንድ ከብራይተን በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት የሚደረጉ የዛሬ መርሐ ግብሮች ናቸው፡፡
Пост от 13.03.2026 20:13
1 142
0
1
ባህርዳር ከተማ እና ሲዳማ ቡና ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ባህርዳር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የባህርዳር ከተማን የማሸነፊያ ግቦች አንተነህ ተፈራ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ የሊጉ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ምድረ ገነት ሽረን 2 ለ 0 አሸንፏል።

የሲዳማ ቡና የማሸነፊያ ግቦችን ብርሀኑ በቀለ እና አቤል ያለው ከመረብ አሳርፈዋል።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄዱ የሊጉ ጨዋታዎች ሸገር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 0 ያሸነፈ ሲሆን፤ ፋሲል ከነማ እና መቻል 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 13.03.2026 17:07
1 275
0
1
ሸገር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሸገር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የሸገር ከተማን የማሸነፊያ ግቦች አሚር አብዶ እና ሚሊዮን ሀይሉ አስቆጥረዋል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ፋሲል ከነማ እና መቻል 0 ለ 0 ተለያይተዋል፡፡

የሊጉ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከባህር ዳር ከተማ እንዲሁም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሲዳማ ቡና ከምድረ ገነት ሽረ በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
👍 2
Смотреть все посты