Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
16.6K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
39 610
Сегодня
-31
Просмотров на пост
Всего
1 130
ER
Общий
2.91%
Суточный
3.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 16633 постов
Смотреть все посты
Пост от 12.01.2026 12:42
1 172
0
0
የማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ለመሆን የተቃረበው ማይክል ካሪክ… አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞው የማንቼስተር ዩናይትድ ተጫዋች ማይክል ካሪክ እስከ ወድድር ዓመቱ መጨረሻ ክለቡን በጊዜያዊ አሰልጣኝነት ለመረከብ መቃረቡ እየተነገረ ይገኛል፡፡ ማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪምን ካሰናበተ በኋላ በቀድሞ ተጫዋቹ ዳረን ፍሌቸር እየተመራ ሁለት ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን፥ በትናንትናው ዕለት በብራይተን ተሸንፎ ከኤፍ ኤ ዋንጫ ተሰናብቷል፡፡ ከሩበን አሞሪም ስንብት በኋላ በርካታ አሰልጣኞች በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት ኃላፊነቱን እንደሚረከቡ ስማቸው እየተነሳ ይገኛል፡፡ በተለይም የቀድሞ የክለቡ ተጫዋችና አሰልጣኝ ኦሊጉነር ሶልሻየር እና ማይክል ካሪክ ከክለቡ ኃላፊዎች ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን በርካታ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡ ክለቡ ቀጣዩን አሰልጣኝ በቀጣይ ሁለት ቀናት ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግ የተገለጸ ሲሆን፥ የ44 ዓመቱ ማይክል ካሪክ የተሻለ እድል እንዳለው ቢቢሲ እና ዘ አትሌቲክ አስነብበዋል፡፡ ማይክል ካሪክ የሻምፒየንሺፑን ክለብ ሚድልስቦሮ ለ2 ዓመት ከግማሽ ማሰልጠኑ የሚታወስ ሲሆን ባሳለፍነው ክረምት ከክለቡ ጋር መለያየቱ አይዘነጋም፡፡
👎 4
Пост от 12.01.2026 00:06
1 366
0
2
ባርሴሎና የስፔን ሱፐር ካፕ ሻምፒዮን ሆነ አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኤልክላሲኮ ደርቢ ባርሴሎና ሪያል ማድሪድን በማሸነፍ የስፔን ሱፐር ካፕ ሻምፒዮን ሆኗል። በሳዑዲ አረቢያ በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ባርሴሎና ሪያል ማድሪድን 3 ለ 2 አሸንፏል። የካታሉንን ክለብ ግቦች ራፊንሃ (2) እና ሌዋንዶውስኪ ሲያስቆጥሩ፥ ማድሪድን ከሽንፈት ያልታደጉትን ግቦች ቪኒሺየስ ጁኒየር እና ጎንዛሎ ጋርሺያ ከመረብ አሳርፈዋል። ውጤቱን ተከትሎ ባርሴሎና የዋንጫው ባለቤት መሆን ችሏል።
👍 2
Пост от 11.01.2026 10:50
1 257
0
3
የ’ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ’ የሩጫ ውድድር በደብረብርሃን ተካሄደ አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የ’ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክ 2018’ የሩጫ ውድድር በደብረብርሃን ከተማ ተካሂዷል። ውድድሩ ከዚህ በፊት በአራት የተለያዩ ከተሞች ይደረግ የነበረ ሲሆን በዚህ ዓመት ደብረብርሃን እና ሀረርን በማካተት በስድስት ከተሞች ይደረጋል። በስፖርት ቱሪዝምን ማስተዋወቅ የውድድሩ አንድ አካል ሲሆን ተሳታፊዎች በአንኮበር ቤተ መንግሥት ጉብኝት አድርገዋል። በውድድሩ በወንዶች አትሌት ‎ስጦታው ሰማኸኝ፣ ቦጋለ ሰለሞን እና አየለ ከበደ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ አጠናቅቀዋል። በሴቶች ደግሞ አትሌት አማረች ገብሬ፣ ደመቅ ጥላሁን እና የዘብነሽ ወንዴ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ውድድሩን ጨርሰዋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 5ኛ ደረጃን ይዘው ላጠናቀቁ አትሌቶች የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በእንዳልካቸው ወዳጄ
👍 2
🙏 1
Пост от 10.01.2026 22:09
1 365
0
1
የፌስቡክ የስፖርት ገጻችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/share/1EModWytp6/
Пост от 10.01.2026 21:43
1 009
0
3
በየዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የብር ሜዳሊያ አገኘች አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ46ኛው የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና በአዋቂ ወንዶች 10 ሺህ ሜትር ሩጫ ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። አትሌት በሪሁ አረጋዊ 28 ደቂቃ ከ36 ሰኮንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ የብር ሜዳሊያውን ማስገኘት ችሏል። እንዲሁም በዚሁ ውድድር ታደሰ ወርቁ 4ኛ እንዲሁም ቢኒያም መሃሪ 6ኛ በመውጣት አጠናቅቀዋል። በተጨማሪም ቀደም ብሎ በአዋቂ ሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሩጫ ኢትዮጵያ ሁለተኛውን ነሃስ እንዲሁም በቡድን ወርቅ ሜዳሊያ ማግኘት ችላለች። በዚህም አትሌት ሰናይት ጌታቸው 3ኛ ደረጃን በመያዝ የነሃስ ሜዳሊያ ስታስገኝ አትሌት አሳየች አይቸው 4ኛ፣ አትሌት አለሺኝ ባወቀ 5ኛ እንዲሁም አትሌት ዓለም ንጉስ 7ኛ ደረጃን ይዘው ጨርሰዋል። በሻምፒዮናው ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ውድድር አትሌት ማርታ አለማየሁ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ወርቅ ሜዳልያ አስገኝታለች። እንዲሁም አትሌት ወሰኔ አሰፋ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳልያ ስታስገኝ አትሌት የኔነሽ ሽመክት አምስተኛ ደረጃን በመያዝ ማጠናቀቅ ችላለች።
🙏 2
Пост от 10.01.2026 21:14
1 001
0
1
ናይጄሪያ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀለች አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ናይጄሪያ አልጄሪያን 2 ለ 0 አሸንፋለች። ምሽት 1 ሰዓት በተካሄደው ጨዋታ ናይጄሪያ አልጄሪያን በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀሏን አረጋግጣለች። በጨዋታው የናይጄሪያን ማሸነፊያ ግቦችን ቪክቶር ኦሲሜን እና አኮር አዳምስ ከመረብ ጋር አገናኝተዋል። ይህንንም ተከትሎ ናይጄሪያ ካሜሩንን በማሸነፍ የግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀል ከቻለችው ሞሮኮ ጋር በግማሽ ፍጻሜ ትገናኛለች። የሩብ ፍጻሜ የመጨረሻ ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ግብጽ ከኮትዲቯር ያደርጋሉ።
Пост от 10.01.2026 20:09
1 002
0
0
ኢትዮጵያ መድን ወላይታ ድቻን አሸነፈ አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ14ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 አሸንፏል። በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ የኢትዮጵያ መድንን የማሸነፊያ ግቦች በረከት ካሌብ እና ብሩክ ሙሉጌታ አስቆጥረዋል። ወላይታ ድቻን ከመሸነፍ ያላዳነችውን ብቸኛ ግብ ደግሞ ቴዎድሮስ ሀ/ማርያም ከመረብ አሳርፏል። በሊጉ ቀደም ሲል በተካሄዱ ጨዋታዎች ባሕር ዳር ከተማ መቻልን 2 ለ 1 እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና ፋሲል ከነማን 2 ለ 0 ሲያሸንፉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሀድያ ሆሳዕና 0 ለ 0 ተለያይተዋል።
Смотреть все посты