Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.5K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 986
Сегодня
-76
Просмотров на пост
Всего
1 705
ER
Общий
4.16%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 480 постов
Смотреть все посты
Пост от 20.05.2026 18:16
459
0
1
ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀዋሳ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ብሩክ አለማየሁ አስቆጥሯል፡፡

ቀደም ብለው በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች መቐለ 70 እንደርታ ሸገር ከተማን 1 ለ 0 እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና ፋሲል ከነማን 2 ለ 1 አሸንፈዋል፡፡

ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ድሬዳዋ ከተማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ከምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡
Пост от 20.05.2026 15:09
847
0
1
መቐለ 70 እንደርታ ሸገር ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛው ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ ሸገር ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታን ማሸነፊያዋ ብቸኛ ግብ ቦና አሊ ከመረብ አገናኝቷል።

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀዋሳ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

በተመሳሳይ ከ9 ሰዓት ጀምሮ ኢትዮጵያ ቡና ከፋሲል ከነማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸው እያደረጉ ሲሆን÷ አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከተማ በተመሳሳይ ስታዲየም ይገናኛሉ።
Пост от 20.05.2026 12:34
1 123
0
1
ገደኛው ቪክቶር ዮከሬሽ…

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቪክቶር ኢናር ዮከሬሽ የተወለደው በአውሮፓዊቷ ሀገር ስዊዲን በፈረንጆቹ 1998 ነው፡፡ በፈረንጆቹ 2015 በሀገሩ ክለብ ብሮማፖጅካርና የመጀመሪያ ጨዋታውን በማድረግ የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ህይወትን የጀመረው ቪክቶር÷ በብራይተን፣ ኮቨንተሪ ሲቲ እና ስዋንሲ ሲቲ በመሳሰሉ የእንግሊዝ ክለቦች ያልተሳካ ጊዜን አሳልፏል፡፡ በውጣ ውረድ የተሞላው የቪክቶር ዮከሬሽ የእግር ኳስ ህይወት ተጫዋቹን…

https://www.fanamc.com/archives/315266
Пост от 20.05.2026 11:42
1 141
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛው ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።

ቀን 7 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ እና መቐለ 70 እንደርታ እንዲሁም 10 ሰዓት ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀዋሳ ከተማ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

በተመሳሳይ ቀን 9 ሰዓት ኢትዮጵያ ቡና ከፋሲል ከነማ እንዲሁም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከተማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይገናኛሉ።
Пост от 19.05.2026 23:26
1 409
0
5
አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ሆነ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2025/26 የውድድር ዓመት ሻምፒዮን ሆኗል።

በ37ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት ማንቼስተር ሲቲ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ መድፈኞቹ አንድ ጨዋታ እየቀራቸው የዋንጫው ባለቤት መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
🙏 12
👍 5
👏 1
Пост от 19.05.2026 20:44
1 672
0
1
የዋንጫው ባለቤት ዛሬ ይታወቃል ወይስ…

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘንድሮው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ባለቤት የሚሆነውን ክለብ ሊወስን የሚችለው የቦርንማውዝ እና ማንቼስተር ሲቲ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ይደረጋል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ የምሽቱን ጨዋታ አቻ ካጠናቀቀ ወይም ሽንፈት ካስተናገደ አርሰናል አንድ ጨዋታ እየቀረው የ2025/26 ሻምፒዮን መሆኑን ዛሬ ምሽት ያረጋግጣል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ተስፋውን እስከ መጨረሻው ሳምንት ለማስቀጠል የምሽቱን ጨዋታ የማሸነፍ ግዴታ ውስጥ ገብቷል፡፡

በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከሲቲ ጋር እንደሚለያዩ የሚጠበቁት ፔፕ ጋርዲዮላ በምሽቱ ጨዋታ የሚጠቀሙት ቋሚ አሰላለፍ ይፋ ሆኗል፡፡

ጂያንሉጂ ዶናሩማ፣ ማቲያስ ኑኔዝ፣ ኩሳኖቭ፣ ማርክ ጉሂ፣ ኒኮ ኦ'ሬሊ፣ ሮድሪ፣ ኮቫቺች፣ በርናርዶ ሲልቫ፣ ሴሜንዮ፣ ዶኩ እና ሀላንድ በቋሚነት ወደ ሜዳ ይገባሉ፡፡

ባለሜዳው ክለብ ቦርንማውዝ ፔትሮቪች፣ ትሩፌርት፣ ሴኔሲ፣ ስኮት፣ ኢቫኒልሰን፣ አዳምስ፣ ስሚዝ፣ ታቨርኔር፣ ክሩፒ ጁኒየር፣ ሂል እና ራያንን በቋሚ አሰላለፍ ይጠቀማል፡፡

ጨዋታው ምሽት 3 ሰዓት ከ30 የሚጀመር ሲሆን፥ የ47 ዓመቱ አንቶኒ ቴይለር በመሃል ዳኝነት ይመሩታል፡፡

በሌላ ጨዋታ በለንደን ደርቢ ቼልሲ በሊጉ ለመቆየት 1 ነጥብ የሚፈልገውን ቶተንሃም ሆትስፐር ምሽት 4 ሰዓት ከ15 በስታምፎርድ ብሪጅ ያስተናግዳል፡፡
Пост от 19.05.2026 18:21
1 324
0
1
ባህርዳር ከተማ እና መቻል አቻ ተለያዩ

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ባህርዳር ከተማ እና መቻል 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የባህርዳር ከተማን ግብ አንተነህ ተፈራ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል፡፡

የመቻል የአቻነት ግብ ፈቱዲን ጀማል (በፍጹም ቅጣት ምት) በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም የተደረገው የሀድያ ሆሳዕና እና ኢትዮጵያ ንግድ ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡

አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በተመሳሳይ ስታዲየም የተገናኙት ኢትዮጵያ መድን እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
Смотреть все посты