Каталог каналов Мои подборки Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.2K
13.6K
186
100
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 433
Сегодня
-11
Просмотров на пост
Всего
1 873
ER
Общий
4.26%
Суточный
3.3%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 214 постов
Смотреть все посты
Пост от 01.05.2026 21:39
822
0
2
"ሊጉን ለማሸነፍ ለመጨረሻዎቹ አራት ጨዋታዎች ዝግጁ ነን" - ሚኬል አርቴታ

"ከኤቨርተን ጋር የምናደርገው ጨዋታ ለእኛ የፍጻሜ ጨዋታ ነው" - ፔፕ ጋርዲዮላ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ ምሽት በሚጀምረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ35ኛ ሳምንት መርሐ ግብር በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝነት ያላቸው ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ከሚቀረው ማንቼስተር ሲቲ በሦስት ነጥብ በልጦ ሊጉን እየመራ የሚገኘው አርሰናል ነገ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢምሬትስ ፉልሃምን ያስተናግዳል፡፡

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ከነገው ጨዋታ በፊት በሰጡት አስተያየት፥ የሊጉን ዋንጫ ለማሸነፍ ስንቅ የሚሆን በቂ ተነሳሽነት አለን ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

የነገውን ጨዋታ ጨምሮ አራቱም ቀሪ ጨዋታዎቻችን ዋንጫውን ለማሸነፍ ወሳኝ በመሆናቸው ለእያንዳንዱ ፈተና ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡

አርሰናል በነገው ጨዋታ ፉልሃምን የሚያሸንፍ ከሆነ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ስድስት ማስፋት ይችላል፡፡

ውሃ ሰማያዊዎቹ በመጪው ሰኞ ምሽት በሂል ዲኪንሰን ስታዲየም ኤቨርተንን የሚገጥሙ ሲሆን፥ ፔፕ ጨዋታው ለእኛ የፍጻሜ ያህል ነው ብለዋል፡፡

አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በሰጡት አስተያየት፥ ከአርሰናል ጋር የስድስት ነጥብ ልዩነት ቢፈጠርም የተለየ ጫና እንደማይፈጥርባቸው ተናግረዋል፡፡
👍 5
Пост от 01.05.2026 18:28
982
0
2
ባህር ዳር ከተማ እና ምድረ ገነት ሽረ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ29ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ባህር ዳር ከተማ እና ምድረ ገነት ሽረ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 10 ላይ በተደረገው ጨዋታ የባህር ዳር ከተማን ግብ ተካልኝ ደጀኔ ሲያስቆጥር የምድረ ገነት ሽረን ግብ ደግሞ ሰለሞን ገ/ክርስቶስ (በራሱ ላይ) ከመረብ አሳርፏል፡፡

አስቀድሞ ቀን 8 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሲዳማ ቡና ያለ ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡

ሊጉን ሲዳማ ቡና በ55 ነጥብ ሲመራው መቻል በ47 እንዲሁም ነገሌ አርሲ በ45 ነጥብ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡

የሊጉን ኮከብ ግብ አስቆጣሪነት አቤል ያለው ከሲዳማ ቡና በ14 ግቦች ሲመራ አዲስ ግደይ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ10 ግቦች ይከተላል፡፡
👍 1
Пост от 01.05.2026 16:23
1 002
0
1
ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሲዳማ ቡና አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ29ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሲዳማ ቡና ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 8 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ወጥተዋል።

በሌላ መርሐ ግብር ባህር ዳር ከተማ እና ምድረ ገነት ሽረ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 10 ላይ ጨዋታቸውን ማድረግ ጀምረዋል።
Изображение
Изображение
Изображение
👍 1
Пост от 01.05.2026 08:41
1 339
0
1
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ29ኛው ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።

በዚሁም ቀን 8 ሰዓት ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሲዳማ ቡና በአዲስ አበባ ስታዲየም ይገናኛሉ።

የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ ቀን 10 ሰዓት ላይ ባህር ዳር ከተማ እና ምድረ ገነት ሽረ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
Пост от 01.05.2026 08:27
1 177
0
1
የቀድሞ ብቃቱ ላይ የማይገኘው ቡካዮ ሳካ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት ዓመታት ለአርሰናል የዋንጫ ተፎካካሪነት ትልቁን ሚና መወጣት የቻለ ተጫዋች ነው ቡካዮ ሳካ፡፡ በፈረንጆቹ 2001 የተወለደው ቡካዮ ሳካ የአርሰናል አካዳሚን የተቀላቀለው ገና የስምንት ዓመት ልጅ እያለ ነበር፡፡ ቡካዮ ሳካ ፕሮፌሽናል ኮንትራቱን በፈረንጆቹ 2010 የተፈራረመ ሲሆን በ17 ዓመቱ ለአርሰናል ዋናው ቡድን የመጀመሪያውን ጨዋታ አድርጓል፡፡ እንግሊዛዊው የፊት…

https://www.fanamc.com/archives/314017
👏 2
Пост от 30.04.2026 17:14
1 278
0
3
ነገሌ አርሲና ፋሲል ከነማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ29ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ነገሌ አርሲ እና ፋሲል ከነማ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ወጥተዋል፡፡

በዚሁ ስታዲየም ኢትዮጵያ ቡና ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ መቐለ 70 እንደርታ እና ሀድያ ሆሳዕና 1 አቻ መለያታቸው ይታወቃል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ላይ መደረግ የጀመረው የአርባ ምንጭ ከተማ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታ ያለ ምንም ግብ ቀጥሏል፡፡
Изображение
Изображение
Пост от 30.04.2026 15:34
1 119
0
2
ሀድያ ሆሳዕና እና መቐለ 70 እንደርታ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ29ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና እና መቐለ 70 እንደርታ አንድ አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታን ግብ ኬኔዲ ገብረፃዲቅ ሲያስቆጥር የሀድያ ሆሳዕናን የአቻነት ግብ ደግሞ ፀጋዓብ ግዛው ከመረብ አሳርፏል።

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል አርባ ምንጭ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀን 10 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡

ነገሌ አርሲ ከፋሲል ከነማ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን የጀመሩ ሲሆን÷ኢትዮጵያ ቡና ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ምሽት 12 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
Изображение
Изображение
Изображение
Изображение
Смотреть все посты