Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.3K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 360
Сегодня
-10
Просмотров на пост
Всего
1 792
ER
Общий
4.26%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 271 поста
Смотреть все посты
Пост от 06.05.2026 17:05
1
0
0
ኢትዮጵያ መድን ሲዳማ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ መድንን የማሸነፊያ ግብ ሳሙኤል ሳሊሶ በ2ኛው አጋማሽ አስቆጥሯል፡፡

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና መሸነፉን ተከትሎ ከተከታዩ መቻል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 10 ከፍ የሚያደርግበትን ዕድል ሳይጠቀም ቀርቷል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ ፋሲል ከነማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

የባህር ዳር ከተማን ግቦች አማኑኤል ገብረሚካኤል እና ብሩክ ሰሙ አስቆጥረዋል፡፡

ሊጉ ሲቀጥል ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከነገሌ አርሲ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይገናኛሉ፡፡
Пост от 06.05.2026 12:20
619
0
1
ከፓሪስ እስከ ቡዳፔስት… 20 ዓመታት የፈጀው ጉዞ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል አትሌቲኮ ማድሪድን በማሸነፍ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ለአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ማለፉን አረጋግጧል፡፡ የሰሜን ለንደኑ ክለብ በመድረኩ ለፍጻሜ ሲያልፍ የዘንድሮው ለ2ኛ ጊዜ ሲሆን፥ ከዚህ ቀደም ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ ለፍጻሜ የደረሰው በ2005/6 የውድድር ዓመት ነበር፡፡ በፈረንጆቹ 2006 በፓሪስ በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ በባርሴሎና 2 ለ 1…

https://www.fanamc.com/archives/314292
Пост от 06.05.2026 10:12
845
0
2
ባየርን ሙኒክ ወይስ ፒኤስጂ - ማን የፍጻሜ ተፋላሚ ይሆናል?

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ ባየርን ሙኒክ በሜዳው ፒኤስጂን ያስተናግዳል፡፡

የጀርመኑ ክለብ ባየርን ሙኒክ በውድድር ዓመቱ የሦስትዮሽ ዋንጫ ሕልሙን ለማሳካት የሚያደርገውን ጉዞ ለማጠናከር የሚያደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡

ባየርን ሙኒክ በዚህ የውድድር ዓመት አስፈሪ የፊት መስመር ጥምረት ያለው ቡድን መሆኑን በሁሉም ውድድሮች እያሳየ ይገኛል፡፡

ሙኒክ በውድድር ዓመቱ እስካሁን ድረስ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ 42 ግቦችን እንዲሁም በቡንደስሊጋው ደግሞ 116 ግቦችን ተጋጣሚዎቹ ላይ አስቆጥሯል፡፡

የአምና የመድረኩ አሸናፊ ፒኤስጂ ለተከታታይ የውድድር ዓመት ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡

ፒኤስጂ በውድድር ዓመቱ እስካሁን ድረስ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ 43 ግቦችን ተጋጣሚዎቹ ላይ አስቆጥሯል፡፡

በዚህም በ2025/26 የውድድር ዓመት በመድረኩ በርካታ ግቦችን ተጋጣሚዎች ላይ በማስቆጠር ቀዳሚው ክለብ ነው፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በፓርክ ደ ፕሪንስ ያደረጉትን የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ፒኤስጂ 5 ለ 4 ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት በአሊያንዝ አሬና የሚደረገውን ተጠባቂ ጨዋታ የ38 ዓመቱ ፖርቹጋላዊ ዳኛ ጇ ፒንሄሮ በመሐል ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል፡፡

የሁለቱ ቡድኖች የድምር ውጤት አሸናፊ በፍጻሜው ከአርሰናል ጋር ይገናኛል፡፡

አርሰናል አትሌቲኮ ማድሪድን በድምር ውጤት 2 ለ 1 በማሸነፍ ከ20 ዓመታት በኋላ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን ማረጋገጡ ይታወቃል፡፡
👏 2
Пост от 06.05.2026 09:30
802
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድን የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ሲዳማ ቡና የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ከተከታዩ መቻል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 10 ከፍ ማድረግ ይችላል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከባህር ዳር ከተማ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ ነገሌ አርሲ ይገናኛሉ፡፡
Пост от 05.05.2026 23:54
1 027
0
3
አርሰናል ከ20 ዓመታት በኋላ ለሻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ አርሰናል አትሌቲኮ ማድሪድን 1 ለ 0 አሸንፏል።

የአርሰናል ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቡካዮ ሳካ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል።

ወደ ስፔን አቅንቶ የመጀመሪያውን ዙር ጨዋታ 1 አቻ አጠናቅቆ የተመለሰው አርሰናል፥ በድምር ውጤት 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ፍጻሜው አልፏል።

በዚህም አርሰናል ከ20 ዓመታት በኋላ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ተፋላሚ ሆኗል።

አርሰናል በፍጻሜው ከባየርን ሙኒክ እና ፒኤስጂ አሸናፊ ጋር ይፋለማል።
👍 14
Пост от 05.05.2026 20:06
1 248
0
1
ምድረ ገነት ሽረ ኢትዮ ኤሌክትሪክን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ምድረ ገነት ሽረ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ምሽት 12 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የምድረ ገነት ሽረን ማሸነፊያ ግብ አንተነህ ተስፋዬ ከመረብ አሳርፏል።

ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ያለምንም ግብ አቻ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 እንዲሁም አርባ ምንጭ ከተማ መቐለ 70 እንደርታን 2 ለ 0 አሸንፈዋል።
👍 4
Пост от 05.05.2026 18:07
1 034
0
1
አርባ ምንጭ ከተማ መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባ ምንጭ ከተማ መቐለ 70 እንደርታን 2 ለ 0 አሸንፏል።

ሁለቱ ቡድኖች ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን÷ የአርባ ምንጭ ከተማን ማሸነፊያ ግቦች አብዱል ራህማን እና አሸናፊ ፊዳ አስቆጥረዋል።

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምድረ ገነት ሽረ እና ባህር ዳር ከተማ ከምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ።

ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ያለምንም ግብ አቻ ሲለያዩ÷ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 አሸንፏል።
👍 1
Смотреть все посты