Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.7K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 504
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
1 932
ER
Общий
4.66%
Суточный
4.1%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 707 постов
Смотреть все посты
Пост от 19.06.2026 20:03
163
0
1
የዓለም ዋንጫው የምድብ 2ኛ ጨዋታዎች…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ 2ኛ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

በምድብ አራት የምትገኘው አዘጋጇ ሀገር አሜሪካ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከአውስትራሊያ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ አሜሪካ ፓራጓይን እንዲሁም አውስትራሊያ ቱርክዬን በማሸነፍ በግብ ክፍያ ተበላልጠው በምድቡ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡

በዚሁ ምድብ በመጀመሪያ ጨዋታዎቻቸው ሽንፈት ያስተናገዱት ቱርክዬ እና ፓራጓይ የመጀመሪያ ነጥባቸውን ለማሳካት ነገ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በሌሎች የምድብ 2ኛ ጨዋታዎች ምድብ ሦስትን እየመራች የምትገኘው ስኮትላንድ ከሞሮኮ ዛሬ ሌሊት 7 ሰዓት ሲገናኙ፥ በዚሁ ምድብ ብራዚል የመጀመሪያ ድሏን ለማሳካት ሌሊት 9 ሰዓት ከ30 ሄይቲን ትገጥማለች፡፡
Пост от 19.06.2026 13:15
1
0
0
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የውድድር ዘመን የጨዋታ መርሐ ግብር ይፋ ተደርጓል፡፡

ሻምፒዮኑ አርሰናል በሜዳው ኢምሬትስ ከአዲስ አዳጊው ኮቬንትሪ ሲቲ ጋር የሊጉን የመክፈቻ ጨዋታውን ያደርጋል።

በአዲሱ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ የሚመራው ማንችስተር ሲቲ በሜዳው ከ በርንማውዝ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን የሚያደርግ ይሆናል፡፡

በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የሚመራው ማንቼስተር ዩናይትድ በበኩሉ ወደ ሊጉ ካደገው ሃል ሲቲ ጋር በመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታው ይገናኛል፡፡

አንዶኒ ኢራኦላን በኋላፊነት የሾመው ሊቨርፑል ከኒውካስል ዩናይትድ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

ከአውሮፓ ውድድሮች ውጪ ሆኖ የውድድር ዓመቱን ያጠናቀቀው ቼልሲ በመጀመሪያ ሳምንት ከፉልሀም ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

ሌላኛው ወደ ሊጉ ያደገው ኢፕስዊች ታውን የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን ከሰንደርላንድ ጋር የሚያደርግ ይሆናል፡፡

የወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል በ3ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በሜዳው ቼልሲን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡

በሊጉ ከሚጠበቁ ጨዋታዎች መካከል አንዱ የሆነው የአርሰናል እና ማንቼስተር ዩናይትድ ጨዋታ በ16ኛ ሳምንት በኢምሬትስ ስታዲየም ይካሄዳል፡፡

ተጠባቂው የማንቼስተር ደርቢ ጨዋታ በ4ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በኦልድትራፎርድ ይደርጋል፡፡

የላንክሻር ደርቢ ጨዋታ ደግሞ በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም በ11ኛ ሳምንት የሚካሄድ ይሆናል፡፡

በመርሐ ግብሩ መሰረት አዲሱ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀመር ይሆናል፡፡
Пост от 19.06.2026 09:42
207
0
1
ሮናልዶ የቡድኑ ድክመት

ከደቂቃዎች በኋላ በኤክስትራ ታይም ስፖርት ቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን

#ስፖርት_ፖድካስት
#ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #PoodkaastiiFaanaa #fanadigitalmedia فانا_عربي_بودكاست
Пост от 18.06.2026 21:04
1
0
0
ደቡብ አፍሪካና ቼክ ሪፐብሊክ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ አንድ 2ኛ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ እና ቼክ ሪፐብሊክ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

የቼክ ሪፐብሊክን ግብ ሚሼል ሳዲሌክ ሲያስቆጥር÷የደቡብ አፍሪካን የአቻነት ግብ ደግሞ ሞክዌና ከመረብ አሳርፏል፡፡

የቼክ ሪፐብሊክ ግብ በ2026 ዓለም ዋንጫ እስካሁን ከተመዘገቡት ግቦች ውስጥ ፈጣኗ መሆን ችላለች፡፡
Пост от 18.06.2026 10:30
1
0
0
በዓለም ዋንጫ የጋሪ ሊንከርን ክብረ ወሰን የተጋራው ሃሪ ኬን…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሃሪ ኬን በዓለም ዋንጫ ውድድር በርካታ ግቦችን በማስቆጠር የሀገሩን ልጅ ጋሪ ሊንከር ክብረ ወሰን ተጋርቷል፡፡ በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ትናንት ምሽት እንግሊዝ ክሮሺን 4 ለ 2 ማሸነፏ ይታወቃል፡፡ እንግሊዛዊው የ32 ዓመቱ…

https://www.fanamc.com/archives/316987
Пост от 17.06.2026 12:12
224
0
2
በዓለም ዋንጫ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የተጋራው ሊዮ ሜሲ..

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በስድስት የዓለም ዋንጫ ውድድሮች በመጫወት ክብረወሰን ያስመዘገበው ሊዮኔል ሜሲ በ16 ግቦች የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን ክብረ ወሰን ተጋርቷል፡፡

በፈረንጆቹ 2006 በጀርመን ዓለም ዋንጫ በ18 አመቱ ሀገሩን ወክሎ መጫወት የጀመረው የሮዛሪዮው ተወላጅ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ የዘንድሮውን ጨምሮ በስድስት የዓለም ዋንጫዎች ተሳትፏል፡፡

ትናንት ምሽት አርጀንቲና አልጀሪያን 3 ለ 0 ባሸነፈችበት የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ ሦስቱንም ግቦች በማስቆጠር ሀትሪክ የሰራው ሜሲ የዓለም መነጋገሪያ ሆኗል፡፡

ለሀገሩ አርጀንቲና እስካሁን 200 ጨዋታዎችን ያደረገው የ38 አመቱ ኮከብ በጀርመናዊው ሚሮስላቭ ክሎስ ተይዞ የነበረውን የምንጊዜም የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰን ተጋርቷል፡፡

የ2022ቱ የኳታር ዓለም ዋንጫ አሸናፊው ሜሲ አሁንም የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋች መሆኑን ከማስመስከር ባሻገር ሀገሩ በዘንድሮውም ዓለም ዋንጫ ለአሸናፊነት እንድትታጭ አስችሏል፡፡

የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ጅማሮ በሀትሪክ ያሳመረው ሊዮ ሜሲ በቀጣይ ጨዋታዎች ክብረ ወሰኑን የግሉ የማድረግ ሰፊ እድል አለው፡፡

የ26 አመቱ ፈረንሳዊ ኪሊያን ምባፔ ትናንት ምሽት ሀገሩ ሴኔጋልን ባሸነፈችበት ጨዋታ ያስቆጠራቸውን ሁለት ግቦች ጨምሮ 14 ግቦችን ከመረብ ያሳረፈ ሲሆን፥ ክብረ ወሰኑን የግሉ ለማድረግ ከሜሲ ጋር ተፋጧል፡፡

ሊዮኔል ሜሲ በተጨማሪም በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ ሦስት ግቦችን ያሰቆጠረ በእድሜ አንጋፋው ተጫዋች በመሆን ተጨማሪ ክብረ ወሰን የግሉ አድርጓል፡፡

በአቤል ነዋይ
Пост от 17.06.2026 11:41
237
0
1
ፖርቹጋል ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ..

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሀገር ፖርቹጋል የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ዛሬ ምሽት ታደርጋለች፡፡ ፖርቹጋል ምሽት 2 ሰዓት ላይ ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ጋር በሂውስተን ስታዲየም በምታደርገው ጨዋታ የማሸነፍ ቅድመ ግምት ተሰጥቷታል፡፡ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ተሳትፎውን የሚያደርገው ፖርቹጋላዊ ኮከብ በጨዋታው ልዩነት ፈጣሪ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በአውሮፓ የተለያዩ ክለቦች ቁልፍ…

https://www.fanamc.com/archives/316942
Смотреть все посты