Каталог каналов Мои подборки Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.1K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 572
Сегодня
-14
Просмотров на пост
Всего
1 696
ER
Общий
4.22%
Суточный
3.2%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 148 постов
Смотреть все посты
Пост от 24.04.2026 14:59
921
0
3
አሜሪካ በቀጣዩ የዓለም ዋንጫ ኢራንን በጣሊያን ለመተካት…

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሜሪካ በቀጣዩ የዓለም ዋንጫ ኢራንን በጣሊያን መተካት እንደምትፈልግ ገለጸች፡፡

የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ፓውሎ ዛምፖሊ ፊፋ በዓለም ዋንጫው ኢራንን በጣሊያን እንዲተካ ጠይቀዋል።

ኢራን ከአሜሪካ እና እስራኤል ጋር በገባችበት ጦርነት ምክንያት ብሔራዊ ቡድኑ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የመካፈሉ ጉዳይ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል፡፡

የኢራን ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ካለፉ ብሔራዊ ቡድኖች መካከል አንዱ ሲሆን÷ ጣሊያን ለሶስተኛ ተከታታይ ጊዜ ከውድድር ውጪ መሆኗ ይታወሳል፡፡

የአራት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊዋ ጣሊያን ከ2026 ዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ መሆኗን ተከትሎ የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ እና የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ከኃላፊነት መነሳታቸው ይታወሳል፡፡

የጣሊያን መንግሥት በበኩሉ÷ ሀገሪቱ ኢራንን እንድትተካ የቀረበውን ሐሳብ በይፋ ተቃውሟል።

የጣሊያን ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ሉቺያኖ ቦንፊግልዮ እንዳሉት÷ ጣሊያን በመጪው የዓለም ዋንጫ ውድድር ኢራንን የመተካት ፍላጎት የላትም፡፡

የዓለም ዋንጫ ተሳትፎ በችሎታ እና በጠንካራ ስራ መሆን አለበት በማለት ሐሳቡን ውድቅ አድርገዋል፡፡

የጣሊያን ስፖርት ሚኒስትር አንድሪያ አቦዲ በበኩላቸው÷ የቀረበው ሐሳብ አስፈላጊ አይደለም፤ ሜዳ ላይ አሸንፈን ነው ማለፍ ያለብን ብለዋል።

የጣሊያን የገንዘብ ሚኒስትር ጂያንካርሎ ጆርጅቲ ሐሳቡ አሳፋሪ መሆኑን ጠቅሰው÷ በዚህ መንገድ ወደ ዓለም ዋንጫ ከሄድን ያሳፍራል ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ፊፋ በበኩሉ÷ አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ የሚያዘጋጁት የ2026 ዓለም ዋንጫ ውድድር በታቀደው ፕሮግራም እንደሚቀጥል ማሳወቁን የቲ አር ቲ ዘገባ አመላክቷል።

በወንድማገኝ ጸጋዬ
👍 1
Пост от 24.04.2026 09:22
1 195
0
1
ኤክስትራ ታይም ስፖርት በፋና ፖድካስት

ከደቂቃዎች በኋላ በቀጥታ ስርጭት  ይጠብቁን

#ስፖርት_ፖድካስት​
#ፖድካስት #ፋናፖድካስት  #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን  #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #PoodkaastiiFaanaa #fanadigitalmedia فانا_عربي_بودكاست
Изображение
👍 1
Пост от 23.04.2026 15:29
1 489
0
2
ላሚን ያማል ከውድድር ዓመቱ ውጪ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው የባርሴሎና የፊት መስመር ተጫዋች ላሚን ያማል ከውድድር ዓመቱ ውጪ ሆኗል፡፡

ትናንት ምሽት ባርሴሎና ሴልታ ቪጎን ባሸነፈበት ጨዋታ ላሚን ያማል ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ተቀይሮ መውጣቱ ይታወቃል፡፡

በዚህም ተጫዋቹ ከቀሪ የውድድር ዓመቱ ጨዋታዎች ውጪ መሆኑን ክለቡ አረጋግጧል፡፡

የ18 ዓመቱ ተጫዋች በዚህ የወድድር ዓመት በሁሉም ውድድሮች ለባርሴሎና ባደረጋቸው 40 ጨዋታዎች 24 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

ስፔናዊው ተጫዋች ላሚን ያማል ለዓለም ዋንጫ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተመሳሳይ የሪያል ማድሪድ ተጫዋች አርዳ ጉለር ባጋጠመው ጉዳት ከውድደር ዓመቱ ውጪ ሆኗል፡፡

ሪያል ማድሪድ ማክሰኞ ምሽት ዲፖርቲቮ አላቬስን ባሸነፈበት ጨዋታ አርዳ ጉለር ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ አይዘነጋም፡፡

በዚህም የ21 ዓመቱ ተጫዋች ከውድድር ዓመቱ ውጪ የሆነ ሲሆን ለዓለም ዋንጫ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
Пост от 23.04.2026 00:07
1 892
0
3
ማንቼስተር ሲቲ የሊጉን መሪነት ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼሰተር ሲቲ በርንሌይን 1 ለ 0 አሸንፏል።

የማንቼስተር ሲቲን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ኤርሊንግ ብራውት ሀላንድ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል።

ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ አርሰናልን በእርስበርስ ግንኙነት በመብለጥ የሊጉን መሪነት ተረክቧል።

በርንሌይ በበኩሉ ቀሪ አራት ጨዋታ እያለው ከሊጉ መውረዱን አረጋግጧል።
Изображение
Изображение
Изображение
👍 5
Пост от 22.04.2026 19:41
1 873
0
4
ቼልሲ አሰልጣኝ ሊያም ሮሴኒየርን አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ አሰልጣኝ ሊያም ሮሴኒየርን ከኃላፊነታቸው አሰናብቷል፡፡

ክለቡ አሰልጣኙን ያሰናበተው ከፈረንጆቹ 1912 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ምንም ግብ ማስቆጠር ሳይችል አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች መሸነፉን ተከትሎ ነው፡፡

የፈረንሳዩ ክለብ ስትራስቡርግን በመልቀቅ በጥር ወር አምስት ዓመት ከግመሽ ኮንትራት በመፈረም ቼልሲን የተቀላቀሉት ሮሴኒየር÷ በሁሉም ውድድሮች 23 ጊዜ ክለቡን መርተው 11 ጊዜ ብቻ አሸንፈዋል፡፡

ትናንት ምሽት በብራይተን 3 ለ 0 መሸነፋቸው ለስንብታቸው ቀጥተኛ ምክንያት ሆኗል፡፡

በአቤል ነዋይ
Изображение
👏 1
Пост от 22.04.2026 08:55
2 070
0
1
የቼልሲ የቀድሞ ኮከብ ዴቪድ ሉዊዝ…

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ጋር ስኬታማ ዓመታትን ማሳለፍ የቻለ ኮከብ ነው ብራዚላዊው ተጫዋች ዴቪድ ሉዊዝ፡፡ የብራዚል ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ተጫዋች ዴቪድ ሉዊዝ ፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ሕይወቱን የጀመረው በሀገሩ ክለብ ቪቶሪያ ነው፡፡ የቼልሲ የቀድሞ ኮከብ በዓለም እግር ኳስ ከታዩ ምርጥ የመሐል ተከላካዮች መካከል አንዱ ሲሆን ከአስደናቂ…

https://www.fanamc.com/archives/313419
Пост от 22.04.2026 00:06
1 950
0
1
ቼልሲ በብራይተን ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ብራይተን ቼልሲን 3 ለ 0 አሸንፏል።

ምሸት 4 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የብራይተንን የማሸነፊያ ግቦች ካዲዮግሉ፣ ሂንሼልውድ እና ዌልቤክ አስቆጥረዋል።

ቼልሲ በሊጉ አምስተኛ ተከታታይ ሽንፈት አስተናግዷል።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
Смотреть все посты