Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
18.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
38 194
Сегодня
-15
Просмотров на пост
Всего
2 293
ER
Общий
4.39%
Суточный
3.8%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 18 868 постов
Смотреть все посты
Пост от 27.03.2026 21:03
775
0
3
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን 3 ለ 0 አሸንፏል።

በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የዋልያዎቹን የማሸነፊያ ግቦች አቤል ያለው (2) እና ከነዓን ማርክነህ አስቆጥረዋል።

የመልሱ ጨዋታ በቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ በድሬዳዋ ስታዲየም የሚደረግ ይሆናል።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
👍 9
Пост от 27.03.2026 20:01
835
0
1
2 ለ 0 እየመራ እረፍት የወጣው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር የመጀመሪያ ጨዋታውን እያደረገ ይገኛል።

ዋልያዎቹ ከነዓን ማርክነህ እና አቤል ያለው ባስቆጠሯቸው ግቦች 2 ለ 0 በመምራት እረፍት ወጥተዋል።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
👏 1
Пост от 27.03.2026 18:29
1 099
0
1
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ምሽት ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

ሳኦቶሜን የሚገጥመው ዋልያዎቹ አሰላለፍ ይፋ ተደርጓል።

በዚህም አቡበከር ኑራ፣ ዓለምብርሃን ይግዛው፣ ራምኬል ጀምስ፣ ያሬድ ባዬ፣ ያሬድ ካሳዬ፣ ወገኔ ገዛኸኝ፣ ከነዓን ማርክነህ፣ ሀብታሙ ተከስተ፣ መስፍን ታፈሰ፣ አቤል ያለው እና ቸርነት ጉግሳ በመጀመሪያው አሰላለፍ ውስጥ ተካትተዋል።

ጨዋታው በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ መደረግ ይጀምራል።

የመልሱ ጨዋታ በቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ በድሬዳዋ ስታዲየም የሚደረግ ይሆናል።
Пост от 27.03.2026 12:13
1 311
0
2
ሳላህ ከምንጊዜም ምርጥ ተጫዋቾች አንዱ ነው - የርገን ክሎፕ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ግብጻዊው ኮከብ ሞሃመድ ሳላህ ከምንጊዜም ምርጥ ተጫዋቾች አንዱ ነው አሉ ጀርመናዊው አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ፡፡

የፈረኦኖቹ ንጉስ ዘጠኝ የስኬት ዓመታትን ካሳለፈበት ሊቨርፑል በመጪው ክረምት እንሚለያይ በዚህ ሳምንት መግለጹ ይታወሳል፡፡

የቀዮቹ የቀድሞ አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ በሰጡት አስተያየት ተጫዋቹ በአንፊልዱ ክለብ በቀላሉ የማይደረስበት አስገራሚ ታሪክ ሰርቷል ብለዋል፡፡

ሞሃመድ ሳላህ የባሎንዶር ሽልማትን እንዴት እንዳላገኘ እንደሚያስገርማቸው ገልጸው፥ ከምንጊዜም ምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ሳላህ በሊቨርፑል ያሳካውን አስደናቂ ስኬት መድገም የሚችል ተጫዋች ስለመኖሩ እንደሚጠራጠሩ አንስተዋል፡፡

ክሎፕ ተጫዋቹን በፈረንጆቹ 2017 ከጣሊያኑ ሮማ በ34 ሚሊየን ፓውንድ ያስፈረሙት ሲሆን፥ በመርሲሳይዱ ክለብ ለሰባት አመታት አሰልጥነውታል፡፡

የ34 አመቱ ሳላህ በአንፊልድ ቆይታው 255 ግቦችን በማስቆጠር የክለቡ ሶስተኛው የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው፡፡

ሳላህ በክሎፕ የአሰልጣኝነት ዘመን ከሊቨርፑል ጋር የሻምፒየንስ ሊግ፣ ፕሪሚየር ሊግ፣ ሱፐር ካፕ፣ የዓለም ክለቦች ዋንጫን ጨምሮ ሌሎች ሦስት የሀገር ውስጥ ዋንጫዎችን ማሳካት ችሏል፡፡

በአቤል ነዋይ
Пост от 24.03.2026 16:52
1 998
0
1
የቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ተስተካካይ ጨዋታ…

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና የሚያደርጉት የ20ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ የሚደረግበትን ቀን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማሕበር ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም ተስተካካይ ጨዋታው ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ የሚደረግ ይሆናል፡፡

ኢትዮጵያ ቡና በ32 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ÷ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ25 ነጥብ 18ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

ሊጉን ሲዳማ ቡና በ45 ነጥብ ሲመራው ሀዋሳ ከተማ በ40፣ ነገሌ አርሲ በ38 እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ37 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
Изображение
Изображение
🙏 4
👍 2
Пост от 24.03.2026 10:25
1 849
0
6
55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአደይ አበባ ስታዲየም ተጀምሯል።

በሻምፒዮናው 9 ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ ከ36 ክለቦች የተወጣጡ ከ1 ሺህ በላይ አትሌቶች ይሳተፋሉ፡፡

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ ሰዓት መመዝገቢያ ማሽን ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

በዚህም በውድድሩ የሚመዘገቡ ሰዓቶች ዓለም አቀፍ ተቀባይነትን የሚያገኙ ይሆናል፡፡

በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑ አትሌቶች የሜዳሊያ እና የገንዘብ ሽልማት የሚበረከት ሲሆን÷ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በምታስተናግደው የዋን ደይ ሚቲንግ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተመላክቷል፡፡

55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመጋቢት 15 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በአደይ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
👍 2
Пост от 24.03.2026 10:25
1
0
0
55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአደይ አበባ ስታዲየም ተጀምሯል።

በሻምፒዮናው 9 ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ ከ36 ክለቦች የተወጣጡ ከ1 ሺህ በላይ አትሌቶች ይሳተፋሉ፡፡

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ ሰዓት መመዝገቢያ ማሽን ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

በዚህም በውድድሩ የሚመዘገቡ ሰዓቶች ዓለም አቀፍ ተቀባይነትን የሚያገኙ ይሆናል፡፡

በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑ አትሌቶች የሜዳሊያ እና የገንዘብ ሽልማት የሚበረከት ሲሆን÷ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በምታስተናግደው የዋን ደይ ሚቲንግ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተመላክቷል፡፡

55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመጋቢት 15 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በአደይ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
Смотреть все посты