Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
16.6K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
39 565
Сегодня
-5
Просмотров на пост
Всего
1 672
ER
Общий
4.27%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 16633 постов
Смотреть все посты
Пост от 20.01.2026 22:42
1 166
0
1
ማንቼስተር ሲቲ በቦዶ ግሊምት 3 ለ 1 ተሸነፈ አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ7ኛ ዙር መርሐ ግብር ከሜዳው ውጭ የኖርዌዩን ቦዶ ግሊምት የገጠመው ማንቼስተር ሲቲ 3 ለ 1 ተሸንፏል፡፡ ካስፐር ሆግ (2) እንዲሁም ጄንስ ሀውጅ ባስቆጠሯቸው ግቦች በቦዶ ግሊምት 3 ለ 0 ሲመሩ የቆዩት ሲቲዎች በባዶ ከመሸነፍ የዳኑበትን ብቸኛ ግብ ራያን ሼርኪ ከመረብ አሳርፏል፡፡ በማንቼስተር ሲቲ በኩል አማካዩ ሮድሪ በሁለት ቢጫ ካርድ 62ኛው ደቂቃ ላይ ከሜዳ ተሰናብቷል። ቀደም ብሎ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 በተደረገው የዕለቱ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ክለብ ብሩጅ ካይራት አልማቲን 4 ለ 1 አሸንፏል፡፡ የሻምፒየንስ ሊጉ የ7ኛ ዙር መርሐ ግብር ቀጥለው ሲደረጉ በመድረኩ በዚህ የውድድር ዓመት በብቸኝነት ሁሉንም ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አርሰናል ምሽት 5 ሰዓት ኢንተር ሚላንን ይገጥማል። ሪያል ማድሪድ ከሞናኮ፣ ስፖርቲንግ ሊዝበን ከፒኤስጂ፣ ቶተንሃም ሆትስፐር ከቦሩሺያ ዶርትመንድ፣ ቪያሪያል ከአያክስ አምስተርዳም እንዲሁም ኦሎምፒያኮስ ከባየር ሊቨርኩሰን በተመሳሳይ 5 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው።
Пост от 20.01.2026 20:22
1 294
0
0
መቐለ 70 እንደርታ ኢትዮ ኤሌክትሪክን አሸነፈ አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ16ኛ ሳምንት መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 1 አሸነፈ፡፡ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጊት ጋትኩት እና ፍፁም አለሙ የመቐለ 70 እንደርታን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡ ሀብታሙ ሸዋለም ኢትዮ ኤሌክትሪክን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡
Пост от 20.01.2026 17:08
1 371
0
2
ወላይታ ድቻ እና ባህርዳር ከተማ አቻ ተለያዩ አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2018 ሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ እና ባህርዳር ከተማ አቻ ተለያይተዋል። ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው ጨዋታ ያለምንም ግብ ተጠናቅቋል። አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ ሲካሄድ መቐለ 70 እንደርታ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ይገናኛሉ።
Пост от 20.01.2026 16:38
1 424
0
2
ማርሴ ኢታን ንዋኔሪን ከአርሰናል በውሰት ለማዘዋወር ተስማማ አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፈረንሳዩ ክለብ ኦሊምፒክ ማርሴ የአርሰናሉን አማካይ ኢታን ንዋኔሪ በውሰት ለማዘዋወር ተስማምቷል፡፡ የ18 ዓመቱ እንግሊዛዊ እስከ ውድድር ዓመቱ መጨረሻ በማርሴ የሚያቆየውን ውል ለመፈረም በነገው ዕለት ወደ ፈረንሳይ እንደሚያቀና ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡ ባሳለፍነው ክረምት እስከ ፈረንጆቹ 2030 በኤሚሬትስ የሚያቆየውን ውል የፈረመው ተጫዋቹ በዚህ የውድድር ዓመት በመድፈኞቹ ቤት በቂ የመጫወት እድል ለማግኘት ተቸግሯል፡፡ ባለፈው የውድድር ዓመት በሁሉም ውድድሮች 37 ጨዋታዎችን ማድረግ የቻለ ሲሆን፥ በዚህ የውድድር ዓመት የመሰለፍ እድል ያገኘው በ12 ጨዋታዎች ላይ ብቻ ነው፡፡ ይህን ተከትሎ ተጫዋቹ የተሻለ የመሰለፍ እድል ለማግኘት ወደ ማርሴ እንደሚያቀና ታውቋል፡፡
Пост от 20.01.2026 09:47
1 779
0
3
ካፍ የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድንን አሰልጣኝ ከስራ አገደ አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የሆኑትን ፔፔ ቲያው ከስራ አግዷል፡፡ ካፍ በአፍሪካ ዋንጫ ሴኔጋል እና ሞሮኮ ባደረጉት አወዛጋቢ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ የታዩ የስነ ምግባር ግድፈቶችን ሲመረምር መቆየቱን አስታውቋል፡፡ ካፍ ባደረገው ምርመራ አሰልጣኝ ፔፔ ቲያው የእለቱን ዳኛ ጂን ጃኩዌስ ናዳላ ውሳኔ ባለመቀበል ተጫዋቾች ሜዳውን ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ መስጠታቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ በዚህም አሰልጣኙ ከአሰልጣኝነት ስራቸው እንዲታገዱ የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ውሳኔውን ተከትሎም አሰልጣኙ አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በሚያዘጋጁት የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ብሔራዊ ቡድንን ላይመሩ ይችላሉ መባሉን አፍሪካን ቶፕ ስፖርት ዘግቧል፡፡ በሚኪያስ አየለ
Пост от 19.01.2026 19:01
1 981
0
0
ማንቼስተር ሲቲ የማርክ ጉሂ ዝውውር ይፋ አደረገ አዲስ አበባ፣ ጥር 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የተከላካይ መስመር ተጫዋቹ ማርክ ጉሂ ወደ ማንቼስተር ሲቲ ያደረገውን ዝውውር ክለቡ ይፋ አድርጓል። የክርስታል ፓላስ የኋላ ደጀን የነበረው እንግሊዛዊው ተጫዋች ጉሂ በፕሪሚየር ሊግ ውስጥ ከሚገኙ ወጥ እና አስተማማኝ ከሚባሉ ተከላካዮች ተርታ መመደብ የቻለ ተጫዋች ነው። የ25 ዓመቱ የመሃል ተከላካይ ተጫዋቹ በሲቲዎች ቤት ለ5 ዓመታት ከግማሽ የሚያቆየውን የረጅም ዓመት ውል ተፈራርሟል። ሊቨርፑል እና ባየር ሙኒክን ጨምሮ በበርካታ ታላላቅ ክለቦች ሲፈለግ የነበረው ጉሂ በማንቼስተር ሲቲ በዓመት 15 ነጥብ 6 ሚሊየን ፓውንድ ክፍያ እንደሚያገኝ ተመላክቷል።
😢 4
Пост от 19.01.2026 09:16
1 800
0
2
ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮን መሆኗን ተከትሎ የዛሬው ዕለት ብሔራዊ በዓል እንዲሆን አወጀች አዲስ አበባ፣ ጥር 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮን መሆኗን ተከትሎ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ የዛሬው ዕለት ብሔራዊ በዓል እንዲሆን አውጀዋል፡፡ ሴኔጋል በሞሮኮ አስተናጋጅነት ሲካሄድ በቆየው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇን ሀገር ሞሮኮ በማሸነፍ በትናንትናው ዕለት የውድድሩ ሻምፒዮን ሆናለች፡፡ ድሉን ተከትሎ በዋና ከተማዋ ዳካር እና በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሴኔጋላውያን ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ የቴራንጋ አንበሶቹ እልህ አስጨራሽ በነበረው የፍፃሜ ጨዋታ ትናንት ምሽት ሞሮኮን በማሸነፍ በታሪካቸው ለ2ኛ ጊዜ የአፍሪካ ሻምፒዮን መሆን ችለዋል፡፡ ሴኔጋል በፈረንጆቹ 2021 የተዘጋጀውን 30ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ባነሳችበት ወቅት የወቅቱ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል በተመሳሳይ ብሔራዊ የድል በዓል ማወጃቸው ይታወሳል፡፡ በሚኪያስ አየለ
👍 12
Смотреть все посты