Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.3K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 370
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
1 778
ER
Общий
4.26%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 265 постов
Смотреть все посты
Пост от 05.05.2026 23:54
298
0
2
አርሰናል ከ20 ዓመታት በኋላ ለሻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ አርሰናል አትሌቲኮ ማድሪድን 1 ለ 0 አሸንፏል።

የአርሰናል ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቡካዮ ሳካ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል።

ወደ ስፔን አቅንቶ የመጀመሪያውን ዙር ጨዋታ 1 አቻ አጠናቅቆ የተመለሰው አርሰናል፥ በድምር ውጤት 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ፍጻሜው አልፏል።

በዚህም አርሰናል ከ20 ዓመታት በኋላ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ተፋላሚ ሆኗል።

አርሰናል በፍጻሜው ከባየርን ሙኒክ እና ፒኤስጂ አሸናፊ ጋር ይፋለማል።
👍 9
Пост от 05.05.2026 20:06
794
0
1
ምድረ ገነት ሽረ ኢትዮ ኤሌክትሪክን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ምድረ ገነት ሽረ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ምሽት 12 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የምድረ ገነት ሽረን ማሸነፊያ ግብ አንተነህ ተስፋዬ ከመረብ አሳርፏል።

ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ያለምንም ግብ አቻ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 እንዲሁም አርባ ምንጭ ከተማ መቐለ 70 እንደርታን 2 ለ 0 አሸንፈዋል።
👍 4
Пост от 05.05.2026 18:07
762
0
1
አርባ ምንጭ ከተማ መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባ ምንጭ ከተማ መቐለ 70 እንደርታን 2 ለ 0 አሸንፏል።

ሁለቱ ቡድኖች ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን÷ የአርባ ምንጭ ከተማን ማሸነፊያ ግቦች አብዱል ራህማን እና አሸናፊ ፊዳ አስቆጥረዋል።

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምድረ ገነት ሽረ እና ባህር ዳር ከተማ ከምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ።

ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ያለምንም ግብ አቻ ሲለያዩ÷ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 አሸንፏል።
👍 1
Пост от 05.05.2026 17:05
750
0
1
ድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ያለምንም ግብ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደረጉት ሁለቱ ቡድኖች ያለምንም ግብ 0 ለ 0 ነው የተለያዩት።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታቸውን እያደረጉ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታ እና አርባምንጭ ከተማ÷ በአርባ ምንጭ ከተማ 1 ለ 0 መሪነት ወደ እረፍት አምርተዋል።

በተመሳሳይ ስታዲየም ምድረ ገነት ሽረ እና ባህር ዳር ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
Пост от 05.05.2026 15:15
887
0
1
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ሁለቱንም ግቦች ናትናኤል ዳንኤል አስቆጥሯል።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ ቀን 10 ሰዓት ላይ በዚሁ ስታዲየም መቐለ 70 እንደርታ እና አርባምንጭ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

እንዲሁም ድሬዳዋ ከተማ ከኢትዮጵያ ቡና ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን እያደረጉ ሲሆን÷ በተመሳሳይ ስታዲየም ምድረ ገነት ሽረ እና ባህር ዳር ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
Пост от 05.05.2026 08:21
1 215
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዕለቱ የመጀመሪያ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ስታዲየም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቀን 7 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።

ቀን 10 ሰዓት ላይ በዚሁ ስታዲየም መቐለ 70 እንደርታ እና አርባምንጭ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ድሬዳዋ ከተማ ከኢትዮጵያ ቡና ቀን 9 ሰዓት እንዲሁም ምድረ ገነት ሽረ ከባህርዳር ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ።
Изображение
Пост от 05.05.2026 00:07
1 362
0
3
ማንቼስተር ሲቲ ነጥብ ጣለ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኤቨርተን እና ማንቼስተር ሲቲ 3 ለ 3 አቻ ተለያይተዋል።

ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ የኤቨርተንን ግቦች ባሪ (2) እና ኦብሬን አስቆጥረዋል።

የማንቼስተር ሲቲን ግቦች ደግሞ ጄርሚ ዶኩ (2) እና ኧርሊንግ ሃላንድ ከመረብ አሳርፈዋል።

አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ያለው ማንቼስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል በ5 ነጥቦች ርቆ ይገኛል።

ማንቼስተር ሲቲ በጨዋታው ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሶስት ለማጥበብ የነበረውን እድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
👍 10
👎 1
Смотреть все посты