Каталог каналов Каналы в закладках Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.0K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 891
Сегодня
-28
Просмотров на пост
Всего
1 769
ER
Общий
4.1%
Суточный
2.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 18 970 постов
Смотреть все посты
Пост от 08.04.2026 00:11
518
0
1
ባየርን ሙኒክ ሪያል ማድሪድን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ባየርን ሙኒክ ሪያል ማድሪድን 2 ለ 1 አሸንፏል።

የባየርን ሙኒክን የማሸነፊያ ግቦች ሉዊስ ዲያዝ እና ሀሪኬን አስቆጥረዋል።

ሪያል ማድሪድን ከሸንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ኪሊያን ምባፔ ከመረብ አሳርፏል።

በሌላ ጨዋታ አርሰናል ስፖርቲንግ ሊዝበንን 1 ለ 0 አሸንፏል።

የአርሰናልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ካይ ሀቨርትዝ በሁለተኛው አጋማሽ አስቆጥሯል።
👏 4
👍 1
Пост от 07.04.2026 21:18
861
0
1
የሪያል ማድሪድ እና ባየርን ሙኒክ አሰላለፍ ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ተጠባቂ ጨዋታዎች አሰላለፍ ይፋ ሆኗል፡፡

በዚህም ሪያል ማድሪድ አንድሬ ሉኒን፣ ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ፣ አንቶኒዮ ሩዲገር፣ ዲን ሁጅሰን፣ አልቫሮ ካሬራስ፣ ፌዴሪኮ ቫልቬርዴ፣ ቲያጎ፣ ቹሀሚኒ፣ አርዳ ጉለር፣ ኪሊያን ምባፔ እና ቪኒሸስ ጁኒየርን በመጀመሪያው አሰላለፍ ውስጥ አካትቷል፡፡

ባየርን ሙኒክ በኩል ማኑኤል ኑየር፣ ኡፓሜካኖ፣ ታህ፣ ኪሚቺ፣ ናብሪ፣ ሀሪኬን፣ ዲያዝ፣ ኦሊሴ፣ ላይመር፣ ስታኒሲች እና ፓቭሎቪች በቋሚነት የሚጀምሩ ይሆናል፡፡

በሌላኛው የምሽቱ ጨዋታ ደግሞ ዴቪድ ራያ፣ ቤንዋይት፣ ሳሊባ፣ ጋብሬል ማጋሌሽ፣ ካላፊዮሪ፣ ዙቢሜንዲ፣ ራይስ፣ ኦዴጋርድ፣ ማዱኬ፣ ትሮሳርድ እና ዮኬሬሽ ስፖርቲንግን በሚገጥመው የአርሰናል የመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ ተካትተዋል፡፡

ተጋጣሚው ስፖርቲንግ ሊዝበን በበኩሉ ሩሂ ሲልቫ፣ ኢናሲዮ፣ ዳይሞንዴ፣ ፍሬስኔዳ፣ አራሆ፣ ሲሞስ፣ ሞሪታ፣ ትሪንካሆ፣ ካታሞ፣ ፖቴ እና ሰዋሬዝን በመጀመሪያው አሰላለፍ ይዞ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ሁለቱም የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች በተመሳሳይ ምሽት 4 ሰዓት ላይ መደረግ ይጀምራሉ፡፡
👍 3
Пост от 07.04.2026 18:55
1 051
0
2
የማራቶን ውድድር ከዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሊቀነስ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከፈረንጆቹ 2030 ጀምሮ ማራቶን ከዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ውጪ እንደሚሆን የዓለም አትሌቲክስ ይፋ አድርጓል፡፡

ማራቶን በፈረንጆቹ 2027 እና 2029 በሚካሄዱት የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ የውድድሩ አካል ሆኖ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

ከፈረንጆቹ 2030 ጀምሮ ማራቶን ከዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር እንደሚወጣ ነው የተገለጸው፡፡

የዓለም አትሌቲክስ አዲስ ዓመታዊ የአትሌቲክስ ውድድር እንደሚያዘጋጅ ተጠቁሟል፡፡

በዚህም በፈረንጆቹ 2030 የዓለም አትሌቲክስ ማራቶን ሻምፒዮና የሚል ራሱን የቻለ ውድድር እንደሚጀመር ተመላክቷል፡፡

በፈረንጆቹ 2030 የሚጀምረው አዲሱ የዓለም አትሌቲክስ ማራቶን ሻምፒዮና በየአመቱ የሚካሄድ ሲሆን፥ የመጀመሪያውን ውድድር አቴንስ እንድታዘጋጅ ተመርጣለች፡፡
Изображение
Изображение
Пост от 07.04.2026 14:20
1 329
0
1
አሮን ራምሴ ራሱን ከእግር ኳስ ዓለም አገለለ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞ የአርሰናል ተጫዋች አሮን ራምሴ ራሱን ከእግር ኳስ ዓለም ማግለሉን ይፋ አድርጓል።

በሜክሲኮው ፑማስ ክለብ እየተጫወተ የነበረው ራምሴ በ35 ዓመቱ ጫማውን ሰቅሏል።

ተጫዋቹ ለአርሰናል፣ ጁቬንቱስ፣ ኖቲንግሃም ፎረስት፣ ካርዲፍ ሲቲ እና ሬንጀርስን ለመሳሰሉ ክለቦች ተጫውቷል።

ራምሴ ከአርሰናል ጋር የኤፍ ኤ እና የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫዎችን አሳክቷል።

ከጣሊያኑ ክለብ ጁቬንቱስ ጋር ደግሞ የጣሊያን ሴሪ አ እና ኮፓ ኢታሊያ ዋንጫዎችን ማሳካቱ ይታወሳል።
Пост от 07.04.2026 12:27
1 373
0
1
ሀሪ ማጓየር በማንቼስተር ዩናይትድ ውሉን አራዘመ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የተከላካይ ሥፍራ ተጫዋች ሀሪ ማጓየር በማንቼስተር ዩናይትድ ለተጨማሪ አንድ ዓመት ለመቆየት ውሉን አራዝሟል፡፡

ተጫዋቹ በዩናይትድ ቤት አስቀድሞ የነበረው ውል በመጪው ሰኔ ወር ላይ የሚጠናቀቅ ሲሆን፥ እስከ ፈረንጆቹ 2027 ለመቆየት ውሉን ማራዘሙ ነው የተገለጸው፡፡

በአዲሱ ውል ላይ ለተጨማሪ አንድ ዓመት የማራዘም አማራጭ ያለው አንቀጽ መካተቱም ተመላክቷል፡፡

እንግሊዛዊው ተጫዋች ሀሪ ማጓየር በፈረንጆቹ 2019 ከሌስተር ሲቲ በ80 ሚሊየን ዩሮ ማንቼስተር ዩናይትድን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

የ33 ዓመቱ ተጫዋች ለማንቼስተር ዩናይትድ 266 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን፥ ከክለቡ ጋር የኤፍ ኤ እና የካራባኦ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡
Пост от 07.04.2026 10:31
1 386
0
2
የፓሪስ ኦሎምፒክ ሻምፒዮኗ አትሌት ጋቢ በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር ላይ እንደምትሳተፍ አሳወቀች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፓሪስ ኦሎምፒክ 200 ሜትር ሻምፒዮኗ አትሌት ጋቢ ቶማስ በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር ላይ እንደምትሳተፍ አሳውቃለች።

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የምታስተናግደው የአንድ ቀን ዓለም አቀፍ ውድድር ሚያዚያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡

በዚህ ውድድር ላይ አሜሪካዊቷ አትሌት ጋቢ ቶማስ እንደምትሳተፍ ተረጋግጧል፡፡

ጋቢ በፈረንጆቹ 2024 በፓሪስ ኦሎምፒክ በ200 ሜትር የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ ስትሆን÷ ከቡድን አጋሮቿ ጋር ደግሞ የወርቅ ሜዳልያ ለሀገሯ ማስገኘቷ ይታወሳል።

አትሌቷ በቡዳፔስት የብር ሜዳልያ፣ በቶኪዮ ዓለም ሻምፒዮና ደግሞ የነሐስ ሜዳልያ አሸናፊ መሆኗ ይታወቃል፡፡
Пост от 05.04.2026 22:35
394
0
2
የኤፍ ኤ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ድልድል ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ድልድል ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት ማንቼስተር ሲቲ ከሳውዛምፕተን እንዲሁም ቼልሲ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ወደ ፍጻሜ ለማለፍ የሚፋለሙ ይሆናል።

ትናንት በተደረጉ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 4 ለ ዐ፣ ቼልሲ ፖርትቬልን 7 ለ ዐ እንዲሁም ሳውዛምፕተን አርሰናልን 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ማለፋቸው ይታወሳል።

ዛሬ በተደረገ የሩብ ፍጻሜ የመጨረሻ ጨዋታ ሊድስ ዩናይትድ ዌስትሃም ዩናይትድን በመለያ ምት በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።

የኤፍ ኤ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ከ20 ቀን በኋላ በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋሉ።
Изображение
Смотреть все посты