Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.7K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 472
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 246
ER
Общий
4.96%
Суточный
4.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 735 постов
Смотреть все посты
Пост от 23.06.2026 11:47
1
0
0
ዶኩ በድጋሚ የቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ስብስብን ይቀላቀላል

‎አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመጀመሪያ ልጁ ሲወለድ ለማየት ብሔራዊ ቡድኑን በመተው ወደ ለንደን ያቀናው ጄሬሚ ዶኩ በድጋሚ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ስብስብ ይመለሳል፡፡

ከዓለም ዋንጫ የብሔራዊ ቡድኑን ስብስብ ጥሎ መውጣቱን ተከትሎ በርካታ ትችቶችን ያስተናገደው ዶኩ ፕሬይዝ የተባለ የወንድ ልጅ አባት ሆኗል፡፡

ተጫዋቹ ልጁ ሲወለድ ከባለቤቱ ጎን ለመሆን በመወሰኑ በአንጻሩ ከብዙሃኑ አድናቆትን አትርፏል፡፡

ቤልጂየም ከዚህ በኋላ በምታደርጋቸው የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች የዶኩን ግልጋሎት የምታገኝ ይሆናል፡፡

ቤልጂየም የምድብ 3ኛ ጨዋታዋን ከኒውዝላንድ ጋር የፊታችን ቅዳሜ ታደርጋለች፡፡

እስካሁን በውድድሩ አንድም ጨዋታ ድል ያላደረገቸው ቤልጂየም በምድቡ 2 ነጥብ ይዛ 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡
Пост от 23.06.2026 11:15
1
0
0
@FMCSport
Пост от 23.06.2026 10:56
1
0
0
እንግሊዝ ከጋና…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ ዛሬ ምሽት እንግሊዝ ከጋና ይገናኛሉ፡፡

በምድብ 12 የሚገኙት እንግሊዝ እና ጋና በምድቡ የመጀመሪያ ጨዋታዎቻቸውን ማሸነፍ የቻሉ ሲሆን፥ የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ የሚያሸንፈው ብሔራዊ ቡድን 32ቱን መቀላቀሉን ያረጋግጣል፡፡

በአሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል የሚመራው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ክሮሽያን ባሸነፈበት ጨዋታ ባሳየው ድንቅ እንቅስቃሴ በውድድሩ ውጤታማ ጊዜን ያሳልፋሉ ተብለው ከሚጠበቁ ቡድኖች መካካል አንዱ ሆኗል፡፡

አንቱዋን ሴሜኒዮን የመሳሰሉ ከዋክብት የያዘችው ምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ጋና ለሦስቱ አናብስት ብርቱ ፈተና እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡

በዚሁ ምድብ ውድድራቸውን በሽንፈት የጀመሩት ክሮሽያ እና ፓናማ በዓለም ዋንጫው የመጀመሪያ ነጥብ ለማግኘት እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ቀደም ብሎ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በምድብ 11 የምትገኘው ፖርቹጋል ከኡዝቤኪስታን ጋር ትጫወታለች፡፡

https://web.facebook.com/share/p/199n2iFihD/
Пост от 22.06.2026 22:19
1
0
0
አርጀንቲና ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ 2ኛ ጨዋታ አርጀንቲና ኦስትሪያን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች።

የአርጀንቲናን ሁለቱንም የማሸነፊያ ግቦች ሊዮኔል ሜሲ ከመረብ አሳርፏል።

ይህን ተከትሎም አርጀንቲና ስድስት ነጥቦችን በመሰብሰብ ከወዲሁ ወደ ጥሎ ማለፉ መቀላቀሏን አረጋግጣለች።

ሜሲ በዓለም ዋንጫ ታሪክ 18 ግቦችን በማስቆጠር የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረ ወሰንን መስበር ችሏል።
Пост от 22.06.2026 21:04
220
0
1
ሊዮኔል ሜሲ የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረ ወሰንን ሰበረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእግር ኳስ ጥበበኛው ሊዮኔል ሜሲ በዓለም ዋንጫ ጨዋታ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረ ወሰንን በመስበር አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል፡፡

ምሽት 2 ሰዓት ላይ መካሄድ በጀመረው እጅግ አስደናቂ ጨዋታ ላይ ሜሲ ክብረ ወሰን መስበር ያስቻለችውን ታሪካዊ ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በዓለም ዋንጫ መድረክ ባስቆጠራት 17ኛዋ ግብም በጀርመናዊው ኮከብ ሚሮስላቭ ክሎዝ በ16 ግቦች ተይዞ የነበረውን የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረ ወሰን በይፋ የግሉ ማድረግ ችሏል፡፡

አርጀንቲና እና ኦስትሪያ እያደረጉት የሚገኘው ጨዋታ የመጀመሪያ አጋማሽ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
👍 1
Пост от 22.06.2026 17:12
1
0
0
አርባምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ ወረደ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርባምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል፡፡

በ36ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ አርባምንጭ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ሁለት ግቦች ታምራት ኢያሱ አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ አርባ ምንጭ ከተማ ቀሪ ሁለት ጨዋታዎች እያሉት ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል።

አርባምንጭ ከተማ ከ2018 የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የወረደ የመጀመሪያው ክለብ ሆኗል።

በተመሳሳይ ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

የኢትዮ ኤሌክትሪክን የማሸነፊያ ግቦች በረከት ወልደዮሐንስ እና አቤል ሀብታሙ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

ወላይታ ድቻን ከሽንፈት ያልታደገውን ግብ ያሬድ ዳርዛ አስቆጥሯል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከሀድያ ሆሳዕና ይገናኛሉ፡፡
Пост от 21.06.2026 11:53
913
0
1
ስፔን ከሳዑዲ አረቢያ…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ 2ኛ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

በምድብ 8 የምትገኘው ስፔን ምሽት 1 ሰዓት ላይ ከሳዑዲ አረቢያ ጋር የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

በ2026 የዓለም ዋንጫ ለሻምፒዮንነት ቅድመ ግምት የተሰጣት ስፔን በውድድሩ የመጀመሪያ ሦስት ነጥብ ለማሳካት ወደ ሜዳ የምትገባ ይሆናል፡፡

ተጋጣሚዋ ሳዑዲ አረቢያም በተመሳሳይ በውድድሩ ሦስት ነጥብ ለማሳካት የምታደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡

በዚሁ ምድብ የሚገኙት ዩራጋይ እና ኬፕቨርዴ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በምድብ-7 ቤልጂየም ከኢራን ምሽት 4 ሰዓት ላይ እንዲሁም ኒውዚላንድ ከግብጽ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡
Смотреть все посты