Каталог каналов Каналы в закладках Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.0K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 834
Сегодня
-8
Просмотров на пост
Всего
1 786
ER
Общий
4.2%
Суточный
3.1%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 18 987 постов
Смотреть все посты
Пост от 11.04.2026 09:33
741
0
2
አርሰናል ከቦርንማውዝ…

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ አርሰናል በኢምሬትስ ቦርንማውዝን ያስተናግዳል፡፡

የሊጉ መሪ አርሰናል በሊጉ አምስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት እና መሪነቱን ለማጠናከር ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ያለፉትን አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው ተጋጣሚው ቦርንማውዝ በበኩሉ÷ ወደ ድል ለመመለስ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሁለቱም በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ድል ሲያደርጉ በቀሪው አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል፡፡

አርሰናል የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ማንቼስተር ሲቲ እስኪጫወት ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ 12 ከፍ የሚያደርግ ይሆናል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በአንፊልድ ሮድ ፉልሃምን ይገጥማል፡፡

ሊቨርፑል በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ይፋለማል፡፡

ተጋጣሚው ፉልሃም በበኩሉ÷ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት የሚያደርገው ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በርንሌይ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከ ኤቨርተን ሌሎች በሊጉ የሚደረጉ የዛሬ ጨዋታዎች ናቸው፡፡

ትናንት ምሽት በተደረገ የሊጉ ጨዋታ ዌስትሃም ዩናይትድ ወልቭስን 4 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

ሊጉን አርሰናል በ70 ነጥብ ሲመራው ማንቼስተር ሲቲ 61፣ ማንቼስተር ዩናይትድ 55 እንዲሁም አስቶንቪላ በ54 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡

በወንድማገኝ ጸጋዬ
Пост от 10.04.2026 18:10
1 165
0
2
መቻል ሲዳማ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቻል ሲዳማ ቡናን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

ቀን 10 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ቸርነት ጉግሳ፣ ግሩም ሀጎስ እና በረከት ደስታ የመቻልን የማሸነፊያ ግቦች አስቆጥረዋል።

የሲዳማ ቡናን ብቸኛ ግብ ደግሞ ፍቅረየሱስ ተ/ብርሃን ከመረብ አሳርፏል።

ቀደም ሲል ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ባህርዳር ከተማ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 ማሸነፉ ይታወቃል።
Пост от 09.04.2026 20:08
1 362
0
2
ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ መሳይ ሰለሞን ባለቀ ሰዓት ባስቆጠረው ግብ ወላይታ ድቻ ማሸነፍ ችሏል።

ቀደም ብሎ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 እንዲሁም ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 ሲያሸንፉ÷ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
👍 2
Пост от 09.04.2026 17:06
1
0
0
ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ምኞት ደበበ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከወላይታ ድቻ ይገናኛል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

የነገሌ አርሲን ግብ ኪቲካ ጅማ ሲያስቆጥር የኢትዮጵያ መድንን የአቻነት ግብ ብሩክ በላቸው ከመረብ አሳርፏል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

የሀድያ ሆሳዕናን የመሪነት ግብ ሄኖክ አርፊጮ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥሯል፡፡
Пост от 09.04.2026 17:06
1 323
0
1
ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ምኞት ደበበ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከወላይታ ድቻ ይገናኛል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

የነገሌ አርሲን ግብ ኪቲካ ጅማ ሲያስቆጥር የኢትዮጵያ መድንን የአቻነት ግብ ብሩክ በላቸው ከመረብ አሳርፏል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

የሀድያ ሆሳዕናን የመሪነት ግብ ሄኖክ አርፊጮ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥሯል፡፡
👍 1
Пост от 09.04.2026 08:50
1 680
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ ነገሌ አርሲ ከኢትዮጵያ መድን እንዲሁም ቀን 10 ሰዓት ላይ አርባ ምንጭ ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ይገናኛሉ፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከሀዋሳ ከተማ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከወላይታ ድቻ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Изображение
👍 1
Пост от 08.04.2026 17:18
1 871
0
2
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መቐለ 70 እንደርታን 3 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደርገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ሁዘይፋ ሻፊ እና ናትናኤል (2) ከመረብ አሳርፈዋል።

እንዲሁም ቀደም ብሎ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የተደረገው የኢትዮጵያ ቡና እና ሸገር ከተማ ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።

በጨዋታው የኢትዮጵያ ቡናን ግብ አቡበከር አዳሙ ሲያስቆጥር÷ የሸገር ከተማን ደግሞ አሚር አብዶ ከመረብ አሳርፏል።

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ የተጀመረው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ በቅዱስ ጊዮርጊስ 1 ለ 0 መሪነት የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቅቋል።

እንዲሁም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምድረ ገነት ሽረ ከድሬዳዋ ከተማ ጨዋታውን ያደርጋል።
👍 4
Смотреть все посты