Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
12.1K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
38 280
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 093
ER
Общий
5.12%
Суточный
3.7%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 12 064 постов
Смотреть все посты
Пост от 24.03.2026 16:52
850
0
1
የቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ተስተካካይ ጨዋታ…

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና የሚያደርጉት የ20ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ የሚደረግበትን ቀን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማሕበር ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም ተስተካካይ ጨዋታው ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ የሚደረግ ይሆናል፡፡

ኢትዮጵያ ቡና በ32 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ÷ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ25 ነጥብ 18ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

ሊጉን ሲዳማ ቡና በ45 ነጥብ ሲመራው ሀዋሳ ከተማ በ40፣ ነገሌ አርሲ በ38 እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ37 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
Изображение
Изображение
🙏 3
Пост от 24.03.2026 10:25
1 145
0
6
55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአደይ አበባ ስታዲየም ተጀምሯል።

በሻምፒዮናው 9 ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ ከ36 ክለቦች የተወጣጡ ከ1 ሺህ በላይ አትሌቶች ይሳተፋሉ፡፡

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ ሰዓት መመዝገቢያ ማሽን ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

በዚህም በውድድሩ የሚመዘገቡ ሰዓቶች ዓለም አቀፍ ተቀባይነትን የሚያገኙ ይሆናል፡፡

በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑ አትሌቶች የሜዳሊያ እና የገንዘብ ሽልማት የሚበረከት ሲሆን÷ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በምታስተናግደው የዋን ደይ ሚቲንግ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተመላክቷል፡፡

55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመጋቢት 15 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በአደይ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
👍 2
Пост от 24.03.2026 10:25
1
0
0
55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአደይ አበባ ስታዲየም ተጀምሯል።

በሻምፒዮናው 9 ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ ከ36 ክለቦች የተወጣጡ ከ1 ሺህ በላይ አትሌቶች ይሳተፋሉ፡፡

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ ሰዓት መመዝገቢያ ማሽን ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

በዚህም በውድድሩ የሚመዘገቡ ሰዓቶች ዓለም አቀፍ ተቀባይነትን የሚያገኙ ይሆናል፡፡

በውድድሩ አሸናፊ ለሆኑ አትሌቶች የሜዳሊያ እና የገንዘብ ሽልማት የሚበረከት ሲሆን÷ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በምታስተናግደው የዋን ደይ ሚቲንግ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተመላክቷል፡፡

55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመጋቢት 15 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በአደይ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል፡፡
Изображение
Изображение
Изображение
Пост от 24.03.2026 08:43
1 243
0
1
ከልጅነቱ የአርሰናል ወዳጅ ሆኖ ያደገው ዊሊያም ሳሊባ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዚህ ወቅት ዓለም ላይ ካሉ ምርጥ የመሐል ተከላካይ ሥፍራ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው ፈረንሳዊው ዊሊያም ሳሊባ፡፡ መካከለኛ የኑሮ ደረጃ ካላቸው ቤተሰቦች የተወለደው ሳሊባ እንደ ማንኛውም ታዳጊ በፓሪስ በምትገኝ ቦንዲ መንደር ውስጥ መንገድ ላይ ኳስ እየተጫወተ ነው ያደገው፡፡ በሳሊባ የእግር ኳስ ሕይወት ላይ ትልቅ ለውጥ ያመጣው…

https://www.fanamc.com/archives/311681
👍 6
Пост от 22.03.2026 21:40
1 756
0
3
ማንቼስተር ሲቲ የካራባኦ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲ አርሰናልን 2 ለ ዐ በማሸነፍ የ2025/26 የእንግሊዝ ካራባኦ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኗል።

የማንቼስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ኒኮ ኦ'ሬሊ በሁለተኛው አጋማሽ አስቆጥሯል።

ውሃ ሰማያዊዎቹ በታሪካቸው ለ9ኛ ጊዜ ዋንጫውን ያሳኩ ሲሆን፥ አርሰናል ከ33 ዓመታት በኋላ ዋንጫውን ለማሸነፍ ያደረገው ጥረት ሳይሳካለት ቀርቷል።
👍 12
Пост от 22.03.2026 20:27
1 842
0
1
ማን የሚያሸንፍ ይመስላችኋዋል?

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ የእንግሊዝ ካራባኦ ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

በጨዋታው የመጀመሪያው አጋማሽ በአርሰናል በኩል ፔሮ ሄንካፔ እንዲሁም በማንቼስተር ሲቲ በኩል ኩሳኖቭ የማስጠንቀቂያ (ቢጫ) ካርድ ተመልክተዋል።

በመጀመሪያው አጋማሽ ጨዋታ ሲቲዎች የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ነበራቸው።

በጨዋታው ማን የሚያሸንፍ ይመስላችኋዋል?
ሐሳብዎትን በአስተያየት መስጫው ያጋሩን👇

https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid0388Yr3uxxXK4mKYxtLPrNznaEpuk7JfU5EH8GEv1WWearMWK61mwCm9L2JQxx5TEql
Изображение
Пост от 22.03.2026 18:45
1 793
0
2
አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ... አሰልጣኞቹ  ምን አሉ?

‎አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ካራባኦ ዋንጫ ፍጻሜ አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በዌምብሌይ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።

የሁለቱ ክለቦች አሰልጣኞች ስለ ወሳኙ የምሽቱ ፍልሚያ በሰጡት አስተያየት ምን አሉ?

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ፦

"ጨዋታው ለክለባችን ታሪክ መስራት የምንችልበት ስለሆነ በከፍተኛ ጉጉት እየጠበቅነው ነው፥ ደጋፊዎቻችንን ማስደሰት እንፈልጋለን...

ጉዟችንን በድልና በዋንጫ ለመቋጨት የምንችልበት እድል በእጃችን ስለሆነ ዛሬ ትልቅ ቀን ነው፥ ያን ማሳካት የምንችል ከሆነ ለቡድናችን ተጨማሪ ጉልበት ይሆነናል፤ ሌሎች በእኛ ላይ ያላቸውን እምነትም ያጠነክራል"

አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ፦

"ጨዋታው ለእኛ ትልቅ ትርጉም አለው፥ ሁሌም በዌምብሌይ ከባድ ፈተና እና ትልቅ ድል አለ። የትኛውም የፍጻሜ ጨዋታ ቀላል አይሆንም፥ ይህ እድል መቼ ተመልሶ እንደሚመጣ ስለማናውቅ አጋጣሚውን በአግባቡ መጠቀም አለብን"
Изображение
👍 7
Смотреть все посты