Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
12.0K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
39 091
Сегодня
-9
Просмотров на пост
Всего
2 527
ER
Общий
5.98%
Суточный
3.8%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 11 976 постов
Смотреть все посты
Пост от 21.02.2026 20:25
82
0
1
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ሲሞን ፒተር፣ ሁዘይፋ ሻፊ እና ሳምሶን ቹቹ አስቆጥረዋል፡፡

ፋሲል ከነማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ታምራት እያሱ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

የአዳማ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቢንያም አይተን (በፍጹም ቅጣት ምት) ከመረብ አሳርፏል፡፡

አስቀድሞ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3 እንዲሁም ባህርዳር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 21.02.2026 19:58
292
0
2
ቼልሲ እና በርንሌይ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቼልሲ እና በርንሌይ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

የቼልሲን ግብ ጇ ፔድሮ በመጀመሪያው አጋማሽ ሲያስቆጥር ፍሌሚንግ የበርንሌይን የአቻነት ግብ በመጨረሻ ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ብራይተን ብሬንትፎርድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ አስቶንቪላ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር 1 አቻ ተለያይቷል፡፡

የሊጉ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ ምሽት 2 ሰዓት 30 ላይ ዌስትሃም ዩናይትድ ከቦርንማውዝ እንዲሁም ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ሲቲ ከኒውካስል ዩናይትድ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Изображение
Изображение
Пост от 21.02.2026 18:10
221
0
1
በፕሪሚየር ሊጉ አዲስ ታሪክ የጻፈው ጀምስ ሚልነር…

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የብራይተኑ ተጫዋች ጀምስ ሚልነር በፕሪሚየር ሊጉ ብዙ ጨዋታዎችን ያደረገ ተጫዋች በሚል በሊጉ የታሪክ መዝገብ ስሙን አስፍሯል፡፡

ሚልነር በአሁኑ ሰዓት ክለቡ ብራይተን ከብሬንትፎርድ ጋር እያደረገው በሚገኘው የ27ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ላይ በቋሚነት በመሰለፍ 654ኛ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታውን አድርጓል፡፡

በዚህም መሰረት የ40 ዓመቱ እንግሊዛዊ የዛሬውን ጨዋታ ጨምሮ በብራይተን፣ ማንቼስተር ሲቲ፣ ሊቨርፑል፣ ኒውካስል ዩናይትድ፣ አስቶን ቪላ እና ሊድስ ዩናይትድ በአጠቃላይ በ654 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል፡፡

ይህን ተከትሎም በሊጉ 653 ጨዋታዎችን በማድረግ ቀዳሚ የነበረውን የቀድሞ የማንቼስተር ሲቲ፣ አስቶን ቪላ እና ዌስትብሮሚች ተጫዋች ጋሪዝ ባሪ ክብረወሰን በመብለጥ አዲስ ታሪክ ጽፏል፡፡

በፈረንጆቹ 2002 የመጀመሪያ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታውን በ16 ዓመቱ ለሊድስ ዩናይትድ ያደረገ ሲሆን፥ በወቅቱ በሊጉ መሰለፍ የቻለ 2ኛው በእድሜ ትንሹ ተጫዋች ነበር፡፡

ከሊቨርፑል ጋር አንድ የሻምፒየንስ ሊግ እና አንድ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን ያሳካው ጀምስ ሚልነር ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ሁለት ጊዜ የሊጉ ባለክብር መሆን ችሏል፡፡

ጀምስ ሚልነር 27ኛ ሳምንቱ ላይ በሚገኘው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጨማሪ ጨዋታዎችን በማድረግ ቁጥሩን ከዚህም ከፍ የማድረግ እድል አለው፡፡

የቀድሞው የማንቼስተር ዩናይትድ ተጫዋች ሪያን ጊግስ (632) እንዲሁም ፍራንክ ላምፓርድ (609) በሊጉ በርካታ ጨዋታዎችን በማድረግ ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡

በኃይለማርያም ተገኝ
Изображение
Изображение
Пост от 21.02.2026 17:23
205
0
1
ወላይታ ድቻ መቻልን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወላይታ ድቻ መቻልን 4 ለ 3 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ግቦች ቴዎድሮስ ሀይለማሪያም፣ ካርሎስ ዳምጠው እና ዮናታን ኤልያስ (2) አስቆጥረዋል፡፡

መቻልን ከሽንፈት ያልታደጉ ግቦችን ቸርነት ጉግሳ(2) እና በረከት ደስታ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ባህርዳር ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

የባህርዳር ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ግርማ ዲሳሳ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥሯል፡፡

የሊጉ ጨዋታዎች ሲቀጥሉ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ኢትዮጵያ መድን ከአዳማ ከተማ በተመሳሳይ አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 19.02.2026 01:06
1 907
0
2
አርሰናል ከዎልቭስ ጋር አቻ ተለያየ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ከሜዳው ውጭ ከዎልቭስ ጋር ባደረገው ጨዋታ 2 ለ 2 አቻ ተለያይቷል።

የሊጉ መሪ አርሰናል በቡካዮ ሳካ እና ሂንካፒ ግቦች 2 ለ ዐ ሲመራ ቢቆይም፥ በሊጉ መጨረሻ ደረጃ ላይ ለሚገኘው ዎልቭስ ቡዪኖ እና ካላፊዮሪ (በራሱ ላይ) ባስቆጠሯቸው ግቦች ሁለቱ ቡድኖች ነጥብ ተጋርተዋል።

ውጤቱን ተከትሎ 27 ጨዋታዎችን ያደረገው አርሰናል በ58 ነጥብ ሊጉን ሲመራ፥ 26 ጨዋታዎችን ያደረገው ማንቼስተር ሲቲ በ5 ነጥብ ልዩነት ይከተላል።
Изображение
🙏 10
👎 3
Пост от 18.02.2026 11:11
1 684
0
2
የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 16 ውስጥ ለመግባት የሚደረጉ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ይካሄዳሉ፡፡

በዚህም መሰረት ካራባግ ከኒውካስል ዩናይትድ፣ ቦዶ ግሊምት ከኢንተርሚላን፣ ክለብ ብሩዥ ከአትሌቲኮ ማድሪድ እንዲሁም ኦሎምፒያኮስ ከባየር ሊቨርኩሰን ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ትናንት በተደረጉ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ ቤንፊካን 1 ለ 0፣ ፒኤስጂ ሞናኮን 3 ለ 2፣ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ አታላንታን 2 ለ 0 እንዲሁም ጋላታሳራይ ጁቬንቱስን 5 ለ 2 አሸንፈዋል።
👎 1
Пост от 18.02.2026 09:45
1 831
0
2
ዎልቭስ ከአርሰናል…

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ31ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ወደ ሞልኒው ስታዲየም በማቅናት ከዎልቭስ ጋር ይጫወታል፡፡

የሊጉ መሪ አርሰናል ምሽት 5 ሰዓት ወራጅ ቀጣና ላይ ከሚገኘው ወልቭስ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማስፋት ቀደም ብሎ የቤት ስራውን መወጣት ይጠበቅበታል፡፡

በአርሰናል በኩል የክንፍ ተከላካዮቹ ካላፊዎሪ እና ቤን ኋይት ለዛሬው ጨዋታ ብቁ መሆናቸውን የጠቀሱት የቡድኑ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ÷ ማርቲን ኦዴጋርድ እና ካይ ሀቨርትዝ ለእሁዱ የሰሜን ደርቢ ፍልሚያ ይደርሳሉ ብለዋል።

የዛሬው የዎልቭስ እና የአርሰናል ጨዋታ በፈረንጆቹ መጋቢት 21 ይካሄዳል ተብሎ በሊጉ መርሐ ግብር የወጣለት ቢሆንም፤ ለካራባኦ ካፕ ፍጻሜ የደረሰው አርሰናል ባለበት ጨዋታ ምክንያት ነው ዛሬ የሚካሄደው።

መድፈኞቹ በ57 ነጥብ ከተከታያቸው ማንቼስተር ሲቲ አራት ነጥብ በመብለጥ ሊጉን እየመሩ ይገኛሉ፡፡
Смотреть все посты