Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.6K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 574
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 192
ER
Общий
4.96%
Суточный
3.7%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 608 постов
Смотреть все посты
Пост от 09.06.2026 21:19
386
0
1
ሪያል ማድሪድ ዩሊያን አልቫሬዝን ለማስፈረም ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ አርጀንቲናዊውን ተጫዋች ዩሊያን አልቫሬዝ ለማስፈረም ለአትሌቲኮ ማድሪድ ያቀረበው የዝውውር ጥያቄ ውድቅ ተደርጓል፡፡

ሪያል ማድሪድ የ26 ዓመቱን የፊት መስመር ተጫዋች ከከተማ ተቀናቃኙ ለማስፈረም የ150 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሂሳብ በይፋ አቅርቧል፡፡

የሪያል ማድሪድ ፕሬዚዳንት ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በፊት በ150 ሚሊየን ዩሮ ኮከብ ተጫዋች እንደሚያስፈርሙ መናገራቸው ይታወሳል፡፡

አልቫሬዝ እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ በአትሌቲኮ ማድሪድ የሚያቆይ ውል ያለው ሲሆን፥ አትሌቲኮ ለተጫዋቹ የቀረበለትን የዝውውር ሂሳብ ውድቅ ማድረጉ ተመላክቷል፡፡

ሌላኛው የስፔን ክለብ ባርሴሎና በተመሳሳይ አርጀንቲናዊውን ተጫዋች ለማስፈረም ፍላጎት እንዳለው ሲገለጽ ቆይቷል፡፡
Пост от 09.06.2026 20:21
94
0
1
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ ጋር አቻ ተለያየ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ ጋር ያደረገውን ሁለተኛ ዙር የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 1 አቻ አጠናቅቋል።

በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንንግብ ቢንያም በላይ ሲያስቆጥር የማላዊን ግብ አዴፖጁ ባባቱንዴ ከመረብ አሳርፏል፡፡

ዋልያዎቹ በተመሳሳይ ስታዲየም ከቀናት በፊት ያደረጉትን የመጀመሪያ ዙር የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወሳል።
Пост от 09.06.2026 17:18
419
0
1
በዓለም ዋንጫ ከታዩ ያልተጠበቁ ድሎች አንዱ - ካሜሩን ከአርጀንቲና

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ36 ዓመታት በፊት የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በዛሬዋ ዕለት በዓለም ዋንጫ ውድድር የማይረሳ ታሪክ ጽፈዋል፡፡

በፈረንጆቹ 1990 ጣሊያን ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ አርጀንቲና እና ካሜሩን በሳን ሲሮ ስታዲየም ተገናኝተዋል፡፡

በወቅቱ ድንቅ ብቃት ላይ በነበረውና በዲያጎ አርማንዶ ማራዶና የሚመራው የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ለጨዋታው ቅድመ ግምት አግኝቷል፡፡

የእግር ኳስ ተንታኞችና ግምቶች ሁሉ ወደ አርጀንቲና ያመዘኑ ሲሆን ÷ ማንም ከአፍሪካ ለመጣው የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን ቦታ አልነበረውም።

የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን በወቅቱ በዓለም ዋንጫ መድረክ አንድም ጨዋታ አሸንፎ አያውቅም፤ በ1982 ተሳትፎውም ሦስት የአቻ ውጤት አስመዝግቦ ነው የተመለሰው፡፡

ሆኖም የካሜሩን ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች (የማይበገሩት አንበሶች) ወደ ጣሊያን የመጡት ለሽርሽር አልነበረም፤ ታሪክ ለመጻፍ እንጂ።

https://www.facebook.com/share/p/1EWv5FcuD4/?mibextid=wwXIfr
Пост от 09.06.2026 17:01
164
0
1
ሶማሊያዊው ዳኛ አርታን አሜሪካ እንዳይገባ ክልከላ ተደረገበት

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በዳኝነት እንዲመራ ተመርጦ የነበረው ሶማሊያዊው ዳኛ ኦማር አርታን አሜሪካ እንዳይገባ ክልከላ ተደረገበት፡፡

በፈረንጆቹ 2025 የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ዳኛ በመባል የተመረጠው ኦማር አርታን ዓለም ዋንጫን የሚዳኝ የመጀመሪያው ሶማሊያዊ እንደሚሆን ሲጠበቅ ነበር፡፡

ሆኖም ግን አሜሪካ ማያሚ እንዳይገባ በዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር እገዳ እንደተጣለበት ተገልጿል፡፡

ዳኛው ስለታገዱበት ምክንያት ከአሜሪካ ኢሚግሬሽን ባለስልጣን የተሰጠ ይፋዊ ማብራሪያ ባይኖርም፤ ሀገሩ ሶማሊያ በዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጉዞ እገዳ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗ ይታወቃል፡፡

ፊፋ የአሜሪካ ባለስልጣናትን በጉዳዩ ላይ ካነጋገረ በኋላ ዳኛው በውድድሩ ላይ በዳኝነት እንደማይሳተፍ አረጋግጧል፡፡

ፊፋ በሀገራት የቪዛ ሂደት ጣልቃ መግባት እንደማይችል በመግለጽ ለዳኛ ኦማር አብዱልቃድር አርታን ጉዳይ መፍትሄ መስጠት እንደማይችልም አስታውቋል፡፡

የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ከዓለም ዋንጫው ጋር በተገናኘ በተለያዩ አካላት ላይ በሚጥላቸው እገዳዎች ምክንያት ከዓለም አቀፉ የስፖርት ቤተሰብ ዘንድ ትችቶችን እያስተናገደ ይገኛል፡፡

በአቤል ነዋይ
😢 2
Пост от 09.06.2026 11:04
265
0
2
ሊሊያን ቱራም እና ማርከስ ቱራም - አባትና ልጅ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን በተለያዩ ጊዜያት በዓለም ዋንጫ መወከል የቻሉት አባትና ልጅ ሊሊያን ቱራም እና ማርከስ ቱራም፡፡

የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በፈረንጆቹ 1998 የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሲሆን ትልቅ አስተዋፅኦ ከነበራቸው ተጫዋቾች አንዱ አባት ሊሊያን ቱራም ነበር።

‎የአባታቸውን ፈለግ የተከተሉት ልጆቹ ማርከስ እና ኬፍራን ቱራም እግር ኳስን በታላቅ ደረጃ እየተጫወቱ ይገኛሉ፡፡

የኢንተርሚላን የፊት መስመር ተጫዋቹ ትልቁ ማርከስ ቱራም እንደ አባቱ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን የመወከል እድልን አግኝቷል።

‌‎በ2022ቱ የኳታር ዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ተፋላሚ የነበረው ማርከስ ቱራም በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ለሻምፒዮንነት ከተገመቱ ብሔራዊ ቡድኖች አንዱ በሆነው የዲዲዬ ዴሾ ስብስብ አካል ሆኖ ሰሜን አሜሪካ ይከትማል።

የማርከስ ቱራም ታናሽ ኬፍራን በጣሊያን ሴሪ ኤ በዩቬንተስ ጥሩ የሚባል ጊዜ ቢያሳልፍም፥ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዲዲዬ ዴሾን ማሳመን ባለመቻሉ ሳይመረጥ ቀርቷል።

በሙባረክ ፈንታው
Пост от 09.06.2026 09:06
286
0
1
ኢትዮጵያ ከማላዊ - የወዳጅነት ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ አቻው ጋር ሁለተኛ ዙር የወዳጅነት ጨዋታውን በዛሬው ዕለት ያደርጋል፡፡

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ የሚደረግ ይሆናል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም በተደረገው የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በፍጹም ጥላሁን ብቸኛ ግብ ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
Пост от 08.06.2026 10:33
531
0
3
በዓለም ዋንጫ የተለያዩ ሀገራትን የወከሉት አባትና ልጅ…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ልጅ ሉካ ዚዳን ሞሮኮን በመወከል በሰሜን አሜሪካ ሀገራት በሚሰናደው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ይሳተፋል፡፡

ከዚህ ቀደም አባቱ ዚነዲን ዚዳን ከፈረንሣይ ብሔራዊ ቡድን ጋር በመድረኩ ወርቃማ ጊዜያትን አሳልፏል፡፡

‎ዚዳን የሚለው ስም በእግር ኳሱ ዓለም እንዲናኝ ያደረገው ዚነዲን ዚዳን በፈረንሣይ ብሔራዊ ቡድን እጅግ የተሳካ ጊዜ ስለነበረው ነው፡፡

‌‎ሀገሩ ለመጀመሪያ ጊዜ አሰናድታ ሻምፒዮን በሆነችበት የ1998ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ኮከብ ከመሆኑም ባለፈ በ2006ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ የፍፃሜ ተፋላሚ ነበር።

‎በእግር ኳስ ታሪክ ከታዩ ምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ዚነዲን ዚዳን ልጅ ሉካ ዚዳን በአንጻሩ ከፈረንሳይ ይልቅ ለአያቶቹ ሀገር አልጄሪያ መጫወትን መርጧል፡፡

‎ሉካ ዚዳን በሰሜን አሜሪካ በሚካሄደው አለም ዋንጫ የበረሃ ቀበሮዎቹ ግብ ጠባቂ በመሆን እንደ አባቱ በዓለም ዋንጫው ተሳትፎ ያደርጋል፡፡

በሙባረክ ፈንታው
😢 1
Смотреть все посты