Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
16.6K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
39 610
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
1 225
ER
Общий
2.95%
Суточный
3.7%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 16633 постов
Смотреть все посты
Пост от 13.01.2026 12:13
991
0
0
በሲዳማ ክልል 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ሴቶች የፋይዳ መታወቂያ እንዲይዙ ለማስቻል … አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሲዳማ ክልል ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በተያዘው በጀት ዓመት በክልሉ 1 ነጥብ 4 ሚሊየን የሚሆኑ ሴቶች የፋይዳ መታወቂያ እንዲይዙ ለማስቻል እየተሰራ ነው አለ። ‘የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ለሁሉም ሴቶች እና ህፃናት’ በሚል መሪ ሀሳብ ቢሮው ያዘጋጀው የሩጫ ውድድር በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። የቢሮው ኃላፊ እመቤት ኢሳያስ እንዳሉት፤ የክልሉ ነዋሪዎች የፋይዳ መታወቂያ እንዲይዙ በትኩረት እየተሰራ ነው። ፋይዳ መታወቂያ ወሳኝ በመሆኑ በማህበረሰቡ ውስጥ ትልቅ ሚና ያላቸው ሴቶች የፋይዳ መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ሴቶች የፋይዳ መታወቂያ እንዲይዙ የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አሸናፊ ኤሊያስ በበኩላቸው፤ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሰራን ባለንበት ወቅት ፋይዳ መታወቂያ ትክክለኛ መረጃ ለመያዝ ጠቃሚ ነው ብለዋል። በክልሉ ዘንድሮ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች ፋይዳ መታወቂያ እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ እስካሁን ከ1 ሚሊየን በላይ ነዋሪዎች የፋይዳ መታወቂያ ባለቤት ሆነዋል ነው ያሉት። በደብሪቱ በዛብህ
😢 1
Пост от 13.01.2026 10:08
1 136
0
0
ኒውካስል ዩናይትድ ከማንቼስተር ሲቲ… አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ካራባኦ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ዛሬ ምሽት ኒውካስል ዩናይትድ ከማንቼስተር ሲቲ ይጫወታሉ፡፡ የአምናው የውድድሩ ሻምፒዮን ኒውካስል ዩናይትድ በሩብ ፍጻሜው ፉልሃምን እንዲሁም ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን አሸንፈው ነው ግማሽ ፍጻሜውን የተቀላቀሉት፡፡ ሁለቱ ቡድኖች በሁሉም ውድድሮች ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ ሦስቱን ያሸነፈ ሲሆን፥ በአንዱ አቻ ተለያይቶ በአንዱ ተሸንፏል፡፡ ሲቲ በካራባኦ ዋንጫ ኒውካስል ዩናይትድን በገጠመበት ያለፉት ሁለት ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል፡፡ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ምሽት 5 ሰዓት ላይ በሴንት ጀምስ ፓርክ የሚደረግ ሲሆን፥ የመልሱ ጨዋታ ከሦስት ሳምንት በኋላ በኢትሃድ ይደረጋል፡፡
Пост от 13.01.2026 09:55
983
0
1
በዓለም የሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ አቀባበል ተደረገ አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ ፍሎሪዳ በተካሄደው 46ኛው የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ዛሬ ጠዋት በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በተደረገው የአቀባበል ስነ ስርዓት ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አትሌት ስለሺ ስህን፣ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) እና ሌሎችም አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ ኢትዮጵያ በመድረኩ በሶስት የወርቅ፣ ሁለት የብር እና ሁለት የነሃስ በአጠቃላይ 7 ሜዳሊያዎችን ያገኘች ሲሆን፥ ኬንያን በመከተል ከዓለም 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። በትዝታ ወንድሙ
Пост от 12.01.2026 21:02
1 477
0
1
ዣቢ አሎንሶ ከሪያል ማድሪድ ጋር ተለያየ አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ኃያል ክለብ ሪያል ማድሪድ አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ ከክለቡ ጋር መለያየቱን ይፋ አድርጓል። ዣቪ አሎንሶ ከአሰልጣኝነት የለቀቀው ሪያል ማድሪድ በስፔን ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ በባርሴሎና 3 ለ 2 በሆነ ውጤት መሸነፉን ተከትሎ ነው፡፡ የ44 ዓመቱን ዣቢ አሎንሶ በመተካት የቀድሞው የሊቨርፑል ተከላካይ አልቫሮ አርቢዮላ ቡድኑን እንደሚረከብ ዘአትሌቲክ ዘግቧል፡፡
Пост от 12.01.2026 12:42
1 984
0
0
የማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ለመሆን የተቃረበው ማይክል ካሪክ… አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞው የማንቼስተር ዩናይትድ ተጫዋች ማይክል ካሪክ እስከ ወድድር ዓመቱ መጨረሻ ክለቡን በጊዜያዊ አሰልጣኝነት ለመረከብ መቃረቡ እየተነገረ ይገኛል፡፡ ማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪምን ካሰናበተ በኋላ በቀድሞ ተጫዋቹ ዳረን ፍሌቸር እየተመራ ሁለት ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን፥ በትናንትናው ዕለት በብራይተን ተሸንፎ ከኤፍ ኤ ዋንጫ ተሰናብቷል፡፡ ከሩበን አሞሪም ስንብት በኋላ በርካታ አሰልጣኞች በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት ኃላፊነቱን እንደሚረከቡ ስማቸው እየተነሳ ይገኛል፡፡ በተለይም የቀድሞ የክለቡ ተጫዋችና አሰልጣኝ ኦሊጉነር ሶልሻየር እና ማይክል ካሪክ ከክለቡ ኃላፊዎች ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን በርካታ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡ ክለቡ ቀጣዩን አሰልጣኝ በቀጣይ ሁለት ቀናት ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግ የተገለጸ ሲሆን፥ የ44 ዓመቱ ማይክል ካሪክ የተሻለ እድል እንዳለው ቢቢሲ እና ዘ አትሌቲክ አስነብበዋል፡፡ ማይክል ካሪክ የሻምፒየንሺፑን ክለብ ሚድልስቦሮ ለ2 ዓመት ከግማሽ ማሰልጠኑ የሚታወስ ሲሆን ባሳለፍነው ክረምት ከክለቡ ጋር መለያየቱ አይዘነጋም፡፡
👎 4
Пост от 12.01.2026 00:06
1 701
0
2
ባርሴሎና የስፔን ሱፐር ካፕ ሻምፒዮን ሆነ አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኤልክላሲኮ ደርቢ ባርሴሎና ሪያል ማድሪድን በማሸነፍ የስፔን ሱፐር ካፕ ሻምፒዮን ሆኗል። በሳዑዲ አረቢያ በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ባርሴሎና ሪያል ማድሪድን 3 ለ 2 አሸንፏል። የካታሉንን ክለብ ግቦች ራፊንሃ (2) እና ሌዋንዶውስኪ ሲያስቆጥሩ፥ ማድሪድን ከሽንፈት ያልታደጉትን ግቦች ቪኒሺየስ ጁኒየር እና ጎንዛሎ ጋርሺያ ከመረብ አሳርፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ባርሴሎና የዋንጫው ባለቤት መሆን ችሏል።
👍 2
Пост от 11.01.2026 10:50
1 430
0
3
የ’ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ’ የሩጫ ውድድር በደብረብርሃን ተካሄደ አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የ’ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018’ የሩጫ ውድድር በደብረብርሃን ከተማ ተካሂዷል። ውድድሩ ከዚህ በፊት በአራት የተለያዩ ከተሞች ይደረግ የነበረ ሲሆን በዚህ ዓመት ደብረብርሃን እና ሀረርን በማካተት በስድስት ከተሞች ይደረጋል። በስፖርት ቱሪዝምን ማስተዋወቅ የውድድሩ አንድ አካል ሲሆን ተሳታፊዎች በአንኮበር ቤተ መንግሥት ጉብኝት አድርገዋል። በውድድሩ በወንዶች አትሌት ‎ስጦታው ሰማኸኝ፣ ቦጋለ ሰለሞን እና አየለ ከበደ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ አጠናቅቀዋል። በሴቶች ደግሞ አትሌት አማረች ገብሬ፣ ደመቅ ጥላሁን እና የዘብነሽ ወንዴ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ውድድሩን ጨርሰዋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 5ኛ ደረጃን ይዘው ላጠናቀቁ አትሌቶች የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በእንዳልካቸው ወዳጄ
👍 2
🙏 1
Смотреть все посты