Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.4K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 171
Сегодня
-18
Просмотров на пост
Всего
1 741
ER
Общий
4.14%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 397 постов
Смотреть все посты
Пост от 15.05.2026 15:05
525
0
1
መቐለ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ መድን አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ መድን 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

ቀን 7 ሰዓት ላይ አዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አብዱል ጋንዩ ኢትዮጵያ መድንን መሪ ቢያደርግም ብርሃኑ አዳሙ የመቐለ 70 እንደርታን የአቻነት ግብ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሸገር ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማ ከባህርዳር ከተማ ይገናኛሉ፡፡
Пост от 15.05.2026 14:40
607
0
2
ማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ማይክል ካሪክን በቋሚነት ሊሾም ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ጊዜያዊ አሰልጣኙን ማይክል ካሪክ በቋሚነት ለመሾም የሁለት ዓመት ውል ማቅረቡ ተነግሯል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ በውድድር ዓመቱ አጋማሽ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪምን በማሰናበት ማይክል ካሪክን በጊዜያዊነት መሾሙ ይታወሳል፡፡

ክለቡ በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ እየተመራ ካደረጋቸው 15 ጨዋታዎች በ10ሩ ሲያሸንፍ፥ ሦስቱን አቻ ተለያይቶ ሁለት ጊዜ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡

በዚህም ክለቡ የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ እንዲያረጋግጥ ማስቻሉን ተከትሎ እስከ ፈረንጆቹ 2028 በቋሚነት እንዲያሰለጥን ውል እንደቀረበለት ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ለተጨማሪ አንድ ዓመት በክለቡ የሚያቆይ አማራጭ መካተቱንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
Пост от 15.05.2026 14:21
621
0
3
ብሩኖ ፈርናንዴዝ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብሩኖ ፈርናንዴዝ የማንቼስተር ዩናይትድ የ2025/26 የውድድር ዘመን የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል፡፡

ብሩኖ ፈርናንዴዝ የማንቼስተር ዩናይትድ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ሲያሸንፍ ለአምስተኛ ጊዜ ነው፡፡

ብሩኖ ፈርናንዴዝ በውድድር ዓመቱ በሊጉ ባደረጋቸው 33 ጨዋታዎች 19 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡

በዚህም የ31 ዓመቱ ተጫዋች ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል በውድድር ዓመቱ ቀዳሚው ተጫዋች ነው፡፡

ብሩኖ ፈርናንዴዝ ትናንት ይፋ በተደረገው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ዕጩ ዝርዝር ውስጥ መካተት የቻለ ሲሆን የእግር ኳስ ጸሀፊዎች ማህበር የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ መመረጡ ይታወሳል፡፡
👍 1
👎 1
Пост от 15.05.2026 11:48
862
0
2
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለአሸናፊነት የሚጠበቁበት የሴቶች 10ሺህ ሜትር ሩጫ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና አራተኛ ቀን ውሎ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለተጨማሪ ድል የሚጠበቁበት ውድድር ዛሬ ቀጥሎ ይደረጋል፡፡

ምሽት 2 ሰዓት ከ05 የሴቶች የ10 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር የሚደረግ ሲሆን፥ በርቀቱ ታዳጊዋ ስምረት በርሄ እና አሰፉ አብርሃ ኢትዮጵያን ይውክላሉ።
አትሌቶቹ ቀደም ሲል በሻምፒዮናው የተመዘገበውን ድል ለማስቀጠል ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ውድድር አስቀድሞ ምሽት 1 ሰዓት ከ45 በሚደረገው የወንዶች የ110 ሜትር መሰናክል የማጣሪያ ውድድር አትሌት ጌታሁን ታደሰ ወደ ቀጣዩ ዙር ለማለፍ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል።

ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው ባሳየችው ድንቅ ብቃት እስካሁን በድምሩ 7 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ በደረጃ ሰንጠረዡ አናት ላይ ትገኛለች።

በወርቅነህ ጋሻሁን
Пост от 15.05.2026 11:22
854
0
2
አስቶን ቪላ ከሊቨርፑል - የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎን ለማረጋገጥ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት አስቶን ቪላ ከሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በእኩል 59 ነጥብ በግብ ክፍያ ተበላልጠው በሊጉ 4ኛ እና 5ኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት ሁለቱ ክለቦች ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ይገናኛሉ፡፡

የቀጣይ ዓመት የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፏቸውን ለማረጋገጥ የምሽቱን ጨዋታ ማሸነፍ ለሁለቱም ክለቦች በቂ ነው፡፡

ሁለቱ ክለቦች በሊጉ እርስ በእርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል ሦስቱን ሲያሸንፍ፥ በሁለቱ ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል፡፡
Пост от 15.05.2026 10:14
929
0
3
የፕሪሚየር ሊጉ የወርቅ ዋንጫ ባለቤት…

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ38 ጨዋታዎች ውድድር አንድም ጨዋታ ሳይሸነፍ የወርቅ ዋንጫ ባለቤት መሆን የቻለ ብቸኛ ክለብ ነው። የሰሜን ለንደኑ ክለብ “ዘ ኢንቪንስብል” (የማይበገሩት) በመባል ይህን ደማቅ ታሪክ የጻፈው ከ22 ዓመታት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት ነበር። በወቅቱ በፈረንሳዊው አሰልጣኝ አርሴን ቬንገር የሚመሩት መድፈኞቹ በሊጉ እስከዛሬም…

https://www.fanamc.com/archives/314898
Пост от 15.05.2026 10:14
899
0
2
ለ3ኛ ተከታታይ የውድድር ዓመት የፈረንሳይ ሊግ ሻምፒዮን – አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ለተከታታይ 3ኛ የውድድር ዓመት ከፒኤስጂ ጋር የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫን ማሸነፍ ችለዋል፡፡ በፈረንጆቹ 1970 ስፔን ውስጥ በዛሬው ዕለት የተወለዱት አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የአሰልጣኝነት ስራቸውን የጀመሩት በባርሴሎና ቢ ቡድን ነው፡፡ ከባርሴሎና ቢ ቡድን በመቀጠል ሮማ እና ሴልታቪጎን ያሰለጠኑት አሰልጣኙ በፈረንጆቹ 2014 የባርሴሎና ዋናውን…

https://www.fanamc.com/archives/314895
Смотреть все посты