Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.4K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 079
Сегодня
-24
Просмотров на пост
Всего
1 694
ER
Общий
4.09%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 442 постов
Смотреть все посты
Пост от 18.05.2026 16:44
640
0
2
ባርሴሎና የአሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክን ውል አራዘመ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ባርሴሎና የአሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክን ውል ማራዘሙን ይፋ አድርጓል፡፡

አሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ በካታላኑ ክለብ ባርሴሎና እስከ ፈረንጆቹ 2028 ድረስ የሚያቆይ ውል ተፈራርመዋል፡፡

የ61 ዓመቱ አሰልጣኝ ከባርሴሎና ጋር ለተከታታይ ሁለት የውድድር ዘመን የስፔን ላሊጋ ሻምፒዮን መሆናቸው ይታወቃል፡፡
👍 3
Пост от 18.05.2026 14:26
913
0
2
ዳኒ ካርቫሃል ከሪያል ማድሪድ ጋር ተለያየ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው የቀኝ መስመር የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ዳኒ ካርቫሃል ከሪያል ማድሪድ ጋር ተለያይቷል፡፡

የ34 ዓመቱ ተጫዋች በሪያል ማድሪድ ቆይታው 4 የስፔን ላሊጋ፣ 6 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ እና 2 የኮፓ ዴል ሬይ ዋንጫዎችን ጨምሮ 27 ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡

በፈረንጆቹ 2013 ከጀርመኑ ክለብ ባየር ሊቨርኩሰን ሎስብላንኮሶቹን የተቀላቀለው ካርቫሃል ከአስደናቂ ስኬታማ ዓመታቶች በኋላ ከሪያል ማድሪድ ጋር መለያየቱን ክለቡ ይፋ አድርጓል፡፡
Пост от 18.05.2026 13:31
997
0
2
ሪያል ማድሪድ አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆን ለመሾም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የቀድሞ አሰልጣኙን ጆዜ ሞሪንሆ በድጋሚ ለመሾም መስማማቱ ተነግሯል፡፡

የውድድር ዓመቱን ከሀገራቸው ክለብ ቤኒፊካ ጋር ያሳለፉት ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ወደ ቀድሞው ቤታቸው ሳንቲያጎ ቤርናባው ለመመለስ ተስማምተዋል፡፡

አሰልጣኙ በሪያል ማድሪድ ለሁለት ዓመት የሚያቆያቸውን ውል በቀጣይ ቀናት እንደሚፈርሙ ስካይ ስፖርት ዘግቧል፡፡

ጆዜ ሞሪንሆ ከፈረንጆቹ 2010 እስከ 2013 ማድሪድን በመሩባቸው ሦስት ዓመታት አንድ የላሊጋ፣ የስፔን ሱፐር ካፕ እና የኮፓ ዴል ሬይ ዋንጫዎችን አሳክተዋል፡፡
👍 3
Пост от 18.05.2026 11:29
1 099
0
1
በዓለም የኤምኤምኤ ከባድ ሚዛን ውድድር ካሜሩናዊው ፍራንሲስ ንጋኑ በዝረራ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ ካሊፎርኒያ በተካሄደው በዓለም የድብልቅ ማርሻል አርት (ኤምኤምኤ) ከባድ ሚዛን ውድድር ካሜሩናዊው ፍራንሲስ ንጋኑ ብራዚላዊውን ፍሊፕ ሊንስ በመጀመሪያው ዙር ግጥሚያ በዝረራ አሸንፏል፡፡

ትናንት ምሽት በተካሄደው ውድድር ንጋኑ ከብራዚላዊው የኤምኤምኤ ኮከብ ፍሊፕ ሊንስ ከባድ ፉክክር ቢገጥመውም በሰነዘረው ቡጢ በዝረራ ማሸነፍ ችሏል።

ድሉ ካሜሮናዊው የኤምኤምኤ ኮከብ በአራት ዓመታት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ያሳካው ድል ሆኖ ተመዘግቦለታል፡፡

ፍራንሲስ ንጋኑ በቀጣይም ከአሜሪካዊያኑ ከባድ ሚዛን ቦክስ እና ኤምኤምኤ ተፋላሚዎቹ ጄክ ፖል እና ጆን ቦንስ ጋር ይጋጠማል፡፡

ፍራንሲስ ንጋኑ በፈረንጆቹ 2021 መጋቢት ወር ላይ በተካሄደ ውድድር በሁለተኛው ዙር ተጋጣሚውን በማሸነፍ የዓለም የከባድ ሚዛን ሻምፒዮን መሆኑ ይታወሳል፡፡

በሚኪያስ አየለ
👍 2
Пост от 18.05.2026 09:47
1 120
0
2
አርሰናል ከበርንሌይ - የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል የሊጉ ሻምፒዮን ለመሆን ወሳኝነት ያለውን ጨዋታ ዛሬ ምሽት ያደርጋል፡፡

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ወደ ሻምፒዮንሺፕ መውረዱን ያረጋገጠውን በርንሌይ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኤሚሬትስ ያስተናግዳል፡፡

ሁለቱ ክለቦች በፕሪሚየር ሊጉ እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል 4ቱን ሲያሸነፍ በአንዱ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል፡፡

79 ነጥቦችን በመሰብሰብ ከተከታያቸው ማንቼስተር ሲቲ በሁለት ነጥብ ልዩነት እየመሩ የሚገኙት መድፈኞቹ የዛሬ ምሽቱን ጨምሮ ከክሪስታል ፓላስ ጋር የሚያደርጓቸውን ጨዋታዎች ካሸነፉ የሲቲን ውጤት ሳይጠብቁ የሊጉ ሻምፒዮን ይሆናሉ፡፡
👍 6
Пост от 17.05.2026 21:37
1 203
0
2
ኒውካስል ዌስትሃምን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛው ሳምንት እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኒውካስል ዩናይትድ ዌስትሃምን 3 ለ 1 አሸንፏል።

ከሰሜን ለንደኑ ቡድን ቶተንሃም ጋር እየተፎካከረ የሚገኘው ዌስትሃም በፕሪሚየር ሊጉ የመቆየት ዕድሉን ያጠበበ ሽንፈት በኒውካስል ዩናይትድ አስተናግዷል።

ዊሊያም ኦሱላ (ሁለት) እና ኒክ ዋልትማደ የኒውካስልን ግቦች ሲያስቆጥሩ፥ ታቲ ካስቴላኖስ የዌስትሃምን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።

በዚህ መሰረት ቶተንሃም ማክሰኞ ዕለት ከቼልሲ የሚያደርገውን ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ ዌስትሃም ዩናይትድ መውረዱን የሚያረጋግጥ ይሆናል።

ቀደም ብለው በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ኖቲንግሃም ፎረስትን 3 ለ 2፣ ሰንደርላንድ እና ኤቨርተንን 3 ለ 1፣ ሊድስ ዩናይትድ ብራይተንን 1 ለ 0 አሸንፈዋል።

እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከክሪስታል ፓላስ 2 ለ 2 እንዲሁም ወልቭስ ከፉልሃም 1 ለ 1 ተለያይተዋል።
👍 2
Пост от 17.05.2026 19:59
1 193
0
2
ኢትዮጵያ 2ኛውን የብር ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጋና አክራ እየተካሄደ ባለው 24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 2ኛውን የብር ሜዳሊያ አገኘች።

በጦር ውርወራ ወንዶች አትሌት ኦታጌ ኦባንግ ሁለተኛ በመውጣት በውድድሩ ለኢትዮጵያ 13ኛውን ሜዳሊያ አስገኝቷል።

በ400 ሜትር መሰናክል ሴቶች አትሌት ባንቻየሁ ተሰማ 5ኛ፤ አትሌት ደራርቱ እኖታ 6ኛውን ደረጃ ይዘው አጠናቅቀዋል።

በወርቅነህ ጋሻሁን
🙏 1
Смотреть все посты