Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.6K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 782
Сегодня
-9
Просмотров на пост
Всего
1 966
ER
Общий
5.15%
Суточный
3.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 558 постов
Смотреть все посты
Пост от 29.05.2026 20:28
480
0
1
ሸገር ከተማ ፋሲል ከነማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሸገር ከተማ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ሄኖክ አዱኛ ባስቆጠረው ግብ ሸገር ከተማ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።

ቀደም ሲል በተደረገ ጨዋታ ሆሳዕና እና ምድረ ገነት ሽረ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ መደረግ ጀምሮ 34ኛው ደቂቃ ላይ የተቋረጠው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ በነገው ዕለት 3 ሰዓት ከ30 በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይደረጋል።

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ሊደረግ የነበረው የወላይታ ድቻ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚደረግ ተመላክቷል፡፡

በተጨማሪም ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም የሚደረጉ የአዲስ አበባ ስታዲየም መርሐ ግብሮች በተያዘላቸው ሰዓት የቦታ ለውጥ ተደርጎባቸው በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚካሄዱ ይሆናል፡፡
Пост от 29.05.2026 17:33
778
0
2
ሪያል ማድሪድ አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆን በኃላፊነት ሾመ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆ የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ ዋና አሰልጣኝ ሆነዋል፡፡

አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆ በሪያል ማድሪድ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2029 ድረስ የሚያቆያቸውን ውል ተፈራርመዋል፡፡

አሰልጣኙ ከዚህ ቀደም ከፈረንጆቹ 2010 እስከ 2013 ሪያል ማድሪድን ማሰልጠናቸው ይታወሳል፡፡
Пост от 29.05.2026 17:19
730
0
1
ሀድያ ሆሳዕና እና ምድረ ገነት ሽረ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀድያ ሆሳዕና እና ምድረ ገነት ሽረ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የሀድያ ሆሳዕናን ግብ እዮብ አለማየሁ ሲያስቆጥር ዳንኤል ዳርጌ ደግሞ የምድረ ገነት ሽረን ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከሸገር ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በአዲስ አበባ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ መደረግ ጀምሮ 34ኛው ደቂቃ ላይ የተቋረጠው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ በነገው ዕለት 3 ሰዓት ከ30 በአበበ ቢቂላ ስታዲየም እንደሚደረግ አክሲዮን ማህበሩ አስታውቋል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ሊደረግ የነበረው የወላይታ ድቻ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚደረግ ተመላክቷል፡፡

በተጨማሪም ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም የሚደረጉ የአዲስ አበባ ስታዲየም መርሐ ግብሮች በተያዘላቸው ሰዓት የቦታ ለውጥ ተደርጎባቸው በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚካሄዱ ይሆናል፡፡
Пост от 29.05.2026 09:37
1 280
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይገናኛሉ፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ወላይታ ድቻ ከነገሌ አርሲ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ ምድረ ገነት ሽረ ከሀድያ ሆሳዕና እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከሸገር ከተማ ይጫወታሉ፡፡
Изображение
Пост от 28.05.2026 20:12
1 500
0
1
አርባምንጭ ከተማ መቻልን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ መቻልን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የአርባምንጭን ግቦች አሸናፊ ተገኝ እና ቴዎድሮስ በንቲ አስቆጥረዋል፡፡

መቻልን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ ፈቱዲን ጀማል ከመረብ አሳርፏል፡፡

ቀደም ሲል ቀን 9 ሰዓት በተደረጉ ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 1 እንዲሁም ሀዋሳ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
Пост от 28.05.2026 17:22
1 353
0
1
ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን የማሸነፊያ ግቦች ብሩክ አለማየሁ እና ሀብታሙ ጉልላት አስቆጥረዋል፡፡

ድሬዳዋ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገውን ግብ ደግሞ አስራት ቱንጆ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ ሌላ የሊጉ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

የሀዋሳ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ በረከት ሳሙኤል (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥሯል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል መቻል ከአርባምንጭ ከተማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Пост от 28.05.2026 16:51
1 416
0
1
70ኛው የባሎንዶር ሽልማት ሥነ ሥርዓት በለንደን ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባሎንዶር ሽልማት የ2026 የሽልማት ሥነ ሥርዓት የሚካሄድበት ከተማ ይፋ ተደርጓል፡፡

በፍራንስ ፉትቦል መጽሔት የሚዘጋጀው የባሎንዶር ሽልማት በመጪው ዓመት ጥቅምት ወር ለ70ኛ ጊዜ ይካሄዳል፡፡

ይህ የሽልማት ሥነ ሥርዓት በእንግሊዝ ለንደን ከተማ እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡

የ2025 የባሎንዶር ሽልማትን ፈረንሳዊው የፒኤስጂ ተጫዋች ኦስማን ዴምቤሌ ማሸነፉ የሚታወስ ነው፡፡
Смотреть все посты