Каталог каналов Мои подборки Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.1K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 589
Сегодня
-8
Просмотров на пост
Всего
1 673
ER
Общий
4.11%
Суточный
3.2%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 144 постов
Смотреть все посты
Пост от 23.04.2026 00:07
658
0
3
ማንቼስተር ሲቲ የሊጉን መሪነት ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼሰተር ሲቲ በርንሌይን 1 ለ 0 አሸንፏል።

የማንቼስተር ሲቲን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ኤርሊንግ ብራውት ሀላንድ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል።

ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ አርሰናልን በእርስበርስ ግንኙነት በመብለጥ የሊጉን መሪነት ተረክቧል።

በርንሌይ በበኩሉ ቀሪ አራት ጨዋታ እያለው ከሊጉ መውረዱን አረጋግጧል።
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 22.04.2026 19:41
1 110
0
4
ቼልሲ አሰልጣኝ ሊያም ሮሴኒየርን አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ አሰልጣኝ ሊያም ሮሴኒየርን ከኃላፊነታቸው አሰናብቷል፡፡

ክለቡ አሰልጣኙን ያሰናበተው ከፈረንጆቹ 1912 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ምንም ግብ ማስቆጠር ሳይችል አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች መሸነፉን ተከትሎ ነው፡፡

የፈረንሳዩ ክለብ ስትራስቡርግን በመልቀቅ በጥር ወር አምስት ዓመት ከግመሽ ኮንትራት በመፈረም ቼልሲን የተቀላቀሉት ሮሴኒየር÷ በሁሉም ውድድሮች 23 ጊዜ ክለቡን መርተው 11 ጊዜ ብቻ አሸንፈዋል፡፡

ትናንት ምሽት በብራይተን 3 ለ 0 መሸነፋቸው ለስንብታቸው ቀጥተኛ ምክንያት ሆኗል፡፡

በአቤል ነዋይ
Изображение
👏 1
Пост от 22.04.2026 08:55
1 614
0
1
የቼልሲ የቀድሞ ኮከብ ዴቪድ ሉዊዝ…

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ጋር ስኬታማ ዓመታትን ማሳለፍ የቻለ ኮከብ ነው ብራዚላዊው ተጫዋች ዴቪድ ሉዊዝ፡፡ የብራዚል ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ተጫዋች ዴቪድ ሉዊዝ ፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ሕይወቱን የጀመረው በሀገሩ ክለብ ቪቶሪያ ነው፡፡ የቼልሲ የቀድሞ ኮከብ በዓለም እግር ኳስ ከታዩ ምርጥ የመሐል ተከላካዮች መካከል አንዱ ሲሆን ከአስደናቂ…

https://www.fanamc.com/archives/313419
Пост от 22.04.2026 00:06
1 699
0
1
ቼልሲ በብራይተን ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ብራይተን ቼልሲን 3 ለ 0 አሸንፏል።

ምሸት 4 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የብራይተንን የማሸነፊያ ግቦች ካዲዮግሉ፣ ሂንሼልውድ እና ዌልቤክ አስቆጥረዋል።

ቼልሲ በሊጉ አምስተኛ ተከታታይ ሽንፈት አስተናግዷል።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 21.04.2026 21:21
1 195
0
3
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቅቋል፡፡

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላለፉት ሁለት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ነው የተጠናቀቀው፡፡

በዚህም ፌዴሬሽኑ ላለፋት ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ተደርጎበት በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል።

በተሻሻለው የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ የስልጣን ጊዜ ከሁለት ዙር እንደማይሻገር ነው የተገለጸው፡፡

ስራ አስፈጻሚ አባላት በአንድ ምርጫ ለአራት ዓመታት የሚመሩ ሲሆን ከአባላቱ መካከል ቢያንስ አንዱ የቀድሞ አትሌት፣ አሰልጣኝ ወይም የስፖርት ሳይንስ ምሁር መሆን እንዳለበት ተመላክቷል፡፡

አህጉራዊ የአትሌቲክስ ተቋማት በጠቅላላ ጉባኤው ላይ ተገኝተው ድምፅ የመስጠት መብት በደንቡ የተሰጣቸው ሲሆን ትውልደ ኢትዮጵያ በስራ አስፈጻሚነት መወዳደር እንደማይችሉ አስቀምጧል፡፡

በተጨማሪም ተቋማዊ ሪፎርም፣ የሰው ሃይል መዋቅራዊ ጥናት፣ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ እና የተሻሻለ የግዥና ፋይናንስ መመሪያዎች ቀርበው መጽደቃቸው ተገልጿል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ መኪዩ መሐመድ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ የተጀመረው ተቋማዊ ለውጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ፌዴሬሽኖች እና ማህበራት ይቀጥላል ብለዋል።

እንደሀገር የተጀመረው የስፖርቱን ስብራት የመጠገን ሂደት የሁሉንም የዘርፉ ተዋንያን ትብብር እንደሚፈልግ ገልጸው መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡

በወርቅነህ ጋሻሁን
🙏 1
Пост от 21.04.2026 17:16
1 284
0
1
ቅዱስ ጊዮርጊስ አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ አዳማ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ፍፁም ጥላሁን በሁለተኛው አጋማሽ አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ35 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ አዳማ ከተማ በበኩሉ በ33 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

አዳማ ከተማ በሊጉ ተከታታይ ስድስተኛ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 21.04.2026 09:57
1 640
0
2
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና አዳማ ከተማ ይጫወታሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና አዳማ ከተማ ይገናኛሉ።

ጨዋታው ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል።

ትናንት በተደረጉ የሊጉ የሳምንቱ መርሐ ግብሮች ሸገር ከተማ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 0፣ ወላይታ ድቻ ምድረ ገነት ሽረን 1 ለ 0 ሲያሸንፉ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
Смотреть все посты