Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 472
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
1 921
ER
Общий
4.84%
Суточный
3.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 869 постов
Смотреть все посты
Пост от 06.07.2026 17:39
1
0
0
ጆርዳን ሄንደርሰን ከዓለም ዋንጫ ውጪ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው ተጫዋች ጆርዳን ሄንደርሰን ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ ሆኗል፡፡

የብሬንትፎርዱ አማካኝ ትላንት ምሽት እንግሊዝ ሜክሲኮን 3 ለ 2 ባሸነፈችበት ጨዋታ የማስታወቂያ ቦርድ ለመዝለል ሲሞክር ወድቆ መጎዳቱ ተመላክቷል፡፡

በዚህም ተጫዋቹ ቀዶ ጥገና እንደሚያስፈልገው እና እንግሊዝ በቀጣይ ከምታደርጋቸው ከዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ውጪ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

ከጉዳቱ በኋላ ሄንደርሰን ወደ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን÷ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ማረፊያ አለመመለሱም ነው የተገለጸው፡፡

የ36 ዓመቱ ተጫዋች በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ 6 ደቂቃ ብቻ ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ግልጋሎት ሰጥቷል፡፡
Пост от 06.07.2026 13:39
1
0
0
ቶተንሃም ሆትስፐር ሳንድሮ ቶናሊን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር ጣሊያናዊውን ተጫዋች ሳንድሮ ቶናሊን ከኒውካስል ዩናይትድ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር የክለቡን የዝውውር ክብረ ወሰን በመስበር በ100 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ሒሳብ ተጫዋቹን የግሉ አድርጓል፡፡

የ26 ዓመቱ ተጫዋች በሰሜን ለንደኑ ክለብ እስከ ፈረንጆቹ 2032 ድረስ የሚያቆየውን ውል ነው የተፈራረመው፡፡

ሳንድሮ ቶናሊ በፈረንጆቹ 2023 ኒውካስል ዩናይትድን የተቀላቀለ ሲሆን÷ 110 ጨዋታዎችን አድርጎ 10 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

ተጫዋቹ በኒውካስል ዩናይትድ ቆይታው የካራባኦ ካፕ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል፡፡
Пост от 06.07.2026 10:41
1
0
0
ከብራዚል ብሔራዊ ቡድን በይፋ መሰናበቱን ያሳወቀው ኔይማር ጁኒየር…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ብራዚል ትናንት ምሽት በኖርዌይ ያልተጠበቀ ሽንፈት አስተናግዳ ከውድድሩ ተሰናብታለች፡፡

በጨዋታው 67ኛ ደቂቃ ላይ ጋብሬል ማርቲኔሊን ተክቶ ወደ ሜዳ የገባው ኔይማር ዳ ሲልቫ ሳንቶስ ጁኒየር ብራዚልን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡

ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በከፍተኛ ሀዘን የተስተዋለው ኔይማር ጁኒየር ራሱን ከብሔራዊ ቡድኑ ማግለሉን በእንባ ታጅቦ ይፋ አደርጓል፡፡

የ34 አመቱ ተጫዋች "ከብራዚል ጋር ዋንጫ ለማሳካት ብዙ ሞክሬያለው፤ ከቡድኑ ጋር በዚሁ ሜትላይፍ ስታዲየም የጀመርኩትን ሙከራ በዚሁ ስታዲየም ቋጭቼያለሁ" ሲል ተደምጧል፡፡

ኔይማር 80 ግቦችን ለብሔራዊ ቡድኑ በማስቆጠር የሀገሩ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሲሆን፥ የዘንድሮውን ጨምሮ በ2014፣ 2018 እና 2022ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ላይ ብራዚልን በመወከል አራት ጊዜ መጫወት ችሏል፡፡

በድንቅ ተሰጥኦው፣ ቄንጠኛ አጨዋወቱና ግብ አስቆጣሪነቱ የሚታወቀው ኔይማር በታሪክ የሚታወሱ ድንቅ የተጫዋችነት ጊዜያትን ማሳለፍ ችሏል፡፡

በአቤል ነዋይ
Пост от 05.07.2026 09:57
57
0
1
በዩጂን ዳይመንድ ሊግና በፒችትሪ የጎዳና ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የፕሪፎንቴይን ክላሲክ - ዩጂን ዳይመንድ ሊግ እና በአሜሪካ የፒችትሪ የጎዳና ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል።

በአሜሪካዋ ዩጂን በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ የሁለት ማይል ርቀት ውድድር አትሌት አለሺኝ ባወቀ በቀዳሚነት አጠናቅቃለች፡፡

አትሌቷ ውድድሩን በበላይነት ያጠናቀቀችው የወቅቱ ፈጣን የሆነ ሰዓት 9 ደቂቃ ከ20 ሴኮንድ ከ02 ማይክሮ ሴኮንድ በማስመዝገብ ነው፡፡

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሒሩት መሸሻ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ውድድሯን ጨርሳለች፡፡

በዚሁ ርቀት የተሳተፉት አትሌት ማርታ አለማየሁ 4ኛ፣ አትሌት የኔዋ ንብረት 7ኛ እንዲሁም አትሌት አሳየች አይቼው 8ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቅቀዋል።

በሌላ በኩል የአሜሪካ የነጻነት ቀን ክብረ በዓል አካል ሆኖ በተካሄደው በ57ኛው የፒችትሪ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ በ31:02 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሯን በበላይነት አጠናቅቃለች።

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት መልክናት ውዱ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን ጨርሳለች፡፡
Пост от 05.07.2026 09:32
1
0
0
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ የመዝጊያ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ጨዋታ በዛሬው ዕለት ይደረጋል፡፡

በዚህም የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በሚያደርጉት ጨዋታ የውድድር ዓመቱ ፍጻሜውን ያገኛል፡፡

የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ቀን 10 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋል።

ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ወደ 71 ከፍ ማድረግ ይችላል፡፡

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ድል የሚያደርግ ከሆነ ደግሞ ነጥቡን 54 በማድረስ 5ኛ ደረጃን ይዞ ውድድር ዓመቱን የሚያጠናቅቅ ይሆናል፡፡

ምድረ ገነት ሽረ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና አርባ ምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊጉ የወረዱ ቡድኖች ናቸው፡፡
Пост от 05.07.2026 09:12
1
0
0
ብራዚል ከኖርዌይ፤ እንግሊዝ ከሜክሲኮ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜውን ለመቀላቀል የሚደረጉ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

የአምስት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊ ብራዚል ምሽት 5 ሰዓት ላይ ከኖርዌይ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ብራዚል ጃፓንን እንዲሁም ተጋጣሚዋ ኖርዌይ ደግሞ ኮትዲቫርን በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡

በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ውድድር 4 ግቦችን ያስቆጠረው ቪኒሸስ ጁኒየር በብራዚል ብሔራዊ ቡድን በኩል ተጠባቂው ተጫዋች ነው፡፡

በሌላ በኩል አምስት ግቦችን ማስቆጠር የቻለው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ ሌላኛው በዛሬው ጨዋታ የሚጠበቅ ተጫዋች ነው፡፡

በሌላ መርሐ ግብር አዘጋጇ ሀገር ሜክሲኮ ሌሊት 9 ሰዓት ላይ ከእንግሊዝ ጋር ትገናኛለች፡፡

አንድም ግብ ሳይቆጠርባት ሁሉንም ጨዋታዎች በማሸነፍ እዚህ የደረሰችው ሜክሲኮ በዛሬው ጨዋታ ለእንግሊዝ ትልቅ ፈተና ትሆናለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን እንዲሁም ሜክሲኮ ኢኳዶርን በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡

እንግሊዝ ከፈረንጆቹ 1966 በኋላ የዓለም ዋንጫን ለማሳካት የምታደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ወደ ሜዳ የምትገባ ይሆናል፡፡

አምስት ግቦችን በማስቆጠር ለወርቅ ጫማው እየተፋለመ የሚገኘው እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሃሪ ኬን በጨዋታው ይጠበቃል፡፡
Пост от 04.07.2026 22:06
46
0
1
ሞሮኮ ካናዳን በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሞሮኮ አዘጋጇን ካናዳ 3 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡

የሞሮኮን የማሸነፊያ ግቦች ኡናሂ (ሁለት) እና ራሂሚ ከመረብ አሳርፈዋል።
Смотреть все посты