Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
12.0K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
38 755
Сегодня
-20
Просмотров на пост
Всего
2 254
ER
Общий
5.28%
Суточный
3.8%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 12 016 постов
Смотреть все посты
Пост от 07.03.2026 18:39
681
0
1
ግራቨንበርች በሊቨርፑል የሚያቆየውን የረጅም ጊዜ ውል ተፈራረመ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኔዘርላንዳዊው የመሐል ሜዳ ተጫዋች ግራቨንበርች በሊቨርፑል የሚያቆየውን የረዥም ጊዜ ውል ተፈራርሟል።

ግራቨንበርች በመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል እስከ ፈረንጆቹ 2032 የሚያቆየውን ተጨማሪ የስድስት ዓመት ውል መፈራረሙን ክለቡ ይፋ አድርጓል።

ግራቨንበርች ውሉን ካራዘመ በኋላ በሰጠው አስተያየት በሚቀጥሉት የወድድር ዓመታት ከሊቨርፑል ጋር ተጨማሪ ዋንጫ ማሸነፍ እፈልጋለሁ በማለት ተናግሯል።

የ23 ዓመቱ ተጫዋች በዚህ የውድድር ዘመን ለሊቨርፑል በፕሪሚየር ሊግ ባደረጋቸው 27 ጨዋታዎች 4 ግቦችን አስቆጥሮ 3 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አቀብሏል።
Изображение
Пост от 07.03.2026 17:33
753
0
1
አርሰናል ማንስፊልድ ታውንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ 5ኛ ዙር የኤፍ ኤ ዋንጫ ጨዋታ አርሰናል ማንስፊልድ ታውንን 2 ለ 1 አሸንፏል።

ቀን 9:15 ሰዓት ላይ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ በሊግ አንድ እየተሳተፈ የሚገኘውን ማንስፊልድ ታውን የገጠመው አርሰናል የማሸነፊያ ግቦቹን ኖኒ ማዱዌኬ እና ኤበሪቼ ኤዜ አስቆጥረዋል።

በጨዋታው ጠንካራ ፉክክር ያሳዩት የማንስፊልድ ታውንን ብቸኛ ግብ ደግሞ ዊል ኢቫንስ ከመረብ ኣሰርፏል።

የኤፍ ኤ ዋንጫ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ኒውካስል ዩናይትድ እና ማንቼስተር ሲቲ በሴንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም ሲገናኙ÷ ቼልሲ ከሜዳው ውጪ ሬክሳምን ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ ይገጥማል።
Изображение
Изображение
Изображение
👍 2
👏 1
Пост от 07.03.2026 10:58
1 044
0
1
በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ 5ኛ ዙር ዛሬ ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ 5ኛ ዙር የኤፍ ኤ ዋንጫ ዛሬ ኒውካስል ዩናይትድ ከማንቼስተር ሲቲ፣ አርሰናል ከማንስፊልድ ታውን እንዲሁም ቼልሲ ከሬክሳም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ማንቼስተር ሲቲ ከሜዳው ውጪ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም በማቅናት ምሽት 5 ሰዓት ላይ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በዚህ ዓመት ብቻ ለ5ኛ ጊዜ የሚገናኙ ሲሆን÷ በቅርቡ በተገናኙበት የካራባኦ ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ በደርሶ መልስ አሸንፎ ለፍጻሜ መድረሱ ይታወሳል፡፡

ለአራቱም ዋንጫዎች እየተፎካካረ የሚገኘው ሲቲ ሩብ ፍጻሜውን ለመቀላቀል በሚያደርገው ጉዞ ከኒውካስል ጠንካራ ፈተና ይጠብቀዋል፡፡

ቀደም ብሎ በተመሳሳይ ለአራቱም ዋንጫዎች እየተፋለሙ የሚገኙት መድፈኞቹ በዋን ኮል ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ከ15 ላይ ከማንስፊልድ ታውን ይጫወታሉ፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በኤፍ ኤ ዋንጫ ሲገናኙ የዛሬው ከ95 ዓመት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ሲሆን÷ አርሰናል በመድረኩ በእንግሊዝ 3ኛው የሊግ እርከን ከሚገኙ ቡድኖች ያደረጋቸውን ያለፉት 15 ጨዋታዎች በሙሉ አሸንፏል፡፡

ቼልሲ በበኩሉ ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ ወደ ሩብ ፍጻሜው ለመቀላቀል ከሬክሳም ጋር የሚጫወት ይሆናል፡፡

በአቤል ነዋይ
Изображение
Изображение
Изображение
👍 4
Пост от 06.03.2026 15:50
1 705
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ የትኬት ዋጋ ጭማሪ አደረገ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ለ2026/27 የውድድር ዘመን የስታዲየም መግቢያ ትኬት ዋጋ ላይ ጭማሪ አድርጓል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች የስታዲየም መግቢያ ትኬት ላይ 5 በመቶ ጭማሪ ማድረጉ ነው የተገለጸው፡፡

ክለቡ የትኬት ዋጋ ላይ ጭማሪ ያደረገው በቀጣይ በእግር ኳስ መሰረተ ልማት ላይ ለሚሰሩ ስራዎች ገቢን ለማሳደግ መሆኑም ተመላክቷል፡፡
Изображение
Пост от 05.03.2026 18:12
1 858
0
2
ድሬዳዋ ከተማ መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ22ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ መቐለ 70 እንደርታን 2 ለ 1 አሸንፏል።

ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የድሬዳዋ ከተማን ግቦች አቡዱልሰላም የሱፍ እና አብዲሳ ጀማል ሲያስቆጥሩ÷ የመቐለ 70 እንደርታን ግብ ተመስገን ተስፋዬ ከመረብ አሳርፏል።

በተመሳሳይ ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው የሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ከተማ ጨዋታ በአንድ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።

በጨዋታው የሀድያ ሆሳዕና ግብ ታሪኩ ፀደቀ ሲያስቆጥር የአዳማ ከተማን ግብ ደግሞ አህመድ ሁሴን ማስቆጠር ችሏል።
Пост от 05.03.2026 09:33
1 996
0
2
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ22ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሀድያ ሆሳዕና ከአዳማ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ መቐለ 70 እንደርታ ከድሬዳዋ ከተማ ይገናኛሉ፡፡
Пост от 05.03.2026 01:19
2 120
0
3
ማንቼስተር ዩናይትድ በኒውካስል ዩናይትድ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ29ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ በኒውካስል ዩናይትድ 2 ለ 1 ተሸንፏል።

የኒውካስል ዩናይትድን ግቦች ጎርደን (በፍጹም ቅጣት ምት) እና ዊሊያም ኦሱላ ሲያስቆጥሩ፥ ካሴሚሮ የማንቼስተር ዩናይትድን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።

በጨዋታው ጃኮብ ራምሴ ከኒውካስል በኩል በመጀመሪያው አጋማሽ መገባደጃ ላይ በቀይ ካርድ ተሰናብቷል።
😢 2
Смотреть все посты