Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 507
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 127
ER
Общий
5.09%
Суточный
4.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 901 поста
Смотреть все посты
Пост от 11.07.2026 00:02
1
0
0
ስፔን ቤልጂየምን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ስፔን ቤልጂየምን 2 ለ 1 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።

የስፔንን ግቦች ፋቢያን ሩዪዝ እና ሚኬል ሞሪኖ አስቆጥረዋል።

ስፔን በግማሽ ፍጻሜው ከፈረንሳይ ጋር ትገናኛለች፡፡
Пост от 10.07.2026 19:07
410
0
2
ኢትዮጵያ ቡና ገብረመድን ሀይሌን የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ቡና ገብረመድን ሀይሌን የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን አስታውቋል፡፡

አሰልጣኝ ገብረድህን ሀይሌ በሁለት ዓመት የኮንትራት ውል ነው የኢትዮጵያ ቡና ዋና አሰልጣኝ ለመሆን የተስማማው፡፡

ኢትዮጵያ ቡና ለቀድሞው ተጫዋች እና አንጋፋው አሰልጣኝ የእንኳን ደህና መጣህ መልዕክቱን ያስተላለፈ ሲሆን መልካም የአሰልጣኝነት ዘመን እንዲሆንለት ተመኝቷል፡፡
Пост от 10.07.2026 19:07
1
0
0
ጆርጅ ጄሱስ የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከአሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ጋር የተለያየው የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ጆርጅ ጄሱስን አሰልጣኝ አድርጎ ሾሟል።

የአል ናስር የቀድሞ አሰልጣኝ ጆርጅ ጄሱስ የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድንን እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ ለማሰልጠን የሚያስችላቸውን ውል ተፈራርመዋል።

በፈረንጆቹ 2030 የሚደረገውን የዓለም ዋንጫ ውድድር ፖርቹጋል፣ ስፔን እና ሞሮኮ በጋራ እንደሚያዘጋጁት ይታወቃል።

የ71 ዓመቱ አሰልጣኝ ጆርጅ ጄሱስ ከአልናስር በተጨማሪ ቤኔፊካ፣ ስፖርቲንግ ሊዝበን፣ ፌነርባቼ እና አል ሂላልን ጨምሮ በርካታ ክለቦችን ማሰልጠናቸው ይታወሳል፡፡

ፖርቹጋል በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ላይ በስፔን ተሸንፋ ከውድድሩ መሰናበቷ ለአሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከቡድኑ ጋር መለያየት ምክንያት መሆኑ አይዘነጋም፡፡

ፖርቹጋል በዓለም ዋንጫው ከኮሎምቢያ እና ዴሞክራቲክ ኮንጎ ጋር አቻ ስትለያይ ኡዝቤኪስታን እና ክሮሽያን ማሸነፍ ችላለች፡፡

የ52 ዓመቱ አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ በ2025 ከፖርቹጋል ጋር የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ዋንጫን ማሸነፋቸው ይታወሳል።
Пост от 10.07.2026 13:38
1
0
0
ስፔን ከቤልጂዬም፣ ተጠባቂው ጨዋታ…

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ይደረጋል፡፡

ምሽት 4 ሰዓት ላይ የአንድ ጊዜ የመድረኩ አሸናፊ ስፔን ከቤልጂዬም ጋር የምታደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ስፔን በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ፖርቹጋልን እንዲሁም ተጋጣሚዋ ቤልጂዬም ደግሞ አዘጋጇን ሀገር አሜሪካን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡

የ2010 የመድረኩ ሻምፒዮን ስፔን በድጋሚ በመድረኩ ለመንገስ የምታደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ወደ ሜዳ የምትገባ ይሆናል፡፡

በፈረንጆቹ 2018 ወርቃማ ትውልዷን ሳትጠቀም የቀረችው ቤልጂዬም በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ እስከ የት ድረስ ትጓዛለች የሚለው ተጠባቂ ነው፡፡

በስፔን ብሔራዊ ቡድን በኩል በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ 4 ግቦችን ያስቆጠረው ሚኬል ኦያርዛባል እና ወጣቱ ኮከብ ላሚን ያማል በዛሬው ጨዋታ ይጠበቃሉ፡፡

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሸናፊ በግማሽ ፍጻሜው ከፈረንሳይ ጋር የሚጫወት ይሆናል፡፡
Пост от 10.07.2026 01:02
957
0
3
ፈረንሳይ ሞሮኮን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።

በቦስተን ጁሌት ስታዲየም በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የፈረንሳይን ግቦች ኪሊያን ምባፔ እና ኦስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል።

በመጀመሪያው አጋማሽ ፍጹም ቅጣት ምት የሳተው ምባፔ በዚህ ዓለም ዋንጫ ከሊዮኔል ሜሲ እኩል 8 ግቦች በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን በጋራ እየመራ ይገኛል።

ፈረንሳይ በሦስት ተከታታይ የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ላይ የፍጻሜ ተፋላሚ ለመሆን በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትገናኛለች፡፡
Пост от 09.07.2026 16:29
1 364
0
1
ኒውካስል ዩናይትድ ሻን ስቱርን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኒውካስል ዩናይትድ ሻን ስቱርን
ከአያክስ አምስተርዳም ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ኒውካስል ዩናይትድ ለ18 ዓመቱ ኔዘርላንዳዊ አማካይ 20 ሚሊየን ፓውንድ እና እየታየ የሚጨመር 3 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ በማድረግ ተጫዋቹን የግሉ አድርጓል፡፡

ሻን ስቱርን በእንግሊዙ ክለብ ኒውካስል ዩናይትድ ቤት ለአምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

ተጫዋቹ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለአያክስ አምስተርዳም 24 ጨዋታዎችን አድርጎ አንድ ግብ ብቻ አስቆጥሯል፡፡

ኒውካስል ዩናይትድ ቀደም ሲል በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ባዙማን ቱሬን ከሆፈንሄይም ማስፈረሙ አይዘነጋም፡፡

በሌላ በኩል ኒውካስል ዩናይትድ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት አንቶኒ ጎርደን ለባርሴሎና እንዲሁም ሳንድሮ ቶናሊን ለቶተንሃም ሆትስፐር አሳልፎ መስጠቱ ይታወቃል፡፡

በተጨማሪም ኒውካስል ዩናይትድ ብራዚላዊውን የቡድኑን አምበል ብሩኖ ጎማሬሽን የሚያጣበት ዕድል ሰፊ መሆኑ በስፋት እየተዘገበ ሲሆን ተጫዋቹ ክለቡን መልቀቅ እንደሚፈልግም አሳውቋል፡፡

በዚህም ክለቡ ቡድኑን ለማጠናከር በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል፡፡

በመልካም ፈቃዱ
Пост от 09.07.2026 13:15
144
0
1
ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 0 በማሸነፍ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል፡፡

በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ የወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ኮንኮኒ ሀፊዝ እና በየነ ባንጃ አስቆጥረዋል፡፡

ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡

የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ዋንጫ ማሳካት የሚችልበትን ዕድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡
Смотреть все посты