Каталог каналов Каналы в закладках Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
18.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
38 040
Сегодня
-13
Просмотров на пост
Всего
2 034
ER
Общий
4.94%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 18 916 постов
Смотреть все посты
Пост от 03.04.2026 17:22
1
0
0
ድሬዳዋ ከተማ እና ፋሲል ከነማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ እና ፋሲል ከነማ አቻ ተለያይተዋል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ 0 ለ 0 ተለያይተዋል፡፡

በዚሁ ስታዲየም የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ መቻል ከምድረ ገነት ሽረ ይገናኛሉ፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው በሌላ የሊጉ ጨዋታ አርባ ምንጭ ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 1 እየመራ ይገኛል፡፡

በዚሁ ስታዲየም አስቀድሞ በተካሄደ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ባሕር ዳር ከተማ ያለምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 03.04.2026 15:26
237
0
1
አሰልጣኝ ጅናሮ ጋቱሶ ከጣሊያን ብሔራዊ ቡድን ጋር ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሰልጣኝ ጅናሮ ጋቱሶ ከጣሊያን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነት መልቀቃቸው ይፋ ተደርጓል፡፡

አሰልጣኙ የጣሊያን ብሔራዊ ቡድንን ወደ 2026 ዓለም ዋንጫ ማሳለፍ ባለመቻላቸው ከኃላፊነታቸው ለቅቀዋል፡፡

ጣሊያን ለሦስተኛ ተከታታይ ጊዜ ከዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ መሆኗ ይታወቃል፡፡

አሰልጣኝ ጅናሮ ጋቱሶ የጣሊያን ብሔራዊ ቡድንን በ2025 የተረከቡ ሲሆን÷ 8 ጨዋታዎችን በማድረግ 6 ድል፣ 1 አቻ እና 1 ሽንፈት አስመዝግበዋል፡፡

ጅናሮ ጋቱሶ ጣሊያን ለመጨረሻ ጊዜ በፈረንጆቹ 2006 የዓለም ዋንጫን ስታሳካ በተጫዋችነት የስብስቡ አካል እንደነበር ይታወሳል፡፡

በትናንትናው ዕለት የጣሊያን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ጋብሪኤል ግራቪና እና የብሔራዊ ቡድኑ መሪ ጂያንሉጂ ቡፎን ከኃላፊነት መልቀቃቸው አይዘነጋም፡፡

በወንድማገኝ ጸጋዬ
Пост от 03.04.2026 15:14
279
0
1
ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ባሕር ዳር ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ባሕር ዳር ከተማ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ 0 ለ 0 ተለያይተዋል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከአርባ ምንጭ ከተማ ጋር ይገናኛል።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ መቻል ከምድረ ገነት ሽረ ይገናኛሉ፡፡
Пост от 03.04.2026 14:54
378
0
1
አሊሰን ቤከር ለወራት ከሜዳ ይርቃል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብራዚላዊው የሊቨርፑል ግብ ጠባቂ አሊሰን ቤከር ለወራት ከሜዳ እንደሚርቅ ክለቡ ይፋ አድርጓል፡፡

የ33 ዓመቱ ግብ ጠባቂ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ነው ከሜዳ እንደሚርቅ የተገለጸው፡፡

አሊሰን ቤከር የውድድር ዘመኑ መጨረሻ አካባቢ ወደ ሜዳ ሊመለስ እንደሚችል አሰልጣኝ አርነ ስሎት ገልጸዋል፡፡

አሊሰን ቤከር በዚህ የውድድር ዓመት በሁሉም ውድድሮች ለሊቨርፑል 31 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ መጫወት ችሏል፡፡
Пост от 03.04.2026 13:56
599
0
1
ኢንዞ ፈርናንዴዝ ከቼልሲ ስብስብ ውጪ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቼልሲ የአማካይ ስፍራ ተጫዋች ኢንዞ ፈርናንዴዝ ከቡድኑ ስብስብ ውጪ ሆኗል፡፡

ኢንዞ ፈርናንዴዝ ከቡድኑ ስብስብ የተቀነሰው በቅርቡ በሰጠው አስተያየት መሆኑን የክለቡ አሰልጣኝ ሊያም ሮሴኒየር ገልጸዋል፡፡

በዚህም ኢንዞ ፈርናንዴዝ ከነገው የኤፍ ኤ ዋንጫ እና በቀጣይ ሳምንት ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ከሚደረገው ተጠባቂ ጨዋታ ውጪ መሆኑን አረጋግጠዋል።
Изображение
👍 2
Пост от 03.04.2026 09:30
958
0
2
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

ቀን 7 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በሚጀመረው የሊጉ መርሐ ግበር ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ባሕር ዳር ከተማ ይገናኛሉ።

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከአርባ ምንጭ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋል።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ድሬዳዋ ከተማ ከፋሲል ከነማ ሲገናኝ አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ መቻል እና ምድረ ገነት ሽረ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ሊጉን ሲዳማ ቡና በ45 ነጥብ ሲመራው ሀዋሳ ከተማ 40፣ ነገሌ አርሲ 38 እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ37 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡

የሊጉን ኮከብ ግብ አስቆጣሪነት አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና እንዲሁም አዲስ ግደይ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተመሳሳይ በ10 ግብ እየመሩት ነው፡፡
Пост от 03.04.2026 09:05
910
0
2
የተረሳው የብራዚል ወርቃማው ልጅ አድሪያኖ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእግር ኳስ ችሎታው ዓለምን ያነጋገረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር የብራዚል ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ተጫዋች አድሪያኖ፡፡ አድሪያኖ እግር ኳስን የጀመረው በሀገሩ ክለብ ፍላሚንጎ ሲሆን በፈረንጆቹ 2002 የጣሊያኑን ክለብ ኢንተር ሚላን ተቀላቅሏል። ለኢንተር ሚላን 8 ጨዋታዎችን ካደረገ በኋላ ለሁለት የውድድር ዓመት ለፓርማ እና ፊዮሬንቲና በውሰት ውል ተጫውቶ አሳልፏል፡፡…

https://www.fanamc.com/archives/312375
Изображение
Смотреть все посты