Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
12.0K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
39 247
Сегодня
-24
Просмотров на пост
Всего
1 903
ER
Общий
4.52%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 11 961 поста
Смотреть все посты
Пост от 11.02.2026 01:12
1 170
0
2
ማንቼስተር ዩናይትድ እና ዌስትሃም ዩናይትድ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ እና ዌስትሃም ዩናይትድ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል።

በጨዋታው ዌስትሃምን መሪ ያደረገችውን ግብ ሶቼክ ሲያስቆጥር፥ የማንቼስተር ዩናይትድን የአቻነት ግብ ሼሽኮ 96ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፏል።

ቀደም ብለው በተደረጉ የዛሬ ምሽት ጨዋታዎች ቼልሲ እና ሊድስ ዩናይትድ 2 ለ 2 አቻ የተለያዩ ሲሆን፥ ኒውካስል ዩናይትድ ቶተንሃም ሆትስፐርን እንዲሁም ቦርንማውዝ ኤቨርተንን በተመሳሳይ 2 ለ 1 አሸንፈዋል።
Изображение
Изображение
Изображение
👍 2
Пост от 11.02.2026 00:30
1 161
0
2
ቼልሲ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር አቻ ተለያየ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር 2 ለ 2 አቻ ተለያይቷል።

በስታምፎርድ ብሪጅ በተደረገው ጨዋታ የቼልሲን ግቦች ዦአዎ ፔድሮ እና ኮል ፓልመር ሲያስቆጥሩ፥ ንሜቻ እና ኦካፎር የሊድስ ዩናይትድን ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 10.02.2026 09:31
1 817
0
6
ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ 5ኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት…

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

ምሽት 5 ሰዓት 15 ላይ ዌስትሃም ዩናይትድ በሜዳው ማንቼስተር ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡

በሊጉ ያለፉትን አራት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው ማንቼስተር ዩናይትድ 5ኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

ወራጅ ቀጠና ላይ የሚገኘው ዌስትሃም ዩናይትድ በበኩሉ ተከታታይ ሁለተኛ ጨዋታውን ለማሸነፍ ይፋለማል።

ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ምሽት 4 ሰዓት 30 ላይ ቼልሲ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

በሊጉ ያለፉትን አራት ተከታታይ ጨዋታዎች ያሸነፈው ቼልሲ አሸናፊነቱን ለማስቀጠል ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር ከኒውካስል ዩናይትድ እንዲሁም ኤቨርተን ከቦርንማውዝ በተመሳሳይ ምሽት 4 ሰዓት 30 ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡

ፕሪሚየር ሊጉን አርሰናል በ56 ነጥቦች ሲመራ፥ ማንቼስተር ሲቲ በ6 ነጥቦች ዝቅ ብሎ ይከተላል።

አስቶን ቪላ በ47፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ44፣ ቼልሲ በ43 እንዲሁም ሊቨርፑል በ39 ነጥብ ከ3 እስከ 6 ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
Пост от 09.02.2026 17:09
1 667
0
2
ሀዲያ ሆሳዕና ፋሲል ከነማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ16ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ የጨዋታ መርሐ ግብር ሀዲያ ሆሳዕና ፋሲል ከነማን 1ለ0 አሸንፏል።

በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የሀዲያ ሆሳዕናን የማሸነፊያ ግብ ሱራፌል ተመስገን ከእረፍት መልስ በ60ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

ያለፉትን 3 ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው ሀዲያ ሆሳዕና የዛሬውን ጨዋታ በማሸነፍ ነጥቡን ወደ 24 ከፍ በማድረግ ደረጃውን አሻሽሏል።

ፋሲል ከነማ በበኩሉ 33 ነጥብን በመያዝ በሊጉ 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
Пост от 09.02.2026 09:49
1 606
0
1
ፋሲል ከነማ የሊጉ መሪ ለመሆን የሚያደርገው ፍልሚያ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ16ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ከሀድያ ሆሳዕና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ፋሲል ከነማ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ወደ 36 ከፍ በማድረግ ሊጉን መምራት ይጀምራል፡፡

ያለፉትን 3 ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው ሀድያ ሆሳዕና በበኩሉ ድል የሚያደርግ ከሆነ ነጥቡን ወደ 24 ከፍ በማድረግ ደረጃውን ማሻሻል ይችላል፡፡

የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም መደረግ ይጀምራል፡፡
Изображение
Изображение
Пост от 09.02.2026 08:45
1 676
0
1
በእግር ኳስ ሕይወቱ 13ኛ ክለቡን የተቀላቀለው ሮድሪጌዝ…

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ2014 የብራዚል ዓለም ዋንጫ በኋላ በምርጥ ብቃቱ መቀጠል ያልቻለ ተጫዋች ነው ኮሎምቢያዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሀሜስ ሮድሪጌዝ፡፡

በፈረንጆቹ 1991 የተወለደው ሀሜስ ሮድሪጌዝ እግር ኳስን መጫወት የጀመረው በሀገሩ ክለብ ኢንቪጋዶ ነው፡፡

ከዚያ በመቀጠል በተለያዩ ሊጎችና ክለቦች መጫወት የቻለ ሲሆን የተጠበቀውን ያህል ውጤታማ መሆን አልቻለም፡፡

ሀሜስ ለሪያል ማድሪድ፣ ባየርን ሙኒክ፣ ፖርቶ፣ ሞናኮ፣ ኤቨርተን እና ኦሎምፒያኮስን ለመሳሳሉ ክለቦች ተጫውቶ አሳልፏል፡፡

ተጫዋቹ እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትን ጨምሮ ለተለያዩ ክለቦች ተጫውቶ ቢያሳልፍም በእግር ኳስ ሕይወቱ ምርጡን ጊዜ ያሳለፈው ከሀገሩ ኮሎምቢያ ጋር በ2014ቱ የዓለም ዋንጫ ነው፡፡

በፈረንጆቹ 2014 በብራዚል አስተናጋጅነት በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ክስተት ከነበሩ ተጫዋቾች መካከል ኮሎምቢያዊው ሀሜስ ሮድሪጌዝ ትልቁ ክስተት ነበር፡፡

በወቅቱ ጀርመን ዋንጫውን ስታሸንፍ ሀሜስ ሮድሪጌዝ ደግሞ የስፖርት ቤተሰቡን ልብ ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

በወቅቱ 22 ዓመቱ ላይ ይገኝ የነበረው ተጫዋቹ ብራዚላውያን በደገሱት የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ በውብ ግቦች ደጋፊውን እያዝናና የእርሱን ያህል የነገሰ አልነበረም።

በውድድሩ ከሀገሩ ጋር እስከ ሩብ ፍጻሜ መጓዝ የቻለ ሲሆን፥ ስድስት ግቦችን በማስቆጠር የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን የወርቅ ጫማ አሸናፊም ነበር፡፡
👇
https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid0EYwCrksKnwVU3KEYd7Eapi841GmFkRYPHP9Kqn7WQtJGZN7dU8XKv9s73Tn1gTaZl
Изображение
Пост от 09.02.2026 08:44
1 407
0
1
በፈረንሳይ ሜትዝ በተደረገው የቤት ውስጥ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንሳይ ሜትዝ በተከናወነው የሴቶች 3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል።

በዓለም አትሌቲክስ የብር ሜዳልያ በተሰጠው የቤት ውስጥ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከአንድ እስከ ሦስት ተከታትሎ በመግባት ድል ተጎናጽፏል።
በዚህም አትሌት ብርቱካን ሞላ በ8:40.49 በመግባት ውድድሩን ስታሸንፍ÷ አትሌት ሽቶ ጉሜ በ8:41.18 2ኛ፣ አትሌት በ8:41.75 3ኛ ደረጃ በመያዝ ተከታትለው ገብተዋል።

ትናንት በተካሄደው በዚህ ውድድር የተሳተፈችው ሌላኛዋ አትሌት ቤተልሔም ኦላና 6ኛ ደረጃ ይዛ አጠናቅቃለች።

በወንዶች ምድብ አትሌት አብዲሳ ፈይሳ በ7:44.83 በመግባት ሶስተኛ፣ አትሌት ኤርሚያስ ግርማ በ7:51.80 አምስተኛ፣ አትሌት ለሚ ተሾመ በ7:55.07 ሰባተኛ ደረጃ በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቅቀዋል።
Изображение
Смотреть все посты