Каталог каналов Мои подборки Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.1K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 685
Сегодня
-26
Просмотров на пост
Всего
1 828
ER
Общий
4.37%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 098 постов
Смотреть все посты
Пост от 18.04.2026 20:17
205
0
1
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 አሸንፏል።

የወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ነፃነት ገብረመድህን እና ፍሬው ሰለሞን አስቆጥረዋል።

ቀደም ብሎ ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ መቐለ 70 እንደርታ ፋሲል ከነማን 3 ለ 0 አሸንፏል።

ጨዋታው የመቐለ 70 እንደርታን ማሸነፊያ ግቦች ቦና አሊ (2) እና ሚሊዮን ወልዴ ከመረብ አሳርፈዋል።
Пост от 18.04.2026 19:02
400
0
1
በርንማውዝ ኒውካስልን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኒውካስል በበርንማውዝ 2 ለ 1 ተሸንፏል።

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የበርንማውዝን ግቦች ማርከስ ታቨርኒየር እና አድሪያን ትረፌርት ሲያስቆጥሩ÷ የኒውካስልን ብቸኛ ግብ ዊሊያም ኦሱላ ከመረብ አሳርፏል።

እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት የተደረገው የሊድስ ዩናይትድ እና ወልቭስ ጨዋታ በሊድስ 3 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

በጨዋታው የሊድስ ዩናይትድን ግቦች ኖዋህ ኦካፎር፣ ጄምስ ጀስቲን እና ካልቨርት ልዊን ከመረብ አሳርፈዋል።

ቀደም ብሎ በተደረገው የሊጉ ጨዋታ ብሬንትፎርድ እና ፉልሃም 0 ለ 0 ተለያይተዋል።

የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሄድ ቼልሲ እና ማንቼስተር ዩናይትድ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
👏 2
Пост от 18.04.2026 18:50
385
0
1
ኢትዮጵያ የዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ የሚሰጠውን ዓለም አቀፍ ውድድር እንድታዘጋጅ ተመረጠች

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ የሚሰጠውን ዓለም አቀፍ ውድድር እንድታዘጋጅ ተመረጠች።

ኢትዮጵያ በ2027 የወርቅ ደረጃ ያለውን ዓለም አቀፍ ውድድር እንድታዘጋጅ ነው የተመረጠችው።

‎የዓለም አትሌቲክስ ኢትዮጵያ ውድድሩን እንድታዘጋጅ የወሰነላት የነሐስ ደረጃ ያለውን ግራንድ ፕሪ ውድድር ለመጀመሪያውን ጊዜ በአዲስ አበባ በብቃት በማስተናገዷ እንደሆነ ተገልጿል።
‌‎
‎በዓለም አትሌቲክስ ስር የሚደረጉ የወርቅ ደረጃ ውድድሮችን በዓለም 21 ከተሞች የሚካሄዱ ሲሆን÷ አዲስ አበባ በዚህ ዝርዝር ውስጥ የገባች ሶስተኛዋ የአፍሪካ ከተማ ሆናለች።

‎የ2026 ዓለም አቀፍ የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ ውድድር ዛሬ ፍፃሜውን አግኝቷል።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 18.04.2026 17:44
556
0
2
አትሌት ፈርድናንድ ኦማናያላ እና ጋብርኤል ቶማስ በ100 ሜትር ፍፃሜ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የ100 ሜትር የፍፃሜ ውድድር በወንዶች ኬኒያዊው አትሌት ኦማንያላ በቀዳሚነት አጠናቅቋል።

የ100 ሜትር ፈጣኑ አትሌት የሆነው ኬኒያዊ ኦማንያላ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 9 ሴኮንድ 98 ማይክሮ ሴኮንድ ፈጅቶበታል።

በተመሳሳይ በሴቶች የ100 ሜትር ፍጻሜ ውድድር አሜሪካዊቷ ጋብርኤል ቶማስ 9 ሴኮንድ 77 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት በበላይነት አጠናቅቃለች።
Пост от 18.04.2026 17:15
608
0
1
በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ በወንዶች 5 ሺህ ሜትር አትሌት ገመቹ ዲዳ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ በወንዶች 5 ሺህ ሜትር አትሌት ገመቹ ዲዳ አሸንፏል።

በውድድሩ አትሌት ገመቹ ርቀቱን 13:46.09 በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ያሸነፈው።

እንዲሁም አትሌት ጀንበሩ ሲሳይ ሁለተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ፤ አትሌት ይበልጣል ጋሻሁን ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ወድድሩን አጠናቅቋል።
Изображение
Пост от 18.04.2026 17:11
453
0
1
መቐለ 70 እንደርታ ፋሲል ከነማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ ፋሲል ከነማን 3 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታን ማሸነፊያ ግቦች ቦና አሊ (2) እና ሚሊዮን ወልዴ አስቆጥረዋል።

የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሄድ አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ይገናኛል።
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 18.04.2026 16:58
530
0
2
በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የወንዶች 400 ሜትር መሰናክል አትሌት ጌታሁን ታደሰ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የወንዶች 400 ሜትር መሰናክል አትሌት ጌታሁን ታደሰ አሸንፏል።

በውድድሩ አትሌት ጌታሁን ታደሰ 51.44 በመግባት 1ኛ ሲወጣ አትሌት ተሻለ አየለ በ51.51 በመግባት 2ኛ እንዲሁም አትሌት ሳይዛና ገብረእግዚአብሔር በ52.23 ላይ በመግባት ሦስተኛ ወጥቷል።

በተመሳሳይ በ400 ሜትር ፍጻሜ ውድድር ባህሬናዊቷ አትሌት አድኮያ ፈሚ በአንደኝነት አጠናቅቃለች።

አትሌቷ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 50 ሰኮንድ 28 ማይክሮ ሰከንድ ወስዶባታል።

በውድድሩ ቻቤት ሜርሲ 2ኛ ስትወጣ፣ ጆርጂያ ፓቲነስ 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።
Изображение
Изображение
Смотреть все посты