Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.4K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 196
Сегодня
-15
Просмотров на пост
Всего
1 755
ER
Общий
4.26%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 379 постов
Смотреть все посты
Пост от 14.05.2026 17:04
24
0
1
ምድረ ገነት ሽረ ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ምድረ ገነት ሽረ ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የምድረ ገነት ሽረን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አቤል እንዳለ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ መቻል ከነገሌ አርሲ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

በዚሁ ስታዲየም 10 ሰዓት ላይ መደረገ የጀመረው የወላይታ ድቻ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታ ያለምንም ግብ ቀጥሏል፡፡
Пост от 14.05.2026 15:09
510
0
1
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀድያ ሆሳዕና ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የሀድያ ሆሳዕናን ማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ደስታ ዋሚሾ ከመረብ አሳርፏል።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ ወላይታ ድቻ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ቀን 10 ሰዓት ላይ በተመሳሳይ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ምድረ ገነት ሽረ ከኢትዮጵያ ቡና ከ9 ሰዓት ጀምሮ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታውን እያደረገ ሲሆን÷ መቻል ከነገሌ አርሲ ምሽት 12 ሰዓት በተመሳሳይ ስታዲየም ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
Пост от 14.05.2026 14:21
628
0
2
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ዕጩዎች ይፋ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2025/26 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ዕጩዎች ይፋ ተደርገዋል፡፡

በዚህም የሊጉ መሪ አርሰናል አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ፣ የማንቼስተር ሲቲው አሰልጣኝ ፔፕ ጓርዲዮለ እና የማቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ በዕጩዎች ውስጥ መካተት ችለዋል።

እንዲሁም የብሬንትፎርድ አሰልጣኝ አንድሪውስ፣ የቦርንማውዝ አሰልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላ እና የሰንደርላንዱ አሰልጣኝ ሊ ብሪስ በዕጩዎች ዝርዝር ውስጥ ተካትተዋል፡፡
Пост от 14.05.2026 14:01
532
0
1
የአትሌት የብርጓል መለሰ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአትሌት የብርጓል መለሰ ሥርዓተ ቀብር በዛው ዕለት ተፈጽሟል።

የአትሌቷ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ቤተሰቦቿ፣ ወዳጅ ዘመዶቿ፣ የመከላከያ ሠራዊት አመራር እና አባላት በተገኙበት በመከላከያ የክብር ዘብ እና ማርሽ ባንድ በመታጀብ ነው የተፈጸመው።

የረጅም ርቀት ሯጭ አትሌት የብርጓል መለሰ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድሮች ስታስጠራ ቆይታለች፡፡

አትሌቷ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ጀምሮ በበርካታ አሕጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ በመካፈል ስኬታማ ጊዜያትን በአትሌቲክሱ ማሳለፏም የሚታወስ ነው፡፡

ሚያዚያ 1982 ዓ.ም የተወለደችው አትሌት የብርጓል ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ማለዳ በጃን ሜዳ የስፖርት ማዘውተሪያ ባገጠማት ድንገተኛ አደጋ በ36 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
Пост от 14.05.2026 13:38
663
0
1
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ዕጩዎች ይፋ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2025/26 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ዕጩዎች ይፋ ተደርገዋል፡፡

በዚህም የሊጉ መሪ አርሰናል ሦስት ተጫዋቾችን በዕጩዎች ዝርዝር ውስጥ በማስመረጥ ቀዳሚ ሲሆን÷ ግብ ጠባቂው ዴቪድ ራያ፣ ጋብሬል ማጋሌሽ እና ዴክላን ራይስ ተካትተዋል፡፡

ተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ ደግሞ ኤርሊንግ ብራውት ሀላንድን እና አንቷን ሴሜኒዮን በእጩ ዝርዝር ውስጥ ማካተት ችሏል፡፡

የማንቼስተር ዩናይትድ የመሐል ሜዳ ተጫዋች ብሩኖ ፈርናዴዝ፣ ኢጎር ቲያጎ ከብሬንትፎርድ እና ሞርጋን ጊብስ ዋይት ከኖቲንግሃም ፎረስት በእጩነት የቀረቡ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
Пост от 14.05.2026 10:37
924
0
1
ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድሮች ስታስጠራ የቆየችው አትሌት የብርጓል መለሰ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያዊቷ የረጅም ርቀት ሯጭ አትሌት የብርጓል መለሰ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድሮች ስታስጠራ ቆይታለች፡፡ አትሌት የብርጓል ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ጀምሮ በበርካታ አሕጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ በመካፈል ስኬታማ ጊዜያትን በአትሌቲክሱ አሳልፋለች፡፡ አትሌቷ በተለያዩ ውድድሮች ኢትዮጵያን በመወከል ከመሳተፍ ባለፈ ለሀገሯ ሜዳልያዎችን ማስገኘት ችላለች፡፡ በፈረንጆቹ 2015…

https://www.fanamc.com/archives/314749
Пост от 14.05.2026 09:55
983
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዕለቱ የመጀመሪያ መርሐ ግብር የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከሀድያ ሆሳዕና ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይገናኛሉ፡፡

ወላይታ ድቻ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ቀን 10 ሰዓት ላይ በተመሳሳይ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ምድረ ገነት ሽረ ከኢትዮጵያ ቡና 9 ሰዓት እንዲሁም መቻል ከነገሌ አርሲ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይገናኛሉ፡፡

ሊጉን ሲዳማ ቡና በ55 ነጥብ ሲመራ ነገሌ አርሲ (51)፣ መቻል (49) እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ (45) ከ2 እስከ 4 ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡

የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት አቤል ያለው በ14 ግቦች ሲመራ፥ አዲስ ግደይ እና ናትናኤል ዳንኤል በተመሳሳይ 10 ግቦች ይከተላሉ፡፡
Смотреть все посты