Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.8K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 440
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 026
ER
Общий
4.97%
Суточный
3.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 772 постов
Смотреть все посты
Пост от 27.06.2026 19:54
175
0
1
የዓለም ዋንጫው የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዎች…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ መርሐ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡

በምድብ-11 አስቀድመው 32ቱን መቀላቀላቸውን ያረጋገጡት ፖርቹጋል እና ኮሎምቢያ ምድቡን በበላይነት ለማጠናቀቅ ሌሊት 8 ሰዓት ከ30 የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በምድቡ 2ኛ ጨዋታ ለሀገሩ ፖርቹጋል 2 ግቦችን በማስቆጠር አዳዲስ ክብረወሰኖችን ያስመዘገበው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በምሽቱ ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በዚሁ ምድብ በተመሳሳይ ሰዓት ኡዝቤክስታንን የምትገጥመው ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ ይህንን ጨዋታ ካሸነፈች ምርጥ 3ኛ በመሆን 32ቱን ትቀላቀላለች፡፡

በሊዮኔል ሜሲ አምስት ግቦች ታግዛ የምድቧን ሁለቱንም ጨዋታዎች በማሸነፍ 32ቱን የተቀላቀለችው አርጀንቲና ንጋት 11 ሰዓት ላይ በምድቡ ግርጌ የምትገኘውን ጆርዳን ትገጥማለች፡፡

በ18 ግቦች የዓለም ዋንጫው የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የግሉ ያደረገው ሊዮኔል ሜሲ በዚህም ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በዚህ ምድብ የምትገኘው ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጄሪያ 32ቱን ለመቀላቀል በተመሳሳይ ሰዓት ከኦስትሪያ ጋር በምታደርገው ጨዋታ አቻ መውጣት ይበቃታል፡፡

ከመጨረሻው ምድብ ከዛሬ ምሽቱ ጨዋታ አስቀድማ ማለፏን ያረጋገጠችው እንግሊዝ መሰናበቷን ካረጋገጠችው ፓናማ ጋር እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ላይ ትጫወታለች፡፡

በተመሳሳይ 32ቱን መቀላቀሏን ያረጋገጠችው የአፍሪካ ተወካይዋ ጋና በበኩሏ ከክሮሺያ ጋር በተመሳሳይ ሰዓት የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
Пост от 27.06.2026 17:22
7
0
1
ድሬዳዋ ከተማ ከፕሪሚየር ሊጉ ወረደ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ በ39 ነጥብ 18ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ድሬዳዋ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል፡፡

ቀደም ሲል አርባምንጭ ከተማ እና መቐለ 70 እንደርታ ከሊጉ መውረዳቸው ተረጋግጧል፡፡
Пост от 27.06.2026 08:55
324
0
1
ሴኔጋል፣ ኬፕቨርዴ እና ግብጽ 32ቱን ተቀላቀሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ ሴኔጋል፣ ግብጽና ኬፕቨርዴ 32ቱን ተቀላቀሉ።

ዛሬ ማለዳ 12 ሰዓት በተደረጉ የምድብ-7 የመጨረሻ ጨዋታዎች ግብጽ ከኢራን 1 ለ 1 አቻ ስትለያይ፥ ቤልጂየም ኒውዚላንድን 5 ለ 1 አሸንፋለች።

ውጤቱን ተከትሎ ቤልጂየም እና ግብጽ በተመሳሳይ 5 ነጥቦች በግብ ክፍያ ተበላልጠው ከምድባቸው ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።

ሌሊት 9 ሰዓት ላይ በምድብ-8 በተደረጉ የመጨረሻ ጨዋታዎች አፍሪካዊቷ ሀገር ኬፕ ቨርዴ ከሳዑዲ አረቢያ ያለ ግብ አቻ የተለያየች ሲሆን፥ ስፔን ዩራጓይን 1 ለ ዐ አሸንፋለች።

በዚህም መሰረት በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችው ኬፕ ቨርዴ ስፔንን በመከተል የ32ቱን ጥሎ ማለፍ ተቀላቅላለች።

በምድብ 9 ትናንት ምሽት ኢራቅን 5 ለ ዐ ያሸነፈችው ሴኔጋል በበኩሏ ምርጥ 3ኛ በመሆን 32ቱን መቀላቀሏን አረጋግጣለች።

እስካሁን ሰባት የአፍሪካ ሀገራት (ደቡብ አፍሪካ፣ ሞሮኮ፣ ኮትዲቯር፣ ጋና፣ ሴኔጋል፣ ግብጽ እና ኬፕቨርዴ) በቀጥታ ከምድባቸው ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።
Пост от 27.06.2026 00:11
50
0
1
ፈረንሳይ ኖርዌይን አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 23ኛው የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ፈረንሳይ ኖርዌይን 4 ለ 1 አሸንፋለች።

በምድብ ዘጠኝ ያደረጓቸውን ሁለቱንም ጨዋታዎች በማሸነፍ አስቀድመው 32ቱን የተቀላቀሉት ፈረንሳይ እና ኖርዌይ ምሽት 4 ሰዓት ተገናኝተው፤ ፈረንሳይ በማሸነፏ 9 ነጥብ በመያዝ ምድቡን በበላይነት አጠናቅቃለች፡፡

የፈረንሳይን ሶስት ግቦች ኦስማን ዴምቤሌ በማስቆጠር ሃት-ሪክ የሰራ ሲሆን፤ አራተኛውን ግብ ዱዌ አስቆጥሯል።

የኖርዌይን ብቸኛ ግብ አስጋርድ ከመረብ አገናኝቷል።

በዚሁ ምድብ በተመሳሳይ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ኢራቅን የገጠመችው አፍሪካዊቷ ሀገር ሴኔጋል 5 ለ 0 በማሸነፍ ምርጥ ሦስተኛ በመሆን 32ቱን ለመቀላቀል የሚያስችላትን ዕድል ፈጥራለች።
Пост от 26.06.2026 21:25
1
0
0
ሪያል ማድሪድ ከዳኒ ሴባዮስ ጋር ተለያየ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ ከስፔናዊው ተጫዋች ዳኒ ሴባዮስ ጋር መለያየቱን ይፋ አድርጓል።

ዳኒ ሴባዮስ ከፈረንጆቹ 2017 ጀምሮ በሪያል ማድሪድ ለሰባት የውድድር ዘመናት ቆይቷል።

የ29 ዓመቱ ተጫዋች ለሪያል ማድሪድ 215 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን 16 ዋንጫዎችን አሳክቷል።

ክለቡ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ ዳኒ ሴባዮስ በሎስብላንኮቹ ቤት በነበረው ቆይታ ላሳየዉ ቁርጠኝነት እና ትጋት ምስጋናውን አቅርቦ ሪያል ማድሪድ ሁልጊዜም የእሱ ቤት መሆኑን ገልጿል።

ሪያል ማድሪድ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ከሌላኛው ስፔናዊ ተጫዋች ዳኒ ካርቫሀል ጋር መለያየቱ ይታወሳል።
Пост от 26.06.2026 18:18
342
0
2
ኢትዮጵያ ቡና መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና መቐለ 70 እንደርታን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲም በተደረገው ጨዋታ ቢኒያም ጌታቸው (ሁለት) እና ቫይን ዋቹንክዋ ለቡናማዎቹ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡

ቀደም ሲል በተካሄዱ የሊጉ ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 እንዲሁም ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 26.06.2026 17:24
1
0
0
ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ፍፁም ጥላሁን አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ይገናኛሉ፡፡

አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና መቐለ 70 እንደርታን 2 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ቡናን ግቦች ዲቫይን ዋችኩዋ (በፍጹም ቅጣት ምት) እና ቢኒያም ጌታቸው ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
Смотреть все посты