Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.2K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 392
Сегодня
-7
Просмотров на пост
Всего
1 798
ER
Общий
4.33%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 240 постов
Смотреть все посты
Пост от 04.05.2026 15:34
245
0
1
ወላይታ ድቻ ሀድያ ሆሳዕናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 7 ሰዓት 30 ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ግብ መልካሙ ቦጋለ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት 30 ላይ ሀዋሳ ከተማ እና ሸገር ከተማ ይገናኛሉ፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ መቻል ከአዳማ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Пост от 04.05.2026 10:37
815
0
2
ኤቨርተን ከማንቼስተር ሲቲ…

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ ከሜዳው ውጭ ኤቨርተንን ይገጥማል፡፡

የዛሬ ምሽቱን ጨምሮ ሁለት ቀሪ ጨዋታዎች በእጁ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ከአርሰናል ያለውን የስድስት ነጥብ ልዩነት ለማጥበብ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

በቀጣይ የውድድር አመት የአውሮፓ መድረክ ተሳትፎን ለማግኘት እየተፋለመ የሚገኘው ኤቨርተን በበኩሉ ለማንቼስተር ሲቲ ቀላል ተጋጣሚ እንደማይሆን ይጠበቃል፡፡

ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ በአዲሱ ሂል ዲኪንሰን ስታዲየም ይደረጋል፡፡

በሌላ የሊጉ የጨዋታ መርሐ ግብር አሰልጣኙን በማሰናበት የኤፍ ኤ ዋንጫ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን ያረጋገጠው ቼልሲ በስታምፎርድ ብሪጅ ኖቲንግሃም ፎረስትን ያስተናግዳል፡፡

በ48 ነጥብ 9ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ የአውሮፓ መድረክ ቦታን ለማግኘት የሚጫወት ሲሆን፥ ጨዋታው ቀን 11 ሰዓት ላይ ይጀምራል፡፡
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 04.05.2026 10:06
780
0
1
https://www.youtube.com/watch?v=19ONdAz3yVc
Пост от 04.05.2026 09:39
766
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በአዲስ አበባ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ ወላይታ ድቻ ከሀድያ ሆሳዕና እንዲሁም ቀን 10 ሰዓት ላይ ሀዋሳ ከተማ ከሸገር ከተማ ይገናኛሉ፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ መቻል ከአዳማ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ሊጉን ሲዳማ ቡና በ55 ነጥብ ሲመራው መቻል በ47 እንዲሁም ነገሌ አርሲ በ45 ነጥብ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡

የሊጉን ኮከብ ግብ አስቆጣሪነት አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና በ14 ግቦች ሲመራ አዲስ ግደይ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ10 ግቦች ይከተላል፡፡
Пост от 04.05.2026 09:34
667
0
1
ኤክስትራ ታይም ስፖርት በፋና ፖድካስት

ከደቂቃዎች በኋላ በቀጥታ ስርጭት  ይጠብቁን

#ስፖርት_ፖድካስት​
#ፖድካስት #ፋናፖድካስት  #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን  #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #PoodkaastiiFaanaa #fanadigitalmedia فانا_عربي_بودكاست
Пост от 03.05.2026 19:31
1 235
0
3
ማንቼስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በማሸነፍ የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን አረጋገጠ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን 3 ለ 2 አሸንፏል፡፡

11 ሰዓት 30 ላይ በኦልድትራፎርድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የማንቼስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ማቲያስ ኩኛ፣ ቤንያሚን ሼሽኮ እና ኮቢ ማይኖ አስቆጥረዋል፡፡

ሊቨርፑልን ከሽንፈት ያልታደጉ ግቦችን ደግሞ ዶሚኒክ ሶቦዝላይ እና ኮዲ ጋክፖ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ዩናይትድ በቀጣይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ መሆኑን አረጋግጧል፡፡

አስቀድሞ በተደረገ በሌላ የሊጉ መርሐ ግብር ቦርንማውዝ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል አስቶንቪላ ምሽት 3 ሰዓት ላይ በሜዳው ቪላ ፓርክ ቶተንሃም ሆትስፐርን ያስተናግዳል፡፡
👍 10
👏 1
Пост от 03.05.2026 08:44
1 446
0
3
በሼህ ዛይድ በጎ አድራጎት የሩጫ ውድድር አትሌት አለሽኝ ባወቀ እና ንብረት ኪዳኔ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ባደረገው ሼህ ዛይድ በጎ አድራጎት 5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር አትሌት አለሽኝ ባወቀ እና ንብረት ኪዳኔ አሸንፈዋል።

በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ኤምባሲ ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ የሩጫ ውድድር በሴቶች አትሌት አለሽኝ ባወቀ ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቃለች።

አትሌት አለሽኝ ባወቀ በመከተል አትሌት ሽቶ ጉሚ እና ሮቤ ዲዳ ተከታትለው በመግባት 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘዋል።

በወንዶች ደግሞ አትሌት ንብረት ኪዳኔ በቀዳሚነት ውድድሩን ሲያጠናቅቅ፤ አትሌት ኡርጌሳ ነጋሳ እና ግዛቸው ሙሴ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ጨርሰዋል።
Изображение
Изображение
Изображение
Смотреть все посты