Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.8K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 432
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 024
ER
Общий
4.97%
Суточный
3.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 782 постов
Смотреть все посты
Пост от 28.06.2026 18:17
1
0
0
ሸገር ከተማ መቻልን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሸገር ከተማ መቻልን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የሸገር ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ፍቅሩ አለማየሁ እና ያሬድ መኮንን ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የተገናኙት ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሀዋሳ ከተማ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

የኢትዮ ኤሌክትሪክን ግብ ሀሰን ሁሴን ሲያስቆጥር ጌታነህ ከበደ የሀዋሳ ከተማን የአቻነት ግብ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ሲዳማ ቡና በሀብታሙ ታደሰ ብቸኛ ግብ ባሕር ዳር ከተማን ማሸነፉ ይታወቃል፡፡
Пост от 28.06.2026 15:15
1
0
0
ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና ባሕር ዳር ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና ባሕር ዳር ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የሲዳማ ቡናን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ሀብታሙ ታደሰ አስቆጥሯል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከሀዋሳ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ሸገር ከተማ ከመቻል ይገናኛሉ፡፡
Пост от 28.06.2026 08:04
1
0
0
የ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ተጠናቅቀዋል።

ከየምድቦቻቸው 1ኛ እና 2ኛ በመሆን 24 ሀገራት በቀጥታ እንዲሁም ተጨማሪ 8 ሀገራት ምርጥ 3ኛ በመሆን የ32ቱን ጥሎ ማለፍ ተቀላቅለዋል።

በዚህም መሰረት የ32ቱ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ከምድብ 1 እና 2 ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቁት ደቡብ አፍሪካ እና አዘጋጇ ሀገር ካናዳ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት  በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል።

ምድብ ሦስትን በበላይነት ያጠናቀቀችው ብራዚል ከጃፓን እንዲሁም የምድብ 5 አሸናፊዋ ጀርመን ከፓራጓይ ተደልድለዋል።

ኔዘርላንድስ ከሞሮኮ፣ ኮትዲቯር ከኖርዌይ፣ ፈረንሳይ ከስዊድን፣ ሜክሲኮ ከኢኳዶር፣ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ እንዲሁም ቤልጂየም ከሴኔጋል ይገናኛሉ።

አሜሪካ ከቦሲኒያ ሄርዞጎቪና፣ ስፔን ከኦስትሪያ፣ ፖርቹጋል ከክሮሺያ፣ ስዊዘርላንድ ከአልጄሪያ፣ አውስትራሊያ ከግብጽ፣ አርጀንቲና ከኬፕቨርዴ እንዲሁም ኮሎምቢያ ከጋና ተደልድለዋል።
Пост от 28.06.2026 06:33
1
0
0
ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ 32ቱን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ 32ቱን መቀላቀሏን አረጋግጣለች።

በምድብ-11 የመጨረሻ ጨዋታ ኡዝቤክስታንን የገጠመችው አፍሪካዊቷ ሀገር ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ 3 ለ 1 አሸንፋለች።

ውጤቱን ተከትሎ በ4 ነጥብ ከምድቧ 3ኛ ደረጃ በመያዝ ያጠናቀቀች ሲሆን፥ ምርጥ 3ኛ በመሆን የ32ቱን ጥሎ ማለፍ ተቀላቅላለች።

በዚሁ ምድብ ፖርቹጋል ከኮሎምቢያ ያደረጉት የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል።

ውጤቱን ተከትሎ ኮሎምቢያ ምድቡን በበላይነት ያጠናቀቀች ሲሆን፥ ፖርቹጋል 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቃለች።

በምድብ-12 በተደረገ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ክሮሺያ ጋናን 2 ለ 1 በማሸነፍ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅላለች።

በዚሁ ምድብ እንግሊዝ ፓናማን 2 ለ ዐ አሸንፋለች።
Пост от 27.06.2026 19:54
175
0
1
የዓለም ዋንጫው የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዎች…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ መርሐ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡

በምድብ-11 አስቀድመው 32ቱን መቀላቀላቸውን ያረጋገጡት ፖርቹጋል እና ኮሎምቢያ ምድቡን በበላይነት ለማጠናቀቅ ሌሊት 8 ሰዓት ከ30 የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በምድቡ 2ኛ ጨዋታ ለሀገሩ ፖርቹጋል 2 ግቦችን በማስቆጠር አዳዲስ ክብረወሰኖችን ያስመዘገበው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በምሽቱ ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በዚሁ ምድብ በተመሳሳይ ሰዓት ኡዝቤክስታንን የምትገጥመው ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ ይህንን ጨዋታ ካሸነፈች ምርጥ 3ኛ በመሆን 32ቱን ትቀላቀላለች፡፡

በሊዮኔል ሜሲ አምስት ግቦች ታግዛ የምድቧን ሁለቱንም ጨዋታዎች በማሸነፍ 32ቱን የተቀላቀለችው አርጀንቲና ንጋት 11 ሰዓት ላይ በምድቡ ግርጌ የምትገኘውን ጆርዳን ትገጥማለች፡፡

በ18 ግቦች የዓለም ዋንጫው የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የግሉ ያደረገው ሊዮኔል ሜሲ በዚህም ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በዚህ ምድብ የምትገኘው ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጄሪያ 32ቱን ለመቀላቀል በተመሳሳይ ሰዓት ከኦስትሪያ ጋር በምታደርገው ጨዋታ አቻ መውጣት ይበቃታል፡፡

ከመጨረሻው ምድብ ከዛሬ ምሽቱ ጨዋታ አስቀድማ ማለፏን ያረጋገጠችው እንግሊዝ መሰናበቷን ካረጋገጠችው ፓናማ ጋር እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ላይ ትጫወታለች፡፡

በተመሳሳይ 32ቱን መቀላቀሏን ያረጋገጠችው የአፍሪካ ተወካይዋ ጋና በበኩሏ ከክሮሺያ ጋር በተመሳሳይ ሰዓት የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
Пост от 27.06.2026 17:22
7
0
1
ድሬዳዋ ከተማ ከፕሪሚየር ሊጉ ወረደ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ በ39 ነጥብ 18ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ድሬዳዋ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል፡፡

ቀደም ሲል አርባምንጭ ከተማ እና መቐለ 70 እንደርታ ከሊጉ መውረዳቸው ተረጋግጧል፡፡
Пост от 27.06.2026 08:55
324
0
1
ሴኔጋል፣ ኬፕቨርዴ እና ግብጽ 32ቱን ተቀላቀሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ ሴኔጋል፣ ግብጽና ኬፕቨርዴ 32ቱን ተቀላቀሉ።

ዛሬ ማለዳ 12 ሰዓት በተደረጉ የምድብ-7 የመጨረሻ ጨዋታዎች ግብጽ ከኢራን 1 ለ 1 አቻ ስትለያይ፥ ቤልጂየም ኒውዚላንድን 5 ለ 1 አሸንፋለች።

ውጤቱን ተከትሎ ቤልጂየም እና ግብጽ በተመሳሳይ 5 ነጥቦች በግብ ክፍያ ተበላልጠው ከምድባቸው ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።

ሌሊት 9 ሰዓት ላይ በምድብ-8 በተደረጉ የመጨረሻ ጨዋታዎች አፍሪካዊቷ ሀገር ኬፕ ቨርዴ ከሳዑዲ አረቢያ ያለ ግብ አቻ የተለያየች ሲሆን፥ ስፔን ዩራጓይን 1 ለ ዐ አሸንፋለች።

በዚህም መሰረት በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችው ኬፕ ቨርዴ ስፔንን በመከተል የ32ቱን ጥሎ ማለፍ ተቀላቅላለች።

በምድብ 9 ትናንት ምሽት ኢራቅን 5 ለ ዐ ያሸነፈችው ሴኔጋል በበኩሏ ምርጥ 3ኛ በመሆን 32ቱን መቀላቀሏን አረጋግጣለች።

እስካሁን ሰባት የአፍሪካ ሀገራት (ደቡብ አፍሪካ፣ ሞሮኮ፣ ኮትዲቯር፣ ጋና፣ ሴኔጋል፣ ግብጽ እና ኬፕቨርዴ) በቀጥታ ከምድባቸው ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።
Смотреть все посты