Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.6K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 633
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 302
ER
Общий
5.48%
Суточный
3.8%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 592 постов
Смотреть все посты
Пост от 06.06.2026 19:58
127
0
1
ዋሊያዎቹ የማላዊ አቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታ የማላዊ ብሄራዊ ቡድንን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የዋሊያዎቹን የአሸናፊነት ግብ ፍጹም ጥላሁን አስቆጥሯል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች የመልስ ጨዋታቸውን በመጪው ማክሰኞ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም ያደርጋሉ፡፡
Пост от 06.06.2026 15:53
1
0
0
የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል በሮምና ሞስኮ...

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሳምንቱ በሮም እና በሞስኮ በተካሄዱ ውድድሮች ላይ በበላይነት አጠናቅቀዋል።

በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደውና በዓለም አትሌቲክስ የኤፍ ደረጃ በተሰጠው የ2026 የዝናሜንስኪ ወንድማማቾች መታሰቢያ የአትሌቲክስ ውድድር የኢትዮጵያ አትሌቶች የበላይነት በመያዝ ውድድሩን በታላቅ ድል ማጠናቀቅ ችለዋል።

በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ኃይሎም 1ኛ በመሆን ማጠናቀቅ ስትችል÷ አትሌት ሳሮን በርሃ ደግሞ 2ኛ ደረጃን ይዛለች።

አትሌት ደስታ ታደለ 5ኛ፣ አትሌት ሲፈን ዳገታ 8ኛ ፣ አትሌት በሻቱ ጌታ 9ኛ እና አትሌት ቤተልሔም ሙላት 15ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።

የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት ፈንታዬ ጫኔ በአንደኝነት ስታሸንፍ÷ አትሌት ቤተልሔም ኦላና 2ኛ ወጥታለች።

አትሌት ሰላማዊት ሻምበል 4ኛ እንዲሁም አትሌት ትርንጎ ታዳለ 6ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።

በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ብርቱካን ገዳሙ ፈጣን ፉክክር በተደረገበት የሩጫ መድረክ ርቀቱን 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።

በ800 ሜትር አትሌት ሀብታም ገበየሁ 6ኛ ደረጃን መያዝ ችላለች።

በወንዶች የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ አትሌት እዮብ ስመኝ በበላይነት ጨርሷል፡፡

በዚሁ ውድድር ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሽመልስ ንጉሴ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ፈፅሟል።

የወንዶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ዲንቃ ፍቃዱ 1ኛ በመሆን ሲያሸንፍ... 👇
https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid02sMcxhRPHmLEdS8w39VV21zKhPgdyz82qJEpA3kQWcYNHXg8q7c5frwVQpV9zQQEVl
Пост от 06.06.2026 10:45
84
0
1
ኢትዮጵያ ከማላዊ…

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዛሬው ዕለት ከማላዊ ብሔራዊ ቡድን ጋር የወዳጅነት ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም የሚካሄድ ይሆናል፡፡

ከማላዊ ብሔራዊ ቡድን ጋር የሚካሄደው ሁለተኛው ዙር የወዳጅነት ጨዋታ ደግሞ የፊታችን ማክሰኞ ይደረጋል፡፡
Пост от 06.06.2026 10:41
127
0
2
638 አትሌቶች የሚሳተፉበት የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር…

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

መነሻው እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ውድድር ላይ በወንዶች 455፣ በሴቶች ደግሞ 183 በድምሩ 638 አትሌቶች የሚሳተፉ ይሆናል፡፡

ውድድሩ በስዊድን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችን ለመምረጥ እና ተተኪዎች ለማፍራት ያለመ ነው።

በውድድሩ ላይ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ደረጃ ይዘው የሚያጠናቅቁ አትሌቶች የገንዘብ፣ የሜዳልያና የዋንጫ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተጠቁሟል፡፡

የዘንድሮው ውድድር ተሳታፊዎች ብዛት ከአምናው ጋር ሲነጻጸር የ434 አትሌቶች ጭማሪ ማሳየቱ ነው የተገለጸው፡፡
Пост от 05.06.2026 16:35
890
0
2
ላሚን ያማል የስፔን ላሊጋ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሆነ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው የፊት መስመር ተጫዋች ላሚን ያማል የ2025/26 የውድድር ዓመት የስፔን ላሊጋ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል፡፡

ላሚን ያማል በውድድር ዓመቱ ከባርሴሎና ጋር የስፔን ላሊጋ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል፡፡

ተጫዋቹ በላሊጋው ለባርሴሎና ባደረጋቸው 28 ጨዋታዎች 16 ግቦችን አስቆጥሮ 11 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡

የባርሴሎናው አሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ የስፔን ላሊጋ የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ተብለው መመረጣቸው አይዘነጋም፡፡
👏 3
🙏 1
Пост от 05.06.2026 15:51
1 032
0
1
ቶተንሃም ሆትስፐር አንዲ ሮበርትሰንን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቶተንሃም ሆትስፐር ስኮትላንዳዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች አንዲ ሮበርትሰን ወደ ስብስቡ መቀላቀሉን ይፋ አድርጓል፡፡

አንዲ ሮበርትሰን ከ9 ዓመታት የአንፊልድ ቆይታ በኋላ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከሊቨርፑል ጋር መለያየቱ ይታወሳል፡፡

ይህን ተከትሎም የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር የ32 ዓመቱን ተጫዋች በነጻ ዝውውር የግሉ አድርጓል፡፡

የቶተንሃም አሰልጣኝ ሮቤርቶ ዲዘርቢ አንዲ ሮበርትሰን የሚያደንቁት ተጫዋች መሆኑን ጠቅሰው÷ በቡድናቸው ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ እንደሚያመጣ አብራርተዋል፡፡

ስኮትላንዳዊው የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች አንዲ ሮበርትስን በሊቨርፑል ቆይታው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን ጨምሮ በርካታ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በሊጉ 17ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
Пост от 05.06.2026 14:03
249
0
2
የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማሕበር የዓመቱ ምርጥ እጩዎች ይፋ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማሕበር የ2025/26 የውድድር ዓመት የዓመቱ ምርጥ እጩዎች ይፋ ሆነዋል፡፡

በዚህም አርሰናል ሦስት ተጫዋቾችን በእጩነት በማስመረጥ ቀዳሚ ሲሆን÷ ጋብሬል ማጋሌሽ፣ ዴቪድ ራያ እና ዴክላን ራይስ በእጩነት ቀርበዋል፡፡

የመድፈኞቹ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ በውድድር ዓመቱ በ19 ጨዋታዎች ግብ ሳይቆጠርበት በመውጣት የወርቅ ጓንቱን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

ጋብሬል ማጋሌሽ እና ዴክላን ራይስ አርሰናል የሊጉን ዋንጫ እንዲያሳካ ትልቁን አስተዋጽኦ ካበረከቱ ተጫዋቾች መካከል ተጠቃሽ ናቸው፡፡

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ያሸነፈው የማንቼስተር ዩናይትድ የመሐል ሜዳ ተጫዋች ብሩኖ ፈርናንዴዝ ሌላኛው በእጩ ዝርዝር ውስጥ የተካተተ ተጫዋች ነው፡፡

ብሩኖ 21 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻቶ በማቀበል በአንድ የውድድር ዓመት በሊጉ በርካታ ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን የማቀብል ክብረ ወሰኑን የግሉ ማድረጉ አይዘነጋም፡፡

በ27 ግቦች የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን የወርቅ ጫማውን ያሸነፈው ኤርሊንግ ብራውት ሀላንድ እና ረያን ሼርኪ ከማንቼስተር ሲቲ በእጩነት ቀርበዋል፡፡
Изображение
👍 3
Смотреть все посты