Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.9K
13.6K
205
108
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 562
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 424
ER
Общий
5.99%
Суточный
4.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 939 постов
Смотреть все посты
Пост от 16.07.2026 17:09
1
0
0
አርሰናል ክሪስቶስ ሶሊስን ለማስፈረም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ክሪስቶስ ሶሊስን ከክለብ ብሩዥ ለማስፈረም ተስማምቷል፡፡

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ለተጫዋቹ ዝውውር 40 ሚሊየን ዩሮ እንደሚከፍል ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

የ24 ዓመቱ የፊት መስመር ተጫዋቹ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለክለብ ብሩዥ ባደረጋቸው 52 ጨዋታዎች 22 ግቦችን አስቆጥሮ 29 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
Изображение
Пост от 16.07.2026 12:18
184
0
2
የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ተፋላሚ ብሔራዊ ቡድኖች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል፡፡

የዓለም ዋንጫው የፍጻሜ ተፋላሚ ብሔራዊ ቡድኖችን የለየ ሲሆን ÷ በዚህም ስፔን እና አርጀንቲና ለዋንጫው ይፋለማሉ፡፡

ስፔን ለዋንጫ የተገመተችውን ሌላኛዋን ሀገር ፈረንሳይን በግማሽ ፍጻሜው 2 ለ 0 በማሸነፍ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኗ ይታወሳል፡፡

በአሰልጣኝ ሉዊስ ዴላፎንቴ የምትመራው ስፔን እስካሁን ድረስ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች ተጋጣሚዎቿ ላይ 13 ግቦችን አስቆጥራለች፤ የተቆጠረባት ደግሞ አንድ ግብ ብቻ ነው፡፡

ስፔን በፈረንጆቹ 2010 የዓለም ዋንጫን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሳካች ሲሆን÷ በድጋሚ በመድረኩ ለመንገስ በፍጻሜው ከአርጀንቲና ጋር ትፋለማለች፡፡

ተጋጣሚዋ ሀገር አርጀንቲና ደግሞ በግማሽ ፍጻሜው እንግሊዝን 2 ለ 1 በማሸነፍ የፍጻሜ ተፋላሚ ሆናለች፡፡

በጨዋታው እንግሊዝ ግብ በማስቆጠር ቀዳሚ ብትሆንም አርጀንቲና ከመመራት ተነስታ በማሸነፍ ለተከታታይ ሁለተኛ ጊዜ በዓለም ዋንጫ መድረክ ፍጻሜ ላይ ተገኝታለች፡፡

https://web.facebook.com/share/p/1DF45tx5u9/
Пост от 16.07.2026 00:11
127
0
2
አርጀንቲና እንግሊዝን በማሸነፍ ወደ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር አርጀንቲና እንግሊዝን በማሸነፍ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።

እንግሊዝ በአንቶኒ ጎርደን ግብ እስከ 85ኛው ደቂቃ ድረስ 1 ለ ዐ እየመራች ብትቆይም አርጀንቲና በኢንዞ ፈርናንዴዝ እና ላውታሮ ማርቲኔዝ ግቦች ጨዋታውን አሸንፋለች።

ሊዮኔል ሜሲ ለሁለቱም ግቦች ኳስ አመቻችቶ በማቀበል ቁልፍ ተጫዋች መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል።

አርጀንቲና በፍጻሜው ከስፔን ጋር ትፋለማለች፡፡
Пост от 15.07.2026 20:37
1
0
0
የተጠባቂው ጨዋታ አሰላለፍ ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የዓለም ዋንጫ ዛሬ ምሽት አርጀንቲና ከእንግሊዝ የሚያደርጉት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

የተጠባቂው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሰላለፍ ይፋ ሆኗል፡፡

በዚህም መሰረት በእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ጆርዳን ፒክፎርድ፣ ማርክ ጉኤሂ፣ ጆን ስቶንስ፣ ስፔንስ፣ አንደርሰን፣ ዴክላን ራይስ፣ ሪስ ጀምስ፣ ጁድ ቤሊንግሃም፣ ሞርጋን ሮጀርስ፣ ጎርደን እና ሃሪ ኬን በመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ ተካትተዋል፡፡

በአርጀንቲና በኩል ደግሞ ኤሚ ማርቲኔዝ፣ ታግላፊኮ፣ ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ፣ ክርስቲያን ሮሜሮ፣ ሞሊና፣ ማካሊስተር፣ ኤንዞ ፈርናንዴዝ፣ ፓራዴዝ፣ ስሞን፣ ሊዮኔል ሜሲን እና ጁሊያን አልቫሬዝን የመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ አካትታለች፡፡

ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ መደረግ የሚጀምር ሲሆን፤ የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሸናፊ በፍጻሜው ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር በመጪው እሁድ ዋንጫውን ለማንሳት ይጫወታል፡፡
Пост от 15.07.2026 00:04
456
0
2
ስፔን ፈረንሳይን በማሸነፍ ወደ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን ፈረንሳይን በማሸነፍ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።

የስፔንን ግቦች ኦያርዛባል (በፍጹም ቅጣት ምት) እና ፔድሮ ፖሮ አስቆጥረዋል።

ስፔን በፍጻሜው ከእንግሊዝ እና አርጀንቲና አሸናፊ ጋር ትገናኛለች፡፡
Пост от 14.07.2026 20:52
516
0
2
ማንቼስተር ዩናይትድ ዩሪ ቴሊማንስን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ቤልጂየማዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ዩሪ ቴሊማንስን ከአስቶን ቪላ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ ለዝውውሩ 35 ሚሊየን ፓውንድ የውል ማፍረሻ በመክፈል ተጫዋቹን ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል፡፡

የ29 ዓመቱ አማካይ በኦልድትራፎርድ እስከ ፈረንጆቹ 2031 ድረስ የሚያቆውን ውል ፈርሟል፡፡

ቴሊማንስ በ2023 ከሌስተር ሲቲ አስቶን ቪላን የተቀላቀለ ሲሆን፥ በተጠናቀቀው የ2025/26 የውድድር ዓመት ከቪላ ጋር የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል፡፡

ተጫዋቹ በዚህ ክረምት ለማንቼስተር ዩናይትድ ፊርማውን ያኖረ ሦስተኛው ተጫዋች ሲሆን፥ ዩናይትድ ቀደም ሲል ሌላኛውን አማካይ አንድሬይ ሳንቶስ ከቼልሲ እንዲሁም ዌልሳዊውን ግብ ጠባቂ ካርል ዳርሎን በነጻ ዝውውር ማስፈረሙ ይታወቃል፡፡
Пост от 14.07.2026 20:47
1
0
0
ስፔን ከፈረንሳይ - የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ ቋሚ አሰላለፍ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የዓለም ዋንጫ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ፈረንሳይ ከስፔን የሚያደርጉት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች በምሽቱ ጨዋታ የሚጠቀሙትን ቋሚ አሰላለፍ ይፋ አድርገዋል፡፡

በዚህም መሰረት ስፔን ኡናይ ሲሞን፣ ፔድሮ ፖሮ፣ ኩባርሲ፣ ላፖርት፣ ኩኩሬያ፣ ሮድሪ፣ ፋቢያን ሩዪዝ፣ ኦልሞ፣ ላሚን ያማል፣ አሌክስ ባይና እና ኦያርዛብልን የመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ አካትታለች፡፡

በፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በኩል ኪሊያን ምባፔ፣ ኦሊሴ፣ ዴምቤሌ፣ ባርኮላ፣ ራቢዮት፣ ቹሃሚኒ፣ ዲኜ፣ ኡፓሚካኖ፣ ሳሊባ፣ ኩንዴ እና ማይግናን በቋሚ አሰላለፍ ወደ ሜዳ የሚገቡ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሸናፊ በፍጻሜው ከአርጀንቲና እና እንግሊዝ አሸናፊ ጋር ለዋንጫው ይፋለማል፡፡
Смотреть все посты