Каталог каналов Каналы в закладках Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.0K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 820
Сегодня
-10
Просмотров на пост
Всего
1 780
ER
Общий
4.44%
Суточный
3.1%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 18 993 постов
Смотреть все посты
Пост от 12.04.2026 13:59
533
0
1
በፓሪስ ማራቶን አትሌት ሹሬ ደምሴ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የፓሪስ ማራቶን ውድድር አትሌት ሹሬ ደምሴ አሸንፋለች።

አትሌት ሹሬ ርቀቱን 2 ሰዓት 18 ደቂቃ ከ35 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ፤ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ምስጋኔ አለማየሁ ርቀቱን 2 ሰዓት 19 ደቂቃ ከ17 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ውድድሩን በ2ኛነት አጠናቅቃለች።

አትሌት እናትነሽ አላምረው ደግሞ 4ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ጨርሳለች።

በወንዶች ምድብ ጣሊያናዊው አትሌት የማነብርሃን ክሪፓ 2 ሰዓት 05 ደቂቃ ከ18 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል።

የማነብርሃንን በመከተል አትሌት ባየልኝ ተሻገር 2 ሰዓት 05 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት 2ኛ ደረጃን ይዟል።
Пост от 12.04.2026 12:03
749
0
1
በአምስቱ የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች የመጀመሪያዋ ሴት አሰልጣኝ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጀርመን ቡንደስሊጋው ክለብ ኡኒየን በርሊን ለዋናው የወንዶች ቡድን ሴት አሰልጣኝ መቅጠሩን ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም አሰልጣኝ ማሪ ሉዊዝ ኤታ በአውሮፓ ውስጥ ካሉ አምስት ታላላቅ ሊጎች የመጀመሪያዋ ሴት የወንዶች ቡድን አሰልጣኝ ሆናለች።

አሰልጣኟ እስከ ውድድር ዓመቱ መጨረሻ ኡኒየን በርሊንን በዋና አሰልጣኝነት የምትመራ ይሆናል፡፡

ኡኒየን በርሊን በቡንደስሊጋው የደረጃ ሰንጠረዥ 32 ነጥብ በመሰብሰብ 11ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
Пост от 12.04.2026 08:26
1 011
0
1
ማንቼስተር ሲቲ ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማጥበብ...

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ሲቲን ያስተናግዳል፡፡

በሊጉ 61 ነጥብ በመሰብሰብ 2ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ማንቼስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 6 ዝቅ ለማድረግ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ያለፉትን ሁለት ተከታታይ የሊጉ ጨዋታዎች አቻ የተለያየው ማንቼስተር ሲቲ ወደ ድል ለመመለስ የሚያደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታን ለማግኘት እየተፋለመ የሚገኘው ቼልሲ በጨዋታው ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ባለሜዳው ቡድን ቼልሲ በሊጉ ከተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ኖቲንግሀም ፎረስት ከአስቶንቪላ፣ ሰንደርላንድ ከቶተንሃም ሆትስፐር እንዲሁም ክሪስታል ፓላስ ከኒውካስል ዩናይትድ በተመሳሳይ ቀን 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Пост от 11.04.2026 09:33
1 609
0
2
አርሰናል ከቦርንማውዝ…

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ አርሰናል በኢምሬትስ ቦርንማውዝን ያስተናግዳል፡፡

የሊጉ መሪ አርሰናል በሊጉ አምስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት እና መሪነቱን ለማጠናከር ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ያለፉትን አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው ተጋጣሚው ቦርንማውዝ በበኩሉ÷ ወደ ድል ለመመለስ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሁለቱም በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ድል ሲያደርጉ በቀሪው አንድ ጨዋታ አቻ ተለያይተዋል፡፡

አርሰናል የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ማንቼስተር ሲቲ እስኪጫወት ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ 12 ከፍ የሚያደርግ ይሆናል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በአንፊልድ ሮድ ፉልሃምን ይገጥማል፡፡

ሊቨርፑል በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ይፋለማል፡፡

ተጋጣሚው ፉልሃም በበኩሉ÷ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት የሚያደርገው ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በርንሌይ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከ ኤቨርተን ሌሎች በሊጉ የሚደረጉ የዛሬ ጨዋታዎች ናቸው፡፡

ትናንት ምሽት በተደረገ የሊጉ ጨዋታ ዌስትሃም ዩናይትድ ወልቭስን 4 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

ሊጉን አርሰናል በ70 ነጥብ ሲመራው ማንቼስተር ሲቲ 61፣ ማንቼስተር ዩናይትድ 55 እንዲሁም አስቶንቪላ በ54 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡

በወንድማገኝ ጸጋዬ
👍 1
Пост от 10.04.2026 18:10
1 496
0
2
መቻል ሲዳማ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቻል ሲዳማ ቡናን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

ቀን 10 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ቸርነት ጉግሳ፣ ግሩም ሀጎስ እና በረከት ደስታ የመቻልን የማሸነፊያ ግቦች አስቆጥረዋል።

የሲዳማ ቡናን ብቸኛ ግብ ደግሞ ፍቅረየሱስ ተ/ብርሃን ከመረብ አሳርፏል።

ቀደም ሲል ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ባህርዳር ከተማ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 ማሸነፉ ይታወቃል።
Пост от 09.04.2026 20:08
1 537
0
2
ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ መሳይ ሰለሞን ባለቀ ሰዓት ባስቆጠረው ግብ ወላይታ ድቻ ማሸነፍ ችሏል።

ቀደም ብሎ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 እንዲሁም ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 ሲያሸንፉ÷ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
👍 2
Пост от 09.04.2026 17:06
1
0
0
ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ምኞት ደበበ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከወላይታ ድቻ ይገናኛል፡፡

በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ነገሌ አርሲ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

የነገሌ አርሲን ግብ ኪቲካ ጅማ ሲያስቆጥር የኢትዮጵያ መድንን የአቻነት ግብ ብሩክ በላቸው ከመረብ አሳርፏል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና አርባ ምንጭ ከተማን 1 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

የሀድያ ሆሳዕናን የመሪነት ግብ ሄኖክ አርፊጮ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥሯል፡፡
Смотреть все посты