Каталог каналов Мои подборки Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.1K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 630
Сегодня
-19
Просмотров на пост
Всего
1 631
ER
Общий
4%
Суточный
3.2%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 135 постов
Смотреть все посты
Пост от 21.04.2026 21:21
424
0
2
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቅቋል፡፡

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላለፉት ሁለት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ነው የተጠናቀቀው፡፡

በዚህም ፌዴሬሽኑ ላለፋት ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ተደርጎበት በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል።

በተሻሻለው የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ የስልጣን ጊዜ ከሁለት ዙር እንደማይሻገር ነው የተገለጸው፡፡

ስራ አስፈጻሚ አባላት በአንድ ምርጫ ለአራት ዓመታት የሚመሩ ሲሆን ከአባላቱ መካከል ቢያንስ አንዱ የቀድሞ አትሌት፣ አሰልጣኝ ወይም የስፖርት ሳይንስ ምሁር መሆን እንዳለበት ተመላክቷል፡፡

አህጉራዊ የአትሌቲክስ ተቋማት በጠቅላላ ጉባኤው ላይ ተገኝተው ድምፅ የመስጠት መብት በደንቡ የተሰጣቸው ሲሆን ትውልደ ኢትዮጵያ በስራ አስፈጻሚነት መወዳደር እንደማይችሉ አስቀምጧል፡፡

በተጨማሪም ተቋማዊ ሪፎርም፣ የሰው ሃይል መዋቅራዊ ጥናት፣ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ እና የተሻሻለ የግዥና ፋይናንስ መመሪያዎች ቀርበው መጽደቃቸው ተገልጿል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ መኪዩ መሐመድ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ የተጀመረው ተቋማዊ ለውጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ፌዴሬሽኖች እና ማህበራት ይቀጥላል ብለዋል።

እንደሀገር የተጀመረው የስፖርቱን ስብራት የመጠገን ሂደት የሁሉንም የዘርፉ ተዋንያን ትብብር እንደሚፈልግ ገልጸው መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡

በወርቅነህ ጋሻሁን
🙏 1
Пост от 21.04.2026 17:16
795
0
1
ቅዱስ ጊዮርጊስ አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ አዳማ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ፍፁም ጥላሁን በሁለተኛው አጋማሽ አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ35 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ አዳማ ከተማ በበኩሉ በ33 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

አዳማ ከተማ በሊጉ ተከታታይ ስድስተኛ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 21.04.2026 09:57
1 249
0
2
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና አዳማ ከተማ ይጫወታሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና አዳማ ከተማ ይገናኛሉ።

ጨዋታው ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል።

ትናንት በተደረጉ የሊጉ የሳምንቱ መርሐ ግብሮች ሸገር ከተማ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 0፣ ወላይታ ድቻ ምድረ ገነት ሽረን 1 ለ 0 ሲያሸንፉ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 21.04.2026 09:32
1 154
0
1
ቼልሲ ከአራት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት በኋላ ወደ ድል ለመመለስ…

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ብራይተንን ይገጥማል፡፡

በሊጉ ባለፉት አራት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት ያስተናገደው ቼልሲ ወደ አሸናፊነት ለመምጣት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ከሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ የአቻ ውጤት ያስመዘገበው ብራይተን በበኩሉ ወደ ድል ለመመለስ ይፋለማል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ብራይተን ሦስቱን ሲያሸንፍ ቼልሲ በሁለቱ ድል አድርጓል፡፡

ሊጉን አርሰናል በ70 ነጥብ ሲመራው አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ያለው ማንቼስተር ሲቲ በ67 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ በ58 ነጥብ 3ኛ እንዲሁም አስቶንቪላ በተመሳሳይ 58 ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡

ወልቭስ አምስት ጨዋታዎች እየቀሩት ወደ ሻምፒዮን ሺፑ መውረዱን ያረጋገጠ ሲሆን ቶተንሃም ሆትስፐር እና በርንሌይ ወራጅ ቀጣናው ላይ የሚገኙ ቡድኖች ናቸው፡፡
Пост от 20.04.2026 18:11
1 191
0
1
ወላይታ ድቻ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ምድረ ገነት ሽረን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 10 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የወላይታ ድቻን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ያሬድ ዳርዛ አስቆጥሯል።

በተመሳሳይ ሰዓት በአዲስ አበባ ስታየም በተደረገው ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ኢትዮጵያ መድን 1 ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

በጨዋታው የኢትዮ ኤሌክትሪክን ግብ በዛብህ መለዮ ሲያስቆጥር÷ የኢትዮጵያ መድንን አማኑኤል ኤርቦ ከመረብ አሳርፏል።

ቀደም ሲል ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሸገር ከተማ ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
👏 3
Пост от 20.04.2026 15:07
1 205
0
1
ሸገር ከተማ ባሕር ዳር ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሸገር ከተማ ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአዲስ አበባ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የሸገር ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ቢንያም ፍቅሩ እና ቡልቻ ሹራ አስቆጥረዋል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ መድን ይገናኛል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ምድረ ገነት ሽረ ከወላይታ ድቻ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Пост от 20.04.2026 11:11
1 116
0
1
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 29ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ በጉባኤው መክፈቻ ላይ አዲሱ የፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ በአንድ ዓመት ውስጥ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን አንስተዋል፡፡

የአትሌቲክሱን ዘርፍ ለማሳደግ ፌዴሬሽኑ ከመንግስት ጋር በመተባበር የውድድር ዝግጀት እና የፋይናንስ ድጋፍ እንዲደረግ ጥረት ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡

ለሁለት ቀናት በሚካሄደው በዚህ መድረክ በ28ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ቃለጉባኤ፣ በ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፣ በውጭ ኦዲት ሪፖርት፣ በ2018 በጀት ዓመት የሥራ እቅድና በጀት፣ በተቋማዊ አሰራር ሪፎርም ሰነድ እና የሰው ኃይል መዋቅራዊ ጥናት ቀርቦ ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል።

እንዲሁም በተሻሻለው የፌዴሬሽኑ መተዳደሪያ ደንብ፣ በአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ እና በተሻሻለውን የፌዴሬሽኑ የግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር መመሪያ በአጀንዳነት የሚመከርባቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።

በሌዊ በለጠ
Смотреть все посты