Каталог каналов Каналы в закладках Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.0K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 855
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
1 755
ER
Общий
4.12%
Суточный
3%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 18 981 поста
Смотреть все посты
Пост от 09.04.2026 20:08
547
0
2
ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ መሳይ ሰለሞን ባለቀ ሰዓት ባስቆጠረው ግብ ወላይታ ድቻ ማሸነፍ ችሏል።

ቀደም ብሎ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 እንዲሁም ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 ሲያሸንፉ÷ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
Пост от 09.04.2026 17:06
1
0
0
ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ምኞት ደበበ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከወላይታ ድቻ ይገናኛል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

የነገሌ አርሲን ግብ ኪቲካ ጅማ ሲያስቆጥር የኢትዮጵያ መድንን የአቻነት ግብ ብሩክ በላቸው ከመረብ አሳርፏል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

የሀድያ ሆሳዕናን የመሪነት ግብ ሄኖክ አርፊጮ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥሯል፡፡
Пост от 09.04.2026 17:06
806
0
1
ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ምኞት ደበበ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከወላይታ ድቻ ይገናኛል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

የነገሌ አርሲን ግብ ኪቲካ ጅማ ሲያስቆጥር የኢትዮጵያ መድንን የአቻነት ግብ ብሩክ በላቸው ከመረብ አሳርፏል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

የሀድያ ሆሳዕናን የመሪነት ግብ ሄኖክ አርፊጮ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥሯል፡፡
Пост от 09.04.2026 08:50
1 244
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ ነገሌ አርሲ ከኢትዮጵያ መድን እንዲሁም ቀን 10 ሰዓት ላይ አርባ ምንጭ ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ይገናኛሉ፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከሀዋሳ ከተማ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከወላይታ ድቻ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Изображение
👍 1
Пост от 08.04.2026 17:18
1 556
0
2
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መቐለ 70 እንደርታን 3 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደርገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ሁዘይፋ ሻፊ እና ናትናኤል (2) ከመረብ አሳርፈዋል።

እንዲሁም ቀደም ብሎ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የተደረገው የኢትዮጵያ ቡና እና ሸገር ከተማ ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።

በጨዋታው የኢትዮጵያ ቡናን ግብ አቡበከር አዳሙ ሲያስቆጥር÷ የሸገር ከተማን ደግሞ አሚር አብዶ ከመረብ አሳርፏል።

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ የተጀመረው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ በቅዱስ ጊዮርጊስ 1 ለ 0 መሪነት የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቅቋል።

እንዲሁም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምድረ ገነት ሽረ ከድሬዳዋ ከተማ ጨዋታውን ያደርጋል።
👍 3
Пост от 08.04.2026 00:11
1 487
0
2
ባየርን ሙኒክ ሪያል ማድሪድን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ባየርን ሙኒክ ሪያል ማድሪድን 2 ለ 1 አሸንፏል።

የባየርን ሙኒክን የማሸነፊያ ግቦች ሉዊስ ዲያዝ እና ሀሪኬን አስቆጥረዋል።

ሪያል ማድሪድን ከሸንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ኪሊያን ምባፔ ከመረብ አሳርፏል።

በሌላ ጨዋታ አርሰናል ስፖርቲንግ ሊዝበንን 1 ለ 0 አሸንፏል።

የአርሰናልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ካይ ሀቨርትዝ በሁለተኛው አጋማሽ አስቆጥሯል።
👏 5
👍 1
Пост от 07.04.2026 21:18
1 766
0
1
የሪያል ማድሪድ እና ባየርን ሙኒክ አሰላለፍ ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ተጠባቂ ጨዋታዎች አሰላለፍ ይፋ ሆኗል፡፡

በዚህም ሪያል ማድሪድ አንድሬ ሉኒን፣ ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ፣ አንቶኒዮ ሩዲገር፣ ዲን ሁጅሰን፣ አልቫሮ ካሬራስ፣ ፌዴሪኮ ቫልቬርዴ፣ ቲያጎ፣ ቹሀሚኒ፣ አርዳ ጉለር፣ ኪሊያን ምባፔ እና ቪኒሸስ ጁኒየርን በመጀመሪያው አሰላለፍ ውስጥ አካትቷል፡፡

ባየርን ሙኒክ በኩል ማኑኤል ኑየር፣ ኡፓሜካኖ፣ ታህ፣ ኪሚቺ፣ ናብሪ፣ ሀሪኬን፣ ዲያዝ፣ ኦሊሴ፣ ላይመር፣ ስታኒሲች እና ፓቭሎቪች በቋሚነት የሚጀምሩ ይሆናል፡፡

በሌላኛው የምሽቱ ጨዋታ ደግሞ ዴቪድ ራያ፣ ቤንዋይት፣ ሳሊባ፣ ጋብሬል ማጋሌሽ፣ ካላፊዮሪ፣ ዙቢሜንዲ፣ ራይስ፣ ኦዴጋርድ፣ ማዱኬ፣ ትሮሳርድ እና ዮኬሬሽ ስፖርቲንግን በሚገጥመው የአርሰናል የመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ ተካትተዋል፡፡

ተጋጣሚው ስፖርቲንግ ሊዝበን በበኩሉ ሩሂ ሲልቫ፣ ኢናሲዮ፣ ዳይሞንዴ፣ ፍሬስኔዳ፣ አራሆ፣ ሲሞስ፣ ሞሪታ፣ ትሪንካሆ፣ ካታሞ፣ ፖቴ እና ሰዋሬዝን በመጀመሪያው አሰላለፍ ይዞ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ሁለቱም የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች በተመሳሳይ ምሽት 4 ሰዓት ላይ መደረግ ይጀምራሉ፡፡
👍 3
Смотреть все посты