Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.2K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 400
Сегодня
-25
Просмотров на пост
Всего
1 852
ER
Общий
4.3%
Суточный
3.2%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 232 постов
Смотреть все посты
Пост от 03.05.2026 19:31
227
0
2
ማንቼስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በማሸነፍ የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን አረጋገጠ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን 3 ለ 2 አሸንፏል፡፡

11 ሰዓት 30 ላይ በኦልድትራፎርድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የማንቼስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ማቲያስ ኩኛ፣ ቤንያሚን ሼሽኮ እና ኮቢ ማይኖ አስቆጥረዋል፡፡

ሊቨርፑልን ከሽንፈት ያልታደጉ ግቦችን ደግሞ ዶሚኒክ ሶቦዝላይ እና ኮዲ ጋክፖ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ዩናይትድ በቀጣይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ መሆኑን አረጋግጧል፡፡

አስቀድሞ በተደረገ በሌላ የሊጉ መርሐ ግብር ቦርንማውዝ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል አስቶንቪላ ምሽት 3 ሰዓት ላይ በሜዳው ቪላ ፓርክ ቶተንሃም ሆትስፐርን ያስተናግዳል፡፡
👍 3
Пост от 03.05.2026 08:44
928
0
3
በሼህ ዛይድ በጎ አድራጎት የሩጫ ውድድር አትሌት አለሽኝ ባወቀ እና ንብረት ኪዳኔ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ባደረገው ሼህ ዛይድ በጎ አድራጎት 5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር አትሌት አለሽኝ ባወቀ እና ንብረት ኪዳኔ አሸንፈዋል።

በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ኤምባሲ ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ የሩጫ ውድድር በሴቶች አትሌት አለሽኝ ባወቀ ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቃለች።

አትሌት አለሽኝ ባወቀ በመከተል አትሌት ሽቶ ጉሚ እና ሮቤ ዲዳ ተከታትለው በመግባት 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘዋል።

በወንዶች ደግሞ አትሌት ንብረት ኪዳኔ በቀዳሚነት ውድድሩን ሲያጠናቅቅ፤ አትሌት ኡርጌሳ ነጋሳ እና ግዛቸው ሙሴ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ጨርሰዋል።
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 03.05.2026 08:19
758
0
2
ሼህ ዛይድ በጎ አድራጎት የ5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ሼህ ዛይድ በጎ አድራጎት 5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር እየተካሄደ ይገኛል።

ውድድሩ የተዘጋጀው በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ኤምባሲ ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና ከታለቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ነው።

የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሼህ ዛይድን መልካም ተግባራት ለማስፋፋት በሚከናወነው በዚህ የሩጫ ውድድር ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተሳታፊ ሆነዋል።
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 02.05.2026 21:27
1 057
0
2
አርሰናል ፉልሃምን በማሸነፍ ከሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 6 አሳደገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል ፉልሃምን በማሸነፍ ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 6 ከፍ አደረገ።

ምሽት 1፡30 ላይ በኤምሬትስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አርሰናል ፉልሃምን 3 ለ 0 አሸንፏል።

በጨዋታው ቪክቶር ዮኬሬሽ 2 ግቦችን ሲያስቆጥር÷ ከግብ ርቆ የነበረው ቡካዮ ሳካ አንድ ግብ ማስቆጠር ችሏል።

በዚህም አርሰናል ሁለት ቀሪ ጨዋታ ካለውና የዋንጫ ተፎካካሪ ከሆነው ማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 6 ከፍ አድርጓል።

ቀደም ብሎ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ኒውካስል ብራይተንን 3 ለ 1፣ ብሬንትፎርድ ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 0 እንዲሁም ዎልቭስ እና ሰንደርላንድ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል።
👍 5
Пост от 02.05.2026 19:06
1 112
0
1
ኒውካስል ዩናይትድ ብራይተንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኒውካስል ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 1 አሸንፏል።

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የኒውካስልን ግቦች ዳን በርን፣ ዊሊያም ኦሱላ እና ሃርቪ ባርነስ ሲያስቆጥሩ÷ ጃክ ሂንሼልውድ የብራይተንን ግብ ከመረብ አሳርፏል።

እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በተደረጉ ጨዋታዎች ብሬንትፎርድ ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ÷ ግቦቹን ኢጎር ቲያጎ (በፍጹም ቅጣት ምት)፣ ሚኬል ዳምስጋርድ እና ማቭሮፓኖስ (በራሱ ላይ) አስቆጥረዋል።

በተጨማሪም ዎልቭስ እና ሰንደርላንድ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ሲለያዩ÷ ሳንቲያጎ ቡኤኖ የወልቭስን እንዲሁም ኖርዲ ሙኪሌ የሰንደርላንድን ግብ ከመረብ አገናኝተዋል።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ስካሄድ÷ ሊጉን በሦስት ነጥብ ልዩነት እየመራ የሚገኘው አርሰናል ምሽት 1፡30 ላይ ፉልሃምን በሜዳው ያስተናግዳል።
👏 2
👎 1
Пост от 02.05.2026 17:23
1 418
0
1
ኢፕስዊች ታውን ወደ ፕሪሚየር ሊግ አደገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢፕስዊች ታውን ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አድጓል።

በሻምፒዮንሺፕ የ2025/2026 የወድድር ዓመት የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታ ኢፕስዊች ታውን ኩዊንስ ፓርክ ሬንጀርስን 3 ለ 0 በማሸነፍ ነው ወደ ፕሪሚየር ሊግ ማለፉን ያረጋገጠው።

የኢፕስዊች ታውን ግቦችን ጆርጅ ሂርስት፣ ጄደን ፊሎጅን እና ካሴይ ማክአቴር አስቆጥረዋል።

ውጤቱን ተከሎም ኢፕስዊች ታውን በሻምፒዮን ሺፑ የደረጃ ሰንጠረዥ ላይ የሁለተኛ መሆን ችሏል።

በሻምፒዮን ሺፕ የመጀመሪያ ደረጃን የያዘው ኮንቨንትሪ ሲቲ ቀድሞ ወደ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን ያረጋገጠ ክለብ መሆኑ ይታወቃል።
👍 2
👎 2
Пост от 01.05.2026 21:39
1 740
0
3
"ሊጉን ለማሸነፍ ለመጨረሻዎቹ አራት ጨዋታዎች ዝግጁ ነን" - ሚኬል አርቴታ

"ከኤቨርተን ጋር የምናደርገው ጨዋታ ለእኛ የፍጻሜ ጨዋታ ነው" - ፔፕ ጋርዲዮላ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ ምሽት በሚጀምረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ35ኛ ሳምንት መርሐ ግብር በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝነት ያላቸው ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ከሚቀረው ማንቼስተር ሲቲ በሦስት ነጥብ በልጦ ሊጉን እየመራ የሚገኘው አርሰናል ነገ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢምሬትስ ፉልሃምን ያስተናግዳል፡፡

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ከነገው ጨዋታ በፊት በሰጡት አስተያየት፥ የሊጉን ዋንጫ ለማሸነፍ ስንቅ የሚሆን በቂ ተነሳሽነት አለን ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

የነገውን ጨዋታ ጨምሮ አራቱም ቀሪ ጨዋታዎቻችን ዋንጫውን ለማሸነፍ ወሳኝ በመሆናቸው ለእያንዳንዱ ፈተና ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡

አርሰናል በነገው ጨዋታ ፉልሃምን የሚያሸንፍ ከሆነ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ስድስት ማስፋት ይችላል፡፡

ውሃ ሰማያዊዎቹ በመጪው ሰኞ ምሽት በሂል ዲኪንሰን ስታዲየም ኤቨርተንን የሚገጥሙ ሲሆን፥ ፔፕ ጨዋታው ለእኛ የፍጻሜ ያህል ነው ብለዋል፡፡

አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በሰጡት አስተያየት፥ ከአርሰናል ጋር የስድስት ነጥብ ልዩነት ቢፈጠርም የተለየ ጫና እንደማይፈጥርባቸው ተናግረዋል፡፡
👍 7
Смотреть все посты