Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.9K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 527
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 225
ER
Общий
6.12%
Суточный
4.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 919 постов
Смотреть все посты
Пост от 13.07.2026 16:19
1
0
0
ማንቼስተር ዩናይትድ አንድሬይ ሳንቶስን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች አንድሬይ ሳንቶስን ከቼልሲ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ 48 ሚሊየን ፓውንድ እና እየታየ የሚጨመር 2 ሚሊየን ፓውንድ ለዝውውሩ ወጪ ማድረጉ ነው የተገለጸው፡፡

በተጨማሪም የቀድሞ ክለቡ ቼልሲ ከተጫዋቹ የወደፊት ሽያጭ 10 በመቶ እንደሚያገኝ በዝውውር ውሉ ላይ ተመላክቷል፡፡

የ22 ዓመቱ ተጫዋች በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት እስከ 2031 የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

አንድሬይ ሳንቶስ በፈረንጆቹ 2023 ከሀገሩ ክለብ ቫስኮ ደጋማ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ በ10 ነጥብ 2 ሚሊየን ፓውንድ መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡
Пост от 13.07.2026 12:57
225
0
2
በጆዜ ሞሪኒሆ የአሰልጣኝነት ሕይወት ዙሪያ የተሰራው ዘጋቢ ፊልም …

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጆዜ ሞሪኒሆ የአሰልጣኝነት ሕይወት ዙሪያ የተሰራው ዘጋቢ ፊልም ለእይታ የሚበቃበት ቀን ይፋ ተደርጓል፡፡

በፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆ የአሰልጣኝነት ሕይወት ዙሪያ ኔትፍሊክስ ሦስት ክፍሎች ያሉት ዘጋቢ ፊልም ሰርቷል፡፡

በጆዜ ሞሪኒሆ የአሰልጣኝነት ሕይወት ላይ የተሰራው ዘጋቢ ፊልምም የፊታችን ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለእይታ ይበቃል፡፡

ጆዜ ሞሪኒሆ የመጀመሪያ ዋንጫቻውን በፈረንጆቹ 2003 እንዲሁም የመጨረሻ ዋንጫቸውን ደግሞ በ2022 ማሸነፋቸውን ገልጸዋል፡፡

ከፈረንጆቹ 2003 ጀምሮ ዋንጫ እያሳኩ መሆኑም ጠቁመው ÷ ምንም ዋንጫ ያላሸነፈ አሰልጣኝ ዘጋቢ ፊልም ሊሰራለት እንደማይችል ተናግረዋል፡፡

በድጋሚ ሪያል ማድሪድን የተረከቡት ጆዜ ሞሪኒሆ ቼልሲ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ፣ ኢንተርሚላን፣ ፖርቶ፣ ቶተንሃም ሆትስፐር፣ ሮማ እና ቤኔፊካን የመሳሰሉ ክለቦችን ማሰልጠናቸው ይታወሳል፡፡
Пост от 13.07.2026 10:04
185
0
0
የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና አቀባበል እየተደረገለት ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና በሀዋሳ ከተማ አቀባበል እየተደረገለት ነው፡፡

የክለቡ ደጋፊዎች፣ የክልሉ እና የከተማዋ ነዋሪዎች በአደባባይ በመገኘት ቡድናቸውን እየተቀበሉ ይገኛሉ።

ሲዳማ ቡና በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ካደረጋቸው 38 ጨዋታዎች 19 ድል፣ 11 አቻ እና 8 ሽንፈት ማስተናገዱ ይታወቃል፡፡

በዚህም ክለቡ 68 ነጥብ በመሰብሰብ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉን ዋንጫ ማሳካቱ ይታወሳል፡፡
Пост от 12.07.2026 21:12
468
0
2
አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ በኒውዮርክ በተካሄደ የ15 ኪ.ሜ ውድድር አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኒውዮርክ በተካሄደው የ15 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ አሸነፈች፡፡

አትሌቷ 47 ደቂቃ ከ29 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሯን በበላይነት አጠናቅቃለች፡፡

አትሌት ጽጌ የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ነው ውድድሩን በቀዳሚነት ያጠናቀቀችው፡፡

ሌላኛዋ በርቀቱ የተሳተፈችው ኢትዮጵያዊት አትሌት መልክናት ውዱ 47 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት 2ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን አጠናቅቃለች፡፡
Пост от 12.07.2026 16:56
1 595
0
2
አራቱ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚዎች…

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ 48 ሀገራት በተሳተፉበት የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ውድድር 44 ሀገራት ተሰናብተው አራት ሀገራት ብቻ ቀርተዋል፡፡

የሦስት ጊዜ የመድረኩ ባለክብር አርጀንቲና፣ የሁለት ጊዜ ሻምፒዮኗ ፈረንሳይ እንዲሁም በተመሳሳይ አንድ ጊዜ ዋንጫውን ከፍ ማድረግ የቻሉት እንግሊዝ እና ስፔን ለሌላ ክብር ተቃርበዋል፡፡

በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ፈረንሳይ ከስፔን እንዲሁም እንግሊዝ ከአርጀንቲና በግማሽ ፍጻሜው ይገናኛሉ፡፡

ፈረንሳይ ሰሜን አፍሪካዊቷን ሀገር ሞሮኮ 2 ለ 0 በመርታት እንዲሁም ስፔን ቤልጂየምን 2 ለ 1 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ወደ ፍጻሜው ለማለፍ በመጪው ማክሰኞ ምሽት በቴክሳስ ዳላስ ስታዲየም (ኤቲ ኤንድ ቲ) የሚያደርጉት ጨዋታ ከወዲሁ ይጠበቃል፡፡

በሌላ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ አርጀንቲና ከእንግሊዝ የፊታችን ረቡዕ ምሽት በአትላንታ ይገናኛሉ፡፡

በሩብ ፍጻሜው እንግሊዝ ኖርዌይን እንዲሁም አርጀንቲና ስዊዘርላንድን በጭማሪ ደቂቃ ግቦች በማሸነፍ ለግማሽ ፍጻሜው መድረሳቸው ይታወቃል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መገናኘታቸውን ተከትሎ ብዙዎች አርጀንቲና ሻምፒዮን በሆነችበት የ1986 የዓለም ዋንጫ "የእግዜር እጅ" በመባል የምትታወቀውንና ዲያጎ ማራዶና በእንግሊዝ ላይ በእጅ ያስቆጠራትን ግብ እያስታወሷት ይገኛሉ፡፡

44 ሀገራት ተሰናብተው አራት ሀገራት በቀሩበት የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ማን ባለክብር ይሆናል የሚለው ከወዲሁ ተጠባቂ ነው፡፡
😢 1
Пост от 12.07.2026 16:11
1
0
0
አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ተሰናበቱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝነት ተሰናብተዋል፡፡

ሴኔጋል በ2026 የዓለም ዋንጫ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ በቤልጂየም ተሸንፋ ከውድድሩ መሰናበቷ ይታወሳል፡፡

አሰልጣኙ በዓለም ዋንጫው ያሳዩት ደካማ ጉዞ ለስንብታቸው ምክንያት መሆኑን የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ገልጿል።

የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት በአሰልጣኙ ስንብትና ቀጣይ ውሳኔዎች ዙሪያ በነገው ዕለት ማብራሪያ እንደሚሰጡ ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።

አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው በአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ ተጫዋቾቻቸው ጨዋታውን አቋርጠው ከሜዳ እንዲወጡ ማድረጋቸውን ተከትሎ ከፍተኛ ትችት ማስተናገዳቸው አይዘነጋም፡፡
Пост от 12.07.2026 14:55
300
0
2
ፊፋ የዓለም ዋንጫ ተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር ወደ 64 ለማሳደግ እያጤነ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፊፋ በ2030 የዓለም ዋንጫ ተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር ወደ 64 ለማሳደግ እያጤነ መሆኑን ገለጸ፡፡ ከፈረንጆቹ 1998 እስከ 2022 ድረስ የዓለም ዋንጫ በ32 ተሳታፊ ሀገራት ሲካሄድ መቆቱ ይታወሳል፡፡ በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር ደግሞ የተሳታፊ ሀገራት ቁጥር ወደ 48 ከፍ…

https://www.fanamc.com/archives/318626
Изображение
Смотреть все посты