Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.6K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 691
Сегодня
-20
Просмотров на пост
Всего
2 008
ER
Общий
5.5%
Суточный
3.8%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 573 постов
Смотреть все посты
Пост от 02.06.2026 11:01
658
0
1
ቶማስ ፓርቴይ ዓለም ዋንጫ በሚሳተፈው የጋና ብሔራዊ ቡድን ስብስብ ውስጥ ተካተተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞው የአርሰናል አማካይ ቶማስ ፓርቴይ በዓለም ዋንጫ በሚሳተፈው የጋና ብሔራዊ ቡድን ስብስብ ውስጥ ተካትቷል፡፡

ከፈረንጆቹ 2020 እስከ 2022 በአራት ሴቶች የጾታዊ ጥቃት ክስ የቀረበበት ቶማስ ፓርቴይ የቀረቡበት ሁሉም ክሶች ሐሰት መሆናቸውን ሲገልጽ ቆይቷል፡፡

የ32 ዓመቱ ተጫዋች አሁን ላይ ለስፔን ላሊጋው ክለብ ቪያ ሪያል እየተጫወተ ሲሆን÷ የቀድሞ ብቃቱ ከድቶት ተስተውሏል፡፡

የጋና ኤፍኤ ፕሬዚዳንት ኩርት ኦክራኩ ቶማስ ምክትል አምበላችን ነው፤ እሱ በዓለም ላይ ካሉ ምርጥ አማካዮች አንዱ ነው በማለት በዚህ አስቸጋሪ ጊዜው ከጎኑ እንቆማለን ብለዋል።

የጋና ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ካርሎስ ኪሮሽ ቶማስ ፓርቴይን ለዓለም ዋንጫ ዝግጅት ብሎም ከዌልስ ጋር ላለባቸው የወዳጅነት ጨዋታ የቡድኑ አካል አድርገውታል፡፡

የስፓርታክ ሞስኮው ተከላካይ አሌክሳንደር ጂኩ እንዲሁም የቶተንሃሙ ሞሀመድ ኩዱስ በጉዳት ከብሔራዊ ቡድኑ ስብስብ ውጪ የሆኑ ተጨዋቾች ናቸው፡፡

የማንቼስተር ሲቲው አንቶኢን ሴሜኞ፣ የኮቨንተሪ ሲቲው አጥቂ ብራንዶን ቶማስ አሳንቴ እንዲሁም የሌስተር ሲቲ ተጫዋቾች የሆኑት ጆርዳን አዩ እና አብዱል ፋታው ብሔራዊ ቡድኑን የተቀላቀሉ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

ጋና የምድቧን የመጀመሪያ ጨዋታ በካናዳ ቶሮንቶ ከፓናማ ጋር ትጫወታለች፡፡

በአቤል ነዋይ
Изображение
👏 2
Пост от 01.06.2026 21:12
1 171
0
3
በራባት የዳይመንድ ሊግ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ ራባት በተካሄደው የሴቶች 1 ሺህ 500 ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ አሸንፋለች፡፡

አትሌት ፍሬወይኒ ርቀቱን 3 ደቂቃ 58 ሰከንድ ከ25 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ነው ቀዳሚ የሆነችው፡፡

በርቀቱ የተሳተፈችው ሌላኛዋ አትሌት ሐረገወይን ካልአዩ ደግሞ 3 ደቂቃ 59 ሰከንድ ከ28 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች፡፡

በሌላ በኩል በሴቶች 800 ሜትር ውድድር አትሌት ፅጌ ድጉማ በ1 ደቂቃ 57 ሰከንድ ከ24 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 2ኛ ሆናለች፡፡
Пост от 31.05.2026 10:10
1 625
0
6
የኢትዮጵያ ካራቴ ብሔራዊ ቡድን አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን አሸነፈ

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የምስራቅ አፍሪካ ካራቴ ሻምፒዮና ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ካራቴ ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያ ቀን ውሎ ዘጠኝ ሜዳሊያዎችን አግኝቷል።

በኬንያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው ውድድር ብሔራዊ ቡድኑ በወንዶች ከ75 ኪሎ ግራም በታች እና ከ53 ኪሎ ግራም በታች እንዲሁም በሴቶች ካታ እና በቡድን ኮሚቴ ባሳየው ድንቅ ብቃት አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን አሸንፏል።

በተጨማሪም በወንዶች ከ67 ኪሎ ግራም በታች እና በቡድን ካታ ውድድር ሁለት የብር ሜዳሊያዎች ተገኝተዋል።

በወንዶች ካታ ከ60 ኪሎ ግራም በታች እና ከ84 ኪሎ ግራም በታች ሶስት የነሐስ ሜዳሊያዎች የተመዘገበባቸው ሌሎች ዘርፎች ናቸው።

በናይሮቢ እየተደረገ ያለው የምስራቅ አፍሪካ የካራቴ ሻምፒዮና ውድድር ዛሬ ፍጻሜውን የሚያገኝ ሲሆን አምስት ሀገራት እየተሳተፉ እንደሚገኙ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል።
👍 8
Пост от 30.05.2026 22:16
1 845
0
4
ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፈረንሳዩ እግር ኳስ ክለብ ፒኤስጂ አርሰናልን በማሸነፍ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አንስቷል፡፡

ፒኤስጂ ከአስቸጋሪ አጀማመር በኋላ አርሰናልን 4 ለ 3 በሆነ ውጤት በመርታት ነው ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ማሳካት የቻለው፡፡

ጨዋታው በጀመረ በ6ኛው ደቂቃ ካይ ሃቨርትዝ ለአርሰናል የመሪነቷን ግብ አስቆጥሮ የመጀመሪያው አጋማሽ በአርሰናል 1 ለ 0 መሪነት ተጠናቅቋል፡፡

ይሁን እንጂበሁለተኛው አጋማሽ ፒኤስጂ በ65ኛው ደቂቃ በኡስማን ዴምቤሌ የፍጹም ቅጣት ምት ግብ አቻ ሆኗል።

መደበኛ የጨዋታ ጊዜው በአቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎም ጨዋታው ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ ያመራ ሲሆን፥ በዚህም  ሳይሸናነፉ ቀርተዋል።

በመጨረሻም የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ አሸናፊን ለመለየት በተሰጠ የመለያ ምት ፒኤስጂ አርሰናልን በማሸነፍ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ ማንሳት ችሏል።
👎 2
Пост от 30.05.2026 18:16
2 010
0
1
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ተፋላሚዎቹ አሰላለፍ ይፋ ሆኗል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ተፋላሚዎች ፒኤስጂ እና አርሰናል አሰላለፋቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡

በዚህም አርሰናል ራያ፣ ማጋሌስ፣ ሳሊባ፣ ሂንካፔ፣ ሞስኬራ፣ ራይስ፣ ሊዊስ ስኬሊ፣ ኦዴጋርድ፣ ሳካ፣ ሃቨርትዝ እና ትሮሳርድን ቋሚ በማድረግ ጨዋታውን ይጀምራል።

ፒኤስጂ በበኩሉ ዴምቤሌ፣ ሜንዴዝ፣ ማርኪኖዮስ፣ ፓቾ፣ ሃኪሚ፣ ቪቲኒያ፣ ኔቬስ፣ ሩይዝ፣ ክቫራቲስኬሊያ እና ዱዌ ቋሚ ተሰላፊ መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በዛሬው ዕለት ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ ይጀምራል፡፡
Пост от 30.05.2026 14:38
2 128
0
4
ሊቨርፑል አሰልጣኝ አርነ ሥሎትን አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዙ ክለብ ሊቨርፑል ኔዘርላንዳዊውን አሠልጣኝ አርነ ሥሎት ማሰናበቱን ይፋ አድርጓል፡፡
🙏 2
Пост от 30.05.2026 11:11
1 627
0
1
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮ ኤሌክትሪክን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛው ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 1 አሸንፏል።

የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ትናንት ተጀምሮ በከባድ ዝናብ ምክንያት በ30ኛው ደቂቃ ላይ የተቋረጠ ሲሆን÷ ዛሬ ከጠዋት 3፡30 ጀምሮ ነው የተካሄደው።

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው በዚህ ጨዋታ ውጤት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ማሸነፊያ ግቦች ናትናኤል ዳንኤል ሲያስቆጥር÷ የኢትዮ ኤሌክትሪክን ግብ ሀብታሙ ሸዋለም ከመረብ አሳርፏል።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ ቀን 7 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ እንዲሁም ቀን 10 ሰዓት መቐለ 70 እንደርታ ከባህር ዳር ከተማ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

እንዲሁም ቀን 10 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና ኢትዮጵያ መድን ይገናኛሉ።
Смотреть все посты