Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
11.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
39 479
Сегодня
-3
Просмотров на пост
Всего
1 984
ER
Общий
4.56%
Суточный
3.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 11 906 постов
Смотреть все посты
Пост от 28.01.2026 10:06
540
0
1
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች …

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል እና ባየርንሙኒክ ቀድመው ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፋቸውን ባረጋገጡበት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ የመጨረሻ መርሐ ግብሮች ዛሬ ምሽት ይከናወናሉ፡፡

ካይራት፣ ስላቪያ ፕራግ፣ ቪያሪያል እና አይንትራፍራንክፈርት ከውድድሩ የተሰናበቱ ሲሆን ቀሪ 30 ቡድኖች ወደ 16ቱ ለማለፍ ዛሬ ምሽት ተጋድሎ ያደረጋሉ፡፡

ከ1ኛ እስከ 8ኛ ደረጃን ይዘው የሚያጠናቅቁት በቀጥታ ጥሎ ማለፉን የሚቀላቀሉ ሲሆን ከ9ኛ እስከ 24ኛ ደረጃን የሚያገኙት ደግሞ በእርስ በርስ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ 16ቱን ለመቀላቀል ይጫወታሉ።

አርሰናል እና ባየርንሙኒክ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃን በመያዝ ጥሎ ማለፉን ቀድመው የተቀላቀሉ ክለቦች ሲሆኑ ከ3ኛ እስከ 32ኛ ደረጃ የተቀመጡት ቡድኖች ግን በቀጥታ ማለፋቸውን እና ለጥሎ ማለፍ መብቃታቸውን ለማረጋገጥ የመጨረሻ ፍልሚያቸውን ዛሬ ያደርጋሉ፡፡

ሁሉም የሻምፒየንስ ሊግ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት በተመሳሳይ 5 ሰዓት የሚደረጉ ሲሆን ሰባቱን የምድብ ጨዋታዎች ያሸነፈው አርሰናል ምንም ጨዋታ ማሸነፍ ያልቻለውን የካዛኪስታኑ ካይራትን በኤምሬትስ ያስተናግዳል።

አርሰናል በሜዳው ቲኒሹ ካይራትን ማሸነፍ ከቻለ በአዲሱ የጨዋታ ቅርጽ ሁሉንም ጨዋታዎች ያሸነፈ የመጀመሪያው ክለብ ይሆናል፡፡

ፒኤስጂ ከኒውካስትል ዩናይትድ፣ ሪያል ማድሪድ ከቤኔፊካ፣ ናፖሊ ከቼልሲ፣ ሊቨርፑል ከካራባግ፣ ባየርንሙኒክ ከፒኤስቪ፣ ማንችስተር ሲቲ ከጋላታሳራይ፣ ኢንተር ሚላን ከቦርሲያ ዶርትሙንድ፣ ጁቬንቱስ ከሞናኮ፣ ባርሴሎና ከኮፐንሀገን እንዲሁም አይንትራ ፍራንክፈርት ከቶተንሀም ሆትስፐር ምሽት ከሚደረጉት ተጠባቂ ጨዋታች መካከል ናቸው፡፡
👍 2
Пост от 27.01.2026 21:08
1 126
0
1
አስቶንቪላ ታሚ አብርሃምን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አስቶንቪላ እንግሊዛዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ታሚ አብርሃምን ከቤሺክታሽ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

በአሰልጣኝ ኡናይ ኢምሬ የሚመራው አስቶንቪላ ለታሚ አብርሃም ዝውውር 18 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ ማድረጉ ተመላክቷል፡፡

እንግሊዛዊው የ28 ዓመት ተጫዋች ከፈረንጆቹ 2021 በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊግ የተመለሰ ሲሆን÷ በቪላ ፓርክ ለአራት ዓመት ከግማሽ የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

ታሚ አብርሃም ከዚህ ቀደም በ2018/19 የውድድር ዓመት ለአስቶንቪላ በውሰት ውል መጫወቱ ይታወሳል፡፡

ተጫዋቹ ለቼልሲ፣ ኤሲሚላን፣ ሮማ እና ቤሺክታሽ ለመሳሳሉ ክለቦች ተጫውቶ ማሳለፉ አይዘነጋም፡፡

በስፔናዊው አሰልጣኝ የሚመራው አስቶንቪላ በፕሪሚየር ሊጉ 46 ነጥቦችን በመሰብሰብ 3ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
👍 3
Пост от 27.01.2026 20:09
1 019
0
1
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ተስፋዬ ታምራት አስቆጥሯል፡፡

አስቀድሞ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ነገሌ አርሲ ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ÷ ሸገር ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ያለምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
👍 1
Пост от 27.01.2026 19:10
1 059
0
1
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከጣልያኑ ትጥቅ አቅራቢ ተቋም ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከጣልያኑ ትጥቅ አቅራቢ ተቋም ማክሮን ጋር በጋራ ለመስራት ተስማምቷል፡፡

ማክሮን ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት የዋልያዎቹ የትጥቅ አጋር ሆኖ እንደሚሰራ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።

በስምምነቱ መሠረት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከማክሮን ትጥቅ አምራች ተቋም ማልያ ሲገዛ 60 በመቶ ቅናሽ እንደሚደረግለት ነው የተገለጸው፡፡

በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ እና ዓለም ዋንጫ ካለፈ የተለያየ ጥቅማ ጥቅም እንደሚያገኝ ተመላክቷል፡፡

በትዝታ ወንድሙ
👍 1
Пост от 27.01.2026 17:10
1 133
0
1
ነገሌ አርሲ ሲዳማ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ነገሌ አርሲ ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የነገሌ አርሲን ግብ ዳዊት ተፈራ (ፍ) አስቆጥሯል።

በተመሳሳይ ሰዓት አዲስ አበባ ስታዲየም የተካሄደው የሸገር ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ የኢትዮጵያ ቡና እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይገናኛሉ።
Пост от 27.01.2026 14:15
1 248
0
1
ፓትሪክ ዶርጉ ከሁለት ወራት በላይ ከሜዳ ይርቃል

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዴንማርካዊው የማንቼስተር ዩናይትድ ተጫዋች ፓትሪክ ዶርጉ ባጋጠመው ጉዳት ከሁለት ወራት በላይ ከሜዳ እንደሚርቅ ተነግሯል።

ተጫዋቹ ማንቼስተር ዩናይትድ ባሳለፍነው እሁድ አርሰናልን 3 ለ 2 ባሸነፈበት ጨዋታ ላይ ድንቅ ግብ ማስቆጠሩ ይታወሳል።

በጨዋታው ጉዳት አስተናግዶ ከሜዳ የወጣው ዶርጉ፥ በዚህም እስከ 10 ሳምንታት ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።
Пост от 27.01.2026 08:55
1 594
0
0
ከ2010 የዓለም ዋንጫ በኋላ ምርጥ ብቃቱ የከዳው ቶሬስ...

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዓለም እግር ኳስ ከተመለከታቸው ምርጥ የፊት መስመር ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው የስፔን ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ኮከብ ፈርናንዶ ቶሬስ፡፡

ቶሬስ በተጫዋችነት ዘመኑ ከምርጥ አጥቂዎች መካከል አንዱ የነበረ ሲሆን÷ በፍጥነቱ፣ በጎል አስቆጣሪነቱ እና በድንቅ ችሎታው ይታወቃል፡፡

ፈርናንዶ ቶሬስ ለተከላካዮች ፈታኝ ከመሆኑ ባለፈ ጥንካሬው፣ ፍጥነቱ፣ ጉልበቱና የአጨራረስ ብቃቱ አስገራሚ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ቶሬስ ወደ አንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ በመጣበት በመጀመሪያው የውድድር ዓመቱ በ33 የሊጉ ጨዋታዎች 24 ግቦችን ለሊቨርፑል ማስቆጠር ችሏል፡፡

በወቅቱ ሊቨርፑል እንደ ቡድን ደካማ ቢሆንም ቶሬስ ግን በአንፊልድ በነበረው ቆይታ በግሉ ምርጥ ብቃት ላይ ነበር፤ከሊቨርፑል በተጨማሪም ለአትሌቲኮ ማድሪድ፣ ቼልሲ እና ኤሲሚላን ተጫውቶ አሳልፏል፡፡

ተጫዋቹ ከምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ጋር የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ፣ ዩሮፓ ሊግ እና የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን ማሳካቱ አይዘነጋም፡፡

በቼልሲ በነበረው ቆይታ ከቡድኑ ጋር ዋንጫዎችን ያሳካ እንጂ በሊቨርፑል ያሳየውን ምርጥ ብቃት ግን ማስቀጠልና ማጠናከር አልቻለም ነበር፡፡

ፈርናንዶ ቶሬስ ዋናውን የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከፈረንጆቹ 2003 ጀምሮ እስከ 2014 ድረስ ያገለገለ ሲሆን÷ በ2010 የዓለም ዋንጫን አሳክቷል፡፡ለስፔን ብሄራዊ ቡድን ባደረጋቸው 110 ጨዋታዎች 38 ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡፡

ከሀገሩ እና ከክለብ ስኬቶቹ በተጨማሪ በግሉ ... 👇
https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid02za3JmGeafvB1RT8UaSt4uGWAKyVf3ohPA3QkojsoYccf2bEDdMmLUtpUEpAKC9Xjl
Изображение
Смотреть все посты