Каталог каналов Каналы в закладках Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.0K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 933
Сегодня
-11
Просмотров на пост
Всего
1 766
ER
Общий
3.94%
Суточный
3%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 18 960 постов
Смотреть все посты
Пост от 07.04.2026 12:27
287
0
1
ሀሪ ማጓየር በማንቼስተር ዩናይትድ ውሉን አራዘመ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የተከላካይ ሥፍራ ተጫዋች ሀሪ ማጓየር በማንቼስተር ዩናይትድ ለተጨማሪ አንድ ዓመት ለመቆየት ውሉን አራዝሟል፡፡

ተጫዋቹ በዩናይትድ ቤት አስቀድሞ የነበረው ውል በመጪው ሰኔ ወር ላይ የሚጠናቀቅ ሲሆን፥ እስከ ፈረንጆቹ 2027 ለመቆየት ውሉን ማራዘሙ ነው የተገለጸው፡፡

በአዲሱ ውል ላይ ለተጨማሪ አንድ ዓመት የማራዘም አማራጭ ያለው አንቀጽ መካተቱም ተመላክቷል፡፡

እንግሊዛዊው ተጫዋች ሀሪ ማጓየር በፈረንጆቹ 2019 ከሌስተር ሲቲ በ80 ሚሊየን ዩሮ ማንቼስተር ዩናይትድን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

የ33 ዓመቱ ተጫዋች ለማንቼስተር ዩናይትድ 266 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን፥ ከክለቡ ጋር የኤፍ ኤ እና የካራባኦ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡
Пост от 07.04.2026 10:31
556
0
1
የፓሪስ ኦሎምፒክ ሻምፒዮኗ አትሌት ጋቢ በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር ላይ እንደምትሳተፍ አሳወቀች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፓሪስ ኦሎምፒክ 200 ሜትር ሻምፒዮኗ አትሌት ጋቢ ቶማስ በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር ላይ እንደምትሳተፍ አሳውቃለች።

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የምታስተናግደው የአንድ ቀን ዓለም አቀፍ ውድድር ሚያዚያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡

በዚህ ውድድር ላይ አሜሪካዊቷ አትሌት ጋቢ ቶማስ እንደምትሳተፍ ተረጋግጧል፡፡

ጋቢ በፈረንጆቹ 2024 በፓሪስ ኦሎምፒክ በ200 ሜትር የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ ስትሆን÷ ከቡድን አጋሮቿ ጋር ደግሞ የወርቅ ሜዳልያ ለሀገሯ ማስገኘቷ ይታወሳል።

አትሌቷ በቡዳፔስት የብር ሜዳልያ፣ በቶኪዮ ዓለም ሻምፒዮና ደግሞ የነሐስ ሜዳልያ አሸናፊ መሆኗ ይታወቃል፡፡
Пост от 05.04.2026 22:35
394
0
2
የኤፍ ኤ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ድልድል ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ድልድል ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት ማንቼስተር ሲቲ ከሳውዛምፕተን እንዲሁም ቼልሲ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ወደ ፍጻሜ ለማለፍ የሚፋለሙ ይሆናል።

ትናንት በተደረጉ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 4 ለ ዐ፣ ቼልሲ ፖርትቬልን 7 ለ ዐ እንዲሁም ሳውዛምፕተን አርሰናልን 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ማለፋቸው ይታወሳል።

ዛሬ በተደረገ የሩብ ፍጻሜ የመጨረሻ ጨዋታ ሊድስ ዩናይትድ ዌስትሃም ዩናይትድን በመለያ ምት በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።

የኤፍ ኤ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ከ20 ቀን በኋላ በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋሉ።
Изображение
Пост от 05.04.2026 18:24
1 556
0
2
ሀዋሳ ከተማ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀዋሳ ከተማ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ 2 አቻ ተለያይተዋል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የሀዋሳ ከተማን ግቦች ያሬድ ብሩክ እና ሽመልስ በቀለ አስቆጥረዋል፡፡

የወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ግቦችን ደግሞ ነፃነት ገ/መድህን እና ዳዊት ገብሩ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

አስቀድሞ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ነገሌ አርሲ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 05.04.2026 17:10
1 132
0
2
ነገሌ አርሲ አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ነገሌ አርሲ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የነገሌ አርሲን ግቦች ዳዊት ተፈራ እና ርሆቦት ሶላሎ አስቆጥረዋል፡፡

አዳማ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ዳዋ ሆቴሳ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በሌላ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1 ለ 0 እየመራ የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቅቋል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እየተካሄደ በሚገኘው ጨዋታ ሀዋሳ ከተማን መሪ ያደረግቸውን ግብ ያሬድ ብሩክ ከመረብ አሳርፏል፡፡
Пост от 05.04.2026 16:33
868
0
2
ሀገር አቀፍ የባህል ስፖርቶች ውድድርና የባህል ስፖርቶች ፌስቲቫል ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 23ኛው የባህል ስፖርቶች ውድድርና 19ኛው የባህል ስፖርቶች ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት ተጠናቅቋል፡፡

"የባህል ስፖርቶች ልማት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ለአንድ ሳምንት በሀረር ከተማ ሲካሄድ ቆይቷል፡፡

የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ሕይወት መሐመድ በፍጻሜ መርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የባህል ስፖርቶች ውድድሮችና የባህል ፌስቲቫል ወንድማማችነትና እህትማማችነት የተረጋገጠበት ነው ብለዋል፡፡

በባህል ስፖርቶች ውድድር የኦሮሚያ ክልል በ61 ነጥቦች የአጠቃላይ ስፖርት ውድድሮች አሸናፊ ሆኗል።

በ19ኛው የባህል ስፖርቶች ፌስቲቫል ደግሞ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሸናፊ ሲሆን፥ ኦሮሚያና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሁለተኛ እና ሦስተኛ በመሆን አጠናቅቀዋል።

24ኛው የባህል ስፖርቶች ውድድርና 20ኛው የባህል ፌስቲቫል በሲዳማ ክልል የሚካሄድ ይሆናል፡፡

በተሾመ ኃይሉ
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 05.04.2026 16:30
948
0
1
"በቀጣዮቹ አስር ዓመታት አሸናፊ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት እንደ ሀገር ከተያዘው የ15 ዓመት በታች የታዳጊዎች የእግር ኳስ ፕሮጀክት ውስጥ በአዲስ አበባ ከተማ ተመልምለው በመሰልጠን ላይ የሚገኙትና ተስፋ የተጣለባቸው ታዳጊዎች በአዲስ ስፖርት ፓርክ ውስጥ ልምምዳቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ" - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
👍 2
Смотреть все посты