Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.6K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 566
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 115
ER
Общий
3.86%
Суточный
3.7%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 631 поста
Смотреть все посты
Пост от 12.06.2026 09:42
1
0
0
የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይካሄዳሉ…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ያዘጋጁት የ2026 ዓለም ዋንጫ ውድድር የምድብ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

የውድድሩ አዘጋጅ ሀገራት ካናዳ እና አሜሪካ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን በዛሬው ዕለት የሚያደርጉ ይሆናል፡፡

ምድብ ሁለት ላይ የምትገኘው ካናዳ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከቦስኒያ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

ምድብ አራት ላይ የተደለደለችው አሜሪካ ደግሞ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ከፓራጓይ ትገናኛለች፡፡

ትናንት ምሽት በመክፈቻው ዕለት በተደረጉ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዎች ሌላኛዋ አዘጋጅ ሀገር ሜክሲኮ ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 0 እንዲሁም ደቡብ ኮሪያ ቼክ ሪፐብሊክን 2 ለ 1 አሸንፈዋል፡፡
Пост от 12.06.2026 00:07
48
0
0
ሜክሲኮ ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 0 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ መክፈቻ ጨዋታ ሜክሲኮ ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡

23ኛው የዓለም ዋንጫ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት በሜክሲኮ አዝቴካ ስታዲም በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ተካሂዷል፡፡

ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተካሄደው የመክፈቻ ጨዋታም ሜክሲኮ ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡

የሜክሲኮን የማሸነፊያ ግቦች ኩዊኖኔስ እና ሒምኔዝ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

ይህን ተከትሎም ኩዊኖኔስ የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያው ግብ አስቆጣሪ በመሆን ስሙን በታሪክ መዝገብ አስፍሯል፡፡

በሌላ በኩል በጨዋታው የደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ ቡድን ሁለት ተጫዋቶች በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብተዋል፡፡
Пост от 11.06.2026 23:07
1
0
0
ሜክሲኮ 1 - 0 ደቡብ አፍሪካ ፤ የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት
Пост от 11.06.2026 17:07
227
0
1
አሜሪካ እንዳይገባ የታገደው ሶማሊያዊ ዳኛ የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ እንዲመራ ተመረጠ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሶማሊያዊው ዳኛ ኦማር አርታን የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ እንዲመራ ተመርጧል፡፡

አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ባዘጋጁት በ2026 የዓለም ዋንጫ አሜሪካ እንዳይገባ የተከለከለው የ34 ዓመቱ ዳኛ የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታን እንዲመራ መመረጡ ተመላክቷል፡፡

የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ አሸናፊው ፒኤስጂ እና በዩሮፓ ሊግ አሸናፊው አስቶን ቪላ መካከል የሚደረግ ይሆናል፡፡

የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በዳኝነት እንዲመራ ተመርጦ አሜሪካ እንዳይገባ የታገደው ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታን ወደ ሀገሩ ሲመለስ ደማቅ አቀባበል እንደተደረገለት ይታወቃል፡፡
👏 2
Пост от 11.06.2026 10:07
639
0
2
በድጋሚ በዓለም ዋንጫ መክፈቻ የሚገናኙት ብሔራዊ ቡድኖች - ሜክሲኮ ከደቡብ አፍሪካ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጋራ ያዘጋጁት የ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር ዛሬ ምሽት በይፋ መካሄድ ይጀምራል፡፡

በጉጉት የሚጠበቀው የዘንድሮ የዓለም ዋንጫ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሦስት ሀገራት የሚያዘጋጁት ውድድር ነው፡፡

በ2026ቱ ዓለም ዋንጫ መርሐ ግብር 48 ሀገራት የሚሳተፉ ሲሆን ÷ በዚህም 104 ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ በአጠቃላይ 1 ሺህ 248 ተጫዋቾች በውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ይሆናል፡፡

በመድረኩ በርካታ ከዋክብት የመጨረሻቸው የዓለም ዋንጫ ውድድር ይሆናል ተብሎም ይጠበቃል፡፡

እስካሁን ድረስ 8 ሀገራት ብቻ የዓለም ዋንጫያሸነፉ ሲሆን ÷ ብራዚል፣ ጣሊያን፣ ጀርመን፣ አርጀንቲና፣ ፈረንሳይ፣ ኡራጓይ፣ እንግሊዝ እና ስፔን በመድረኩ ሻምፒዮን መሆን የቻሉ ሀገራት ናቸው፡፡

የ2026 ዓለም ዋንጫ ውድድር ዛሬ በይፋ ሲጀምር ከአዘጋጆቹ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነቸው ሜክሲኮ ምሽት 4 ሰዓት ከደቡብ አፍሪካ ትገናኛለች፡፡

ሜክሲኮ ለ18ኛ ጊዜ ተጋጣሚዋ ደቡብ አፍሪካ ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ በመድረኩ የሚሳተፉ ይሆናል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች በፈረንጆቹ 2010 ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ ውድድር የመክፈቻ ጨዋታ ላይ መገናኘታቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ያደረጉት የመክፈቻ ጨዋታ አንድ አቻ የተጠናቀቀ ሲሆን÷ ሸበላላ ለደቡብ አፍሪካ ያስቆጠራት ግብ አስደናቂ እንደነበረች አይዘነጋም፡፡

የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ሜክሲኮ ከደቡብ አፍሪካ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሚያደርጉት ጨዋታ ጅማሮውን ያደርጋል፡፡

በወንድማገኝ ጸጋዬ
Пост от 11.06.2026 09:45
708
0
1
Пост от 10.06.2026 17:06
697
0
4
አሜሪካ እንዳይገባ የታገደው ሶማሊያዊ ዳኛ ወደ ሀገሩ ሲመለስ አቀባበል ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በዳኝነት እንዲመራ ተመርጦ አሜሪካ እንዳይገባ የታገደው ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታን ወደ ሀገሩ ሲመለስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡

የ2026 ዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በዳኝነት እንዲመራ የተመረጠው ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታን በመርሐ ግብሩ ለመታደም ወደ አሜሪካ አቅንቶ ነበር፡፡

ይሁን እንጂ በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያው ሶማሊያዊ ዳኛ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ኦማር አርታን አሜሪካ ሲደርስ ያልጠበቀው ነገር ተከሰተ፡፡

በፈረንጆቹ 2025 የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ዳኛ የተባለው ኦማር ማያሚ አውሮፕላን ማረፊያ ከደረሰ በኋላ ወደ አሜሪካ መግባት እንደማይችል ተነግሮታል፡፡

እድል ያልቀናው ኦማር አርታን ወደ እናት ሀገሩ ሶማሊያ ሲመለስም የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ በቤተ መንግሥታቸው ደማቅ አቀባበል አድርገውለታል፡፡

በተጨማሪም ለዳኛ ኦማር አርታን ሌሎች የሀገሪቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የሞቃዲሾ ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል በማድረግ አጋርነታቸውን አሳይተዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ዳኛ ኦማር እስካሁን ላሳየው ስኬት እንዲሁም ለሀገሩ ላበረከተው አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡

በቀጣይ ለሚያከናውነው ሥራ ከጎኑ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል፡፡

ፊፋ የአሜሪካ ባለስልጣናትን በጉዳዩ ላይ ካነጋገረ በኋላ ዳኛው በውድድሩ ላይ በዳኝነት እንደማይሳተፍ ይፋ ማድረጉን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
👍 3
Смотреть все посты