Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 531
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 278
ER
Общий
6%
Суточный
4.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 931 поста
Смотреть все посты
Пост от 15.07.2026 00:04
53
0
1
ስፔን ፈረንሳይን በማሸነፍ ወደ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን ፈረንሳይን በማሸነፍ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።

የስፔንን ግቦች ኦያርዛባል (በፍጹም ቅጣት ምት) እና ፔድሮ ፖሮ አስቆጥረዋል።

ስፔን በፍጻሜው ከእንግሊዝ እና አርጀንቲና አሸናፊ ጋር ትገናኛለች፡፡
Пост от 14.07.2026 20:52
516
0
2
ማንቼስተር ዩናይትድ ዩሪ ቴሊማንስን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ቤልጂየማዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ዩሪ ቴሊማንስን ከአስቶን ቪላ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ ለዝውውሩ 35 ሚሊየን ፓውንድ የውል ማፍረሻ በመክፈል ተጫዋቹን ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል፡፡

የ29 ዓመቱ አማካይ በኦልድትራፎርድ እስከ ፈረንጆቹ 2031 ድረስ የሚያቆውን ውል ፈርሟል፡፡

ቴሊማንስ በ2023 ከሌስተር ሲቲ አስቶን ቪላን የተቀላቀለ ሲሆን፥ በተጠናቀቀው የ2025/26 የውድድር ዓመት ከቪላ ጋር የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል፡፡

ተጫዋቹ በዚህ ክረምት ለማንቼስተር ዩናይትድ ፊርማውን ያኖረ ሦስተኛው ተጫዋች ሲሆን፥ ዩናይትድ ቀደም ሲል ሌላኛውን አማካይ አንድሬይ ሳንቶስ ከቼልሲ እንዲሁም ዌልሳዊውን ግብ ጠባቂ ካርል ዳርሎን በነጻ ዝውውር ማስፈረሙ ይታወቃል፡፡
Пост от 14.07.2026 20:47
1
0
0
ስፔን ከፈረንሳይ - የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ ቋሚ አሰላለፍ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የዓለም ዋንጫ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ፈረንሳይ ከስፔን የሚያደርጉት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች በምሽቱ ጨዋታ የሚጠቀሙትን ቋሚ አሰላለፍ ይፋ አድርገዋል፡፡

በዚህም መሰረት ስፔን ኡናይ ሲሞን፣ ፔድሮ ፖሮ፣ ኩባርሲ፣ ላፖርት፣ ኩኩሬያ፣ ሮድሪ፣ ፋቢያን ሩዪዝ፣ ኦልሞ፣ ላሚን ያማል፣ አሌክስ ባይና እና ኦያርዛብልን የመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ አካትታለች፡፡

በፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በኩል ኪሊያን ምባፔ፣ ኦሊሴ፣ ዴምቤሌ፣ ባርኮላ፣ ራቢዮት፣ ቹሃሚኒ፣ ዲኜ፣ ኡፓሚካኖ፣ ሳሊባ፣ ኩንዴ እና ማይግናን በቋሚ አሰላለፍ ወደ ሜዳ የሚገቡ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሸናፊ በፍጻሜው ከአርጀንቲና እና እንግሊዝ አሸናፊ ጋር ለዋንጫው ይፋለማል፡፡
Пост от 14.07.2026 16:59
383
0
1
ቤሺክታሽ ሊያንድሮ ትሮሳርድን ከአርሰናል አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቱርኩ ክለብ ቤሺክታሽ ቤልጂየማዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ሊያንድሮ ትሮሳርድ ከአርሰናል አስፈርሟል፡፡

ቤሺክታሽ ለትሮሳርድ ዝውውር 20 ሚሊየን ዩሮ ለሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል መክፈሉ ተመላክቷል፡፡

የ31 ዓመቱ ተጫዋች በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ከአርሰናል ጋር የሊጉን ዋንጫ ማሳካቱ ይታወሳል፡፡

ተጫዋቹ ለአርሰናል በሁሉም ውድድሮች ባደረጋቸው 174 ጨዋታዎች 70 የግብ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡

ሊያንድሮ ትሮሳርድ በ2023 ከብራይተን አርሰናልን በ27 ሚሊየን ፓውንድ መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡
Пост от 14.07.2026 15:08
5
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ ዌልሳዊውን ግብ ጠባቂ ካርል ዳርሎውን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ዌልሳዊውን ግብ ጠባቂ ካርል ዳርሎውን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

የተጠናቀቀውን የውድድር ዓመት በሊድስ ዩናይትድ ቤት ያሳለፈውን ግብ ጠባቂ ማንቼስተር ዩናይትድ በነጻ ዝውውር የግሉ አድርጎታል።

የ35 ዓመቱ ግብ ጠባቂ በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2028 ድረስ የሚቆይ ይሆናል።

ከአልታይ ባይንደር ጋር እንደሚለያይ የሚጠበቀው ማንቼስተር ዩናይትድ ካርል ዳርሎውን ለሰን ላሜንስ ተጠባባቂ ለማድረግ ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል።

ካርል ዳርሎውን በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን ለሊድስ ዩናይትድ በሊጉ 22 ጨዋታዎችን አድርጓል።
Пост от 14.07.2026 09:13
108
0
2
ፈረንሳይ ከስፔን - የፍጻሜ ተፋላሚ ለመሆን…

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት መደረግ ይጀምራሉ፡፡

በዚህም መሰረት ምሽት 4 ሰዓት ላይ ፈረንሳይ ከስፔን የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡ለዋንጫው ቅድመ ግምት ካገኙት ከሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መካከል የአንዳቸው ጉዞ ዛሬ ምሽት የሚያበቃ ይሆናል፡፡

ፈረንሳይ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ እስካሁን ድረስ ከሴኔጋል፣ ኢራቅ፣ ኖርዌይ፣ ስዊድን፣ ፓራጓይ እና ሞሮኮ ጋር ተገናኝታ ሁሉንም ጨዋታዎች አሸንፋለች፡፡

በአሰልጣኝ ዲዴ ዴሻምፕ የምትመራው ፈረንሳይ እስከ ሩብ ፍጻሜ ድረስ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች 16 ግቦችን ተጋጣሚዎቿ ላይ አስቆጥራ የተቆጠረባት ሁለት ግብ ብቻ ነው፡፡

በፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በኩል ኪሊያን ምባፔ፣ የባሎንዶር አሸናፊው ኦስማን ዴምቤሌ እና ኦሊሴ አስደናቂ ጊዜ እያሳለፉ ይገኛሉ፡፡
https://web.facebook.com/share/p/1F85ku3eRw/
Пост от 13.07.2026 16:19
1 205
0
4
ማንቼስተር ዩናይትድ አንድሬይ ሳንቶስን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች አንድሬይ ሳንቶስን ከቼልሲ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ 48 ሚሊየን ፓውንድ እና እየታየ የሚጨመር 2 ሚሊየን ፓውንድ ለዝውውሩ ወጪ ማድረጉ ነው የተገለጸው፡፡

በተጨማሪም የቀድሞ ክለቡ ቼልሲ ከተጫዋቹ የወደፊት ሽያጭ 10 በመቶ እንደሚያገኝ በዝውውር ውሉ ላይ ተመላክቷል፡፡

የ22 ዓመቱ ተጫዋች በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት እስከ 2031 የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

አንድሬይ ሳንቶስ በፈረንጆቹ 2023 ከሀገሩ ክለብ ቫስኮ ደጋማ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ በ10 ነጥብ 2 ሚሊየን ፓውንድ መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡
Смотреть все посты