Каталог каналов Каналы в закладках Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
18.9K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
38 011
Сегодня
-22
Просмотров на пост
Всего
1 947
ER
Общий
4.66%
Суточный
3.3%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 18 928 постов
Смотреть все посты
Пост от 04.04.2026 17:28
379
0
1
ወላይታ ድቻ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወላይታ ድቻ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሁለቱ ቡድኖች 0 ለ 0 ነው የተለያዩት።

በተመሳሳይ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት መቐለ 70 እንደርታ ከሲዳማ ቡና ይጫወታል።

ኢትዮጵያ መድን ከኢትዮጵያ ቡና ያገናኘው ጨዋታ ቀን 10 ሰዓት ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ስታዲየም እየተካሄደ ይገኛል።

በሊጉ ቀደም ብሎ ቀን 7 ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 ማሸነፉ ይታወቃል።
Пост от 04.04.2026 16:56
449
0
1
ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኤፍ ኤ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 4 ለ 0 አሸንፏል።

በአሰልጣኝ ፔፕ ጓርዲዮላ የሚመሩት የካራባኦ ዋንጫ አሸናፊዎቹ በሜዳቸውና በደጋፊያቸው ፊት ባደረጉት ጨዋታ ነው ሊቨርፑልን ያሸነፉት።

በጨዋታው የማንቼስተር ሲቲ የፊት መስመር አጥቂ ኧርሊንግ ሃላንድ በጨዋታ (2) እንዲሁም በፍጹም ቅጣት ምት (1) ግቦችን በማስቆጠር ሃትሪክ ሰርቷል።

እንዲሁም ሌላኛዋን የማንቼስተር ሲቲ ግብ ሴሚኒዮ ከመረብ ጋር ሲያገናኝ ሊቨርፑሎች በጨዋታው ያገኙትን ፍጹም ቅጣት ምት ሞሀመድ ሳላህ ከመረብ ማገናኘት ሳይችል ቀርቷል።

በኤፍ ኤ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ ምሽት 1 ሰዓት ከ15 ቼልሲ ፖርትቬልን በሜዳው ሲያስተናግድ ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ሳውዝሃምፕተንን ይገጥማል።
👍 1
Пост от 04.04.2026 15:16
662
0
2
ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸንፏል።

ቀን 7 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን ማሸነፊያ ግቦች ያብስራ ጎሳዬ እና ፉዓድ አብደላ አስቆጥረዋል።

የሀድያ ሆሳዕና ብቸኛ ግብ ደግሞ ያብስራ ጎሳዬ (በራሱ መረብ ላይ) አስቆጥሯል።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ኢትዮጵያ መድን ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ይገናኛል።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ጀምሮ ወላይታ ድቻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እየተጫወተ ሲሆን፤ በተመሳሳይ ሜዳ አመሻሽ 12 ሰዓት መቐለ 70 እንደርታ ከሲዳማ ቡና ይጫወታል።
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 03.04.2026 18:39
1 201
0
1
አርባምንጭ ከተማ ሸገር ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል።

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ ማማዱ ሴክ እና ገዛኸኝ ደሳለኝ (በራስ ላይ) ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።

የሸገር ከተማን ብቸኛ ግብ ቢኒያም ፍቅሩ ከመረብ አሳርፏል።

አስቀድሞ በተካሄደ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ባሕር ዳር ከተማ እንዲሁም ድሬዳዋ ከተማ እና ፋሲል ከነማ ያለምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 03.04.2026 17:22
984
0
1
ድሬዳዋ ከተማ እና ፋሲል ከነማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ እና ፋሲል ከነማ አቻ ተለያይተዋል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ 0 ለ 0 ተለያይተዋል፡፡

በዚሁ ስታዲየም የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ መቻል ከምድረ ገነት ሽረ ይገናኛሉ፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው በሌላ የሊጉ ጨዋታ አርባ ምንጭ ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 1 እየመራ ይገኛል፡፡

በዚሁ ስታዲየም አስቀድሞ በተካሄደ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ባሕር ዳር ከተማ ያለምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 03.04.2026 15:26
1 163
0
1
አሰልጣኝ ጅናሮ ጋቱሶ ከጣሊያን ብሔራዊ ቡድን ጋር ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሰልጣኝ ጅናሮ ጋቱሶ ከጣሊያን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነት መልቀቃቸው ይፋ ተደርጓል፡፡

አሰልጣኙ የጣሊያን ብሔራዊ ቡድንን ወደ 2026 ዓለም ዋንጫ ማሳለፍ ባለመቻላቸው ከኃላፊነታቸው ለቅቀዋል፡፡

ጣሊያን ለሦስተኛ ተከታታይ ጊዜ ከዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ መሆኗ ይታወቃል፡፡

አሰልጣኝ ጅናሮ ጋቱሶ የጣሊያን ብሔራዊ ቡድንን በ2025 የተረከቡ ሲሆን÷ 8 ጨዋታዎችን በማድረግ 6 ድል፣ 1 አቻ እና 1 ሽንፈት አስመዝግበዋል፡፡

ጅናሮ ጋቱሶ ጣሊያን ለመጨረሻ ጊዜ በፈረንጆቹ 2006 የዓለም ዋንጫን ስታሳካ በተጫዋችነት የስብስቡ አካል እንደነበር ይታወሳል፡፡

በትናንትናው ዕለት የጣሊያን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ጋብሪኤል ግራቪና እና የብሔራዊ ቡድኑ መሪ ጂያንሉጂ ቡፎን ከኃላፊነት መልቀቃቸው አይዘነጋም፡፡

በወንድማገኝ ጸጋዬ
Пост от 03.04.2026 15:14
914
0
1
ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ባሕር ዳር ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ባሕር ዳር ከተማ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ 0 ለ 0 ተለያይተዋል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከአርባ ምንጭ ከተማ ጋር ይገናኛል።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ መቻል ከምድረ ገነት ሽረ ይገናኛሉ፡፡
Смотреть все посты