Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.5K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
37 062
Сегодня
-15
Просмотров на пост
Всего
1 736
ER
Общий
4.34%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 467 постов
Смотреть все посты
Пост от 19.05.2026 20:44
355
0
1
የዋንጫው ባለቤት ዛሬ ይታወቃል ወይስ…

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘንድሮው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ባለቤት የሚሆነውን ክለብ ሊወስን የሚችለው የቦርንማውዝ እና ማንቼስተር ሲቲ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ይደረጋል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ የምሽቱን ጨዋታ አቻ ካጠናቀቀ ወይም ሽንፈት ካስተናገደ አርሰናል አንድ ጨዋታ እየቀረው የ2025/26 ሻምፒዮን መሆኑን ዛሬ ምሽት ያረጋግጣል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ተስፋውን እስከ መጨረሻው ሳምንት ለማስቀጠል የምሽቱን ጨዋታ የማሸነፍ ግዴታ ውስጥ ገብቷል፡፡

በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከሲቲ ጋር እንደሚለያዩ የሚጠበቁት ፔፕ ጋርዲዮላ በምሽቱ ጨዋታ የሚጠቀሙት ቋሚ አሰላለፍ ይፋ ሆኗል፡፡

ጂያንሉጂ ዶናሩማ፣ ማቲያስ ኑኔዝ፣ ኩሳኖቭ፣ ማርክ ጉሂ፣ ኒኮ ኦ'ሬሊ፣ ሮድሪ፣ ኮቫቺች፣ በርናርዶ ሲልቫ፣ ሴሜንዮ፣ ዶኩ እና ሀላንድ በቋሚነት ወደ ሜዳ ይገባሉ፡፡

ባለሜዳው ክለብ ቦርንማውዝ ፔትሮቪች፣ ትሩፌርት፣ ሴኔሲ፣ ስኮት፣ ኢቫኒልሰን፣ አዳምስ፣ ስሚዝ፣ ታቨርኔር፣ ክሩፒ ጁኒየር፣ ሂል እና ራያንን በቋሚ አሰላለፍ ይጠቀማል፡፡

ጨዋታው ምሽት 3 ሰዓት ከ30 የሚጀመር ሲሆን፥ የ47 ዓመቱ አንቶኒ ቴይለር በመሃል ዳኝነት ይመሩታል፡፡

በሌላ ጨዋታ በለንደን ደርቢ ቼልሲ በሊጉ ለመቆየት 1 ነጥብ የሚፈልገውን ቶተንሃም ሆትስፐር ምሽት 4 ሰዓት ከ15 በስታምፎርድ ብሪጅ ያስተናግዳል፡፡
Пост от 19.05.2026 18:21
430
0
1
ባህርዳር ከተማ እና መቻል አቻ ተለያዩ

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ባህርዳር ከተማ እና መቻል 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የባህርዳር ከተማን ግብ አንተነህ ተፈራ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል፡፡

የመቻል የአቻነት ግብ ፈቱዲን ጀማል (በፍጹም ቅጣት ምት) በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም የተደረገው የሀድያ ሆሳዕና እና ኢትዮጵያ ንግድ ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡

አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በተመሳሳይ ስታዲየም የተገናኙት ኢትዮጵያ መድን እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 19.05.2026 16:10
796
0
1
6ኛ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎውን የሚያደርገው ክርስቲያኖ ሮናልዶ

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ በ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ የሚጠቀሙትን የመጨረሻ ስብስብ በዛሬው ዕለት ይፋ አድርገዋል፡፡

አሰልጣኙ ይፋ ባደረጉት የመጨረሻ ስብስባቸው ውስጥ የአምስት ጊዜ የባሎንዶር አሸናፊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ተካትቷል፡፡

በዚህም የብሔራዊ ቡድኑ አምበል ሮናልዶ 6ኛ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎውን የሚያደርግ ይሆናል፡፡

የ41 ዓመቱ ተጫዋች በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አዘጋጅነት በሚካሄደው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ወድድር በፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ማልያ የመጨረሻው መሆኑ ይታወቃል፡፡
Пост от 19.05.2026 15:56
746
0
1
የ2027ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የ2027ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ በማጣሪያው በምድብ 10 ከሴኔጋል፣ ሱዳን እና ሞዛምቢክ ጋር ተደልድላለች፡፡

ከየምድቡ 1ኛ እና 2ኛ ሆነው የሚያጠናቅቁ ቡድኖች ሦስቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ኬንያ፣ ታንዛኒያ እና ኡጋንዳ በጋራ ለሚያዘጋጁት የ2027ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ማለፋቸውን ያረጋግጣሉ፡፡

በምድብ ማጣሪያው የውድድሩን አዘጋጅ ሀገራት ጨምሮ 48 ሀገራት የሚሳተፉ ሲሆን፥ የምድብ ማጣሪያዎቹ በቀጣዩ ዓመት መስከረም ወር መካሄድ ይጀምራሉ፡፡
Пост от 19.05.2026 15:09
759
0
1
ኢትዮጵያ መድን እና ወላይታ ድቻ አቻ ተለያዩ

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛው ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ነው ጨዋታቸውን ያጠናቀቁት፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይገናኛሉ፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ባሕር ዳር ከተማ ከመቻል ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Пост от 19.05.2026 13:08
835
0
2
አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላን የሚተኩት ኢንዞ ማሬስካ….

‎አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ጋር የሚለያየው ማንቼስተር ሲቲ በምትካቸው ጣሊያናዊውን አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በኃላፊነት ለመሾም ከስምምነት ደርሷል፡፡

በማንቼስተር ሲቲ ቤት የ10 ዓመታት ቆይታቸው 20 ዋንጫዎችን ማሳካት የቻሉት አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የፊታችን እሁድ የመጨረሻ ጨዋታቸውን የሚመሩ ይሆናል፡፡

በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኙት ፔፕ በዚህ የውድድር ዓመት የካራባኦ እና የኤፍ ኤ ዋንጫዎችን ማሳካታቸው ይታወቃል፡፡

ጋርዲዮላን የሚተኩት ኢንዞ ማሬስካ በ2022/23 የውድድር ዓመት ማንቼስተር ሲቲ የሦስትዮሽ ዋንጫ ሲያሳካ የቡድኑ ምክትል አሰልጣኝ እንደነበሩ ይታወሳል፡፡

የ46 ዓመቱ የቀድሞ የቼልሲ እና ሌስተር ሲቲ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በማንቼስተር ሲቲ እስከ ፈረንጆቹ 2029 ድረስ የሚያቆያቸውን ውል እንደሚፈራረሙ ቢቢሲ ስፖርት ዘግቧል፡፡

ጣሊያናዊው አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በቼልሲ በነበራቸው ቆይታ የዓለም ክለቦች እና የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ዋንጫዎችን አሳክተዋል፡፡

ፔፕ ከዚህ ቀደም ስለ ኢንዞ ማሬስካ በሰጡት አስተያየት፥ ከዓለም ምርጥ አሰልጣኞች አንዱ ነው በማለት አድናቆታቸውን ገልጸው ነበር፡፡
Пост от 19.05.2026 12:13
807
0
1
ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ የእውቅና እና የሽልማት መርሐ ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተሳታፊ ለነበረው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን የእውቅና እና የሽልማት መርሐ ግብር ተካሂዷል።

በመርሐ ግብሩ በውድድሩ የወርቅ ሜዳሊያ ላስመዘገቡ አትሌቶች 40 ሺህ፣ ለብር ሜዳሊያ 25 ሺህ እና ለነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊዎች 10 ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት እና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

ለአሰልጣኞችም አትሌቶቻቸው እንዳስመዘገቡት የውጤት አይነት የገንዘብ ሽልማት ተሰጥቷቸዋል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በጋና አክራ የተመዘገበው አኩሪ ውጤት በትኩረት ከተሰራ ለውጥ መፍጠር እንደሚቻል ማሳያ ነው።

እየተሻሻለ የመጣው የአትሌቲክስ መሰረተ ልማት ግንባታ አትሌቶችን ጥሩ ውጤት እንዲያስመዘግቡ እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በቀጣይ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ ፌዴሬሽኑ ከአትሌቶች፣ አሰልጣኞች እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡

በዳንኤል እንዳለ
Смотреть все посты