Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
12.0K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
38 458
Сегодня
-8
Просмотров на пост
Всего
1 951
ER
Общий
4.56%
Суточный
3.2%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 12 045 постов
Смотреть все посты
Пост от 17.03.2026 23:23
694
0
1
ስፖርቲንግ ሊዝበን የ3 ለ 0 ሽንፈቱን ቀልብሶ ለሩብ ፍጻሜ አለፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ የመልስ ጨዋታ ስፖርቲንግ ሊዝበን ቦዶ ግሊምትን በድምር ውጤት በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜው አልፏል፡፡

ምሽት 2 ሰዓት ከ45 በኢስታዲዮ ጆዜ አልቫላዴ በተደረገው ጨዋታ በመደበኛው 90 ደቂቃ ባለሜዳው ስፖርቲንግ ሊዝበን 3 ለ ዐ አሸንፏል፡፡

በመጀመሪያው ጨዋታ ቦዶ ግሊምት 3 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ሲሆን፥ በድምር ውጤት 3 አቻ መሆናቸውን ተከትሎ ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ደቂቃ አምርቷል።

ለሩብ ፍጻሜው አላፊውን ቡድን ለመለየት በተደረገው የተጨማሪ 30 ደቂቃ ፍልሚያ ስፖርቲንግ ተጨማሪ ሁለት ግቦች አስቆጥሮ በድምር ውጤት 5 ለ 3 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።

ስፖርቲንግ በሩብ ፍጻሜው ከአርሰናል እና ባየር ሊቨርኩሰን የድምር ውጤት አሸናፊ ጋር ይገናኛል፡፡
Пост от 17.03.2026 09:06
1 422
0
1
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተጠባቂ የመልስ ጨዋታዎች…

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ የመልስ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት መደረግ ይጀምራሉ፡፡

ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ የፖርቹጋሉ ክለብ ስፖርቲንግ ሊዝበን በሜዳው ቦዶ ግሊምትን ያስተናግዳል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች ባለፈው ሳምንት በመጀመሪያ ዙር ያደረጉትን ጨዋታ የኖርዌዩ ክለብ ቦዶ ግሊምት 3 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ የማለፍ እድሉን አስፍቷል፡፡

ቦዶ ግሊምት በዚህ የውድድር ዓመት በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ መድረክ ክስተት ከሆኑ ቡድኖች መካከል አንዱ ነው፡፡

የኖርዌዩ ክለብ በዘንድሮው የውድድር ዘመን በሻምፒየንስ ሊጉ ማንቼስተር ሲቲ፣ ኢንተር ሚላን እና አትሌቲኮ ማድሪድን የመሳሰሉ ትልልቅ ቡድኖችን ማሸነፉ አይዘነጋም፡፡

የቦዶ ግሊምት እና የስፖርቲንግ ሊዝበን የድምር ውጤት አሸናፊ በሩብ ፍጻሜው ከአርሰናል እና ባየር ሊቨርኩሰን አሸናፊ ጋር ይገናኛል፡፡

በሌላ የዛሬ መርሐ ግብር ምሽት 5 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ሪያል ማድሪድን ያስተናግዳል፡፡

በሳንቲያጎ ቤርናባው በተደረገው የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ሪያል ማድሪድ በፌዴሪኮ ቫልቬርዴ ሦስት ግቦች 3 ለ 0 ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች ዛሬ ምሽት የሚያደርጉት ጨዋታ ከፈረንጆቹ 2020 ወዲህ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ መድረክ 13ኛ የእርስ በርስ ግንኙነታቸው ነው፡፡

በሎስ ብላንኮዎቹ በኩል በጉዳት የመጀመሪያው ጨዋታ ያመለጣቸው ኪሊያን ምባፔ...

https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid0rp1nyas3s1PjjdguMV1KTrZLuWbhDZ2GPQDA6ZDTyimVyereh4NTFYGs4P6CwN3jl
Пост от 15.03.2026 18:59
1 719
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ አስቶን ቪላን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ አስቶን ቪላን 3 ለ 1 አሸንፏል።

በሜዳው ኦልድ ትራፎርድ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ አስቶን ቪላን ያስተናገደው ማንቼስተር ዩናይትድ፤ ካሴሚሮ፣ ኩንሃ እና ሴስኮ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።

የአስቶን ቪላን ብቸኛ ግብ ባርክሌይ ከመረብ አሳርፏል።

በዚህም ማንቼስተር ዩናይትድ ነጥቡን 54 በማድረስ በሊጉ ያለውን 3ኛ ደረጃ አስጠብቋል።

የሊጉ ጨዋታ ምሽት 1፡30 ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ ሊቨርፑልን ቶተንሃም ሆትስፐርን በአንፊልድ ያስተናግዳል።
Изображение
Изображение
Изображение
👍 12
Пост от 15.03.2026 18:15
1 442
0
1
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ነገሌ አርሲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ነገሌ አርሲን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ በዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሀሰን ሁሴን ባስቆጠራቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተደረገው የመቐለ 70 እንደርታ እና ወላይታ ድቻ ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 15.03.2026 16:21
1 467
0
2
በባርሴሎና የማራቶን ውድድር አትሌት ፎቴን ተስፋይ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አትሌት ፎቴን ተስፋይ ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፈችበት የባርሴሎና የማራቶን ውድድር ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፋለች፡፡

አትሌት ፎቴን 2 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ከ53 ሴኮንድ በመግባት ነው በቀዳሚነት ያጠናቀቀችው፡፡

አትሌቷ ባስመዘገበችው ሰዓት የቦታውን ክብረወሰን መስበር የቻለች ሲሆን የዓለም ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት በመሆን ተመዝግቧል፡፡

በውድድሩ አትሌት ዘይነባ ይመር፣ ጫልቱ ጬምዴሳ እና ያልጋነሽ እስከመች ከ3ኛ እስከ 5ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቀዋል።
Пост от 15.03.2026 11:18
1 335
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ ከአስቶን ቪላ…

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ ከአስቶን ቪላ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን ለማረጋገጥ እየተፋለሙ የሚገኙና ተመሳሳይ ነጥብ ይዘው በደረጃ ሰንጠረዡ 3ኛ እና 4ኛ ላይ የተቀመጡት ሁለቱ ቡድኖች ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

አዲስ አሰልጣኝ ከቀጠሩ በኋላ ጠንካራ አቋም እያሳዩ የሚገኙት ቀያዮቹ ሰይጣኖች በሜዳቸው ኦልድ ትራፎርድ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ አስቶን ቪላን ያስተናግዳሉ።

እንዲሁም ምሽት 1፡30 ሰዓት ላይ ሊቨርፑልን ከቶተንሃም ሆትስፐር የሚያገናኘው ሌላኛው የዕለቱ ተጠባቂ ጨዋታ ይደረጋል።

የመውረድ አደጋ የተደቀነበት የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ወደ አንፊልድ ተጉዞ የአምናውን የሊጉ ሻምፒዮን ሊቨርፑልን ይገጥማል።

የእለቱ የሊጉ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ ክሪስታል ፓላስ ከሊድስ እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከፉልሃም ጨዋታቸውን በተመሳሳይ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ያደርጋሉ።

በዮናስ ጌትነት
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 15.03.2026 10:51
1 334
0
1
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሁለት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ፡፡

በዚህም ቀን 10 ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ነገሌ አርሲ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ጋር ይገናኛል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት መቐለ 70 እንደርታ እና ወላይታ ድቻ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ፡፡
Смотреть все посты