Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
12.0K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
39 271
Сегодня
-10
Просмотров на пост
Всего
1 860
ER
Общий
4.33%
Суточный
3.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 11 960 постов
Смотреть все посты
Пост от 09.02.2026 17:09
821
0
2
ሀዲያ ሆሳዕና ፋሲል ከነማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ16ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ የጨዋታ መርሐ ግብር ሀዲያ ሆሳዕና ፋሲል ከነማን 1ለ0 አሸንፏል።

በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የሀዲያ ሆሳዕናን የማሸነፊያ ግብ ሱራፌል ተመስገን ከእረፍት መልስ በ60ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

ያለፉትን 3 ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው ሀዲያ ሆሳዕና የዛሬውን ጨዋታ በማሸነፍ ነጥቡን ወደ 24 ከፍ በማድረግ ደረጃውን አሻሽሏል።

ፋሲል ከነማ በበኩሉ 33 ነጥብን በመያዝ በሊጉ 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
Пост от 09.02.2026 09:49
1 219
0
1
ፋሲል ከነማ የሊጉ መሪ ለመሆን የሚያደርገው ፍልሚያ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ16ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ከሀድያ ሆሳዕና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ፋሲል ከነማ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ወደ 36 ከፍ በማድረግ ሊጉን መምራት ይጀምራል፡፡

ያለፉትን 3 ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻለው ሀድያ ሆሳዕና በበኩሉ ድል የሚያደርግ ከሆነ ነጥቡን ወደ 24 ከፍ በማድረግ ደረጃውን ማሻሻል ይችላል፡፡

የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም መደረግ ይጀምራል፡፡
Изображение
Изображение
Пост от 09.02.2026 08:45
1 159
0
1
በእግር ኳስ ሕይወቱ 13ኛ ክለቡን የተቀላቀለው ሮድሪጌዝ…

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ2014 የብራዚል ዓለም ዋንጫ በኋላ በምርጥ ብቃቱ መቀጠል ያልቻለ ተጫዋች ነው ኮሎምቢያዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሀሜስ ሮድሪጌዝ፡፡

በፈረንጆቹ 1991 የተወለደው ሀሜስ ሮድሪጌዝ እግር ኳስን መጫወት የጀመረው በሀገሩ ክለብ ኢንቪጋዶ ነው፡፡

ከዚያ በመቀጠል በተለያዩ ሊጎችና ክለቦች መጫወት የቻለ ሲሆን የተጠበቀውን ያህል ውጤታማ መሆን አልቻለም፡፡

ሀሜስ ለሪያል ማድሪድ፣ ባየርን ሙኒክ፣ ፖርቶ፣ ሞናኮ፣ ኤቨርተን እና ኦሎምፒያኮስን ለመሳሳሉ ክለቦች ተጫውቶ አሳልፏል፡፡

ተጫዋቹ እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትን ጨምሮ ለተለያዩ ክለቦች ተጫውቶ ቢያሳልፍም በእግር ኳስ ሕይወቱ ምርጡን ጊዜ ያሳለፈው ከሀገሩ ኮሎምቢያ ጋር በ2014ቱ የዓለም ዋንጫ ነው፡፡

በፈረንጆቹ 2014 በብራዚል አስተናጋጅነት በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ክስተት ከነበሩ ተጫዋቾች መካከል ኮሎምቢያዊው ሀሜስ ሮድሪጌዝ ትልቁ ክስተት ነበር፡፡

በወቅቱ ጀርመን ዋንጫውን ስታሸንፍ ሀሜስ ሮድሪጌዝ ደግሞ የስፖርት ቤተሰቡን ልብ ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

በወቅቱ 22 ዓመቱ ላይ ይገኝ የነበረው ተጫዋቹ ብራዚላውያን በደገሱት የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ በውብ ግቦች ደጋፊውን እያዝናና የእርሱን ያህል የነገሰ አልነበረም።

በውድድሩ ከሀገሩ ጋር እስከ ሩብ ፍጻሜ መጓዝ የቻለ ሲሆን፥ ስድስት ግቦችን በማስቆጠር የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን የወርቅ ጫማ አሸናፊም ነበር፡፡
👇
https://web.facebook.com/fanasport/posts/pfbid0EYwCrksKnwVU3KEYd7Eapi841GmFkRYPHP9Kqn7WQtJGZN7dU8XKv9s73Tn1gTaZl
Изображение
Пост от 09.02.2026 08:44
962
0
1
በፈረንሳይ ሜትዝ በተደረገው የቤት ውስጥ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንሳይ ሜትዝ በተከናወነው የሴቶች 3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል።

በዓለም አትሌቲክስ የብር ሜዳልያ በተሰጠው የቤት ውስጥ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከአንድ እስከ ሦስት ተከታትሎ በመግባት ድል ተጎናጽፏል።
በዚህም አትሌት ብርቱካን ሞላ በ8:40.49 በመግባት ውድድሩን ስታሸንፍ÷ አትሌት ሽቶ ጉሜ በ8:41.18 2ኛ፣ አትሌት በ8:41.75 3ኛ ደረጃ በመያዝ ተከታትለው ገብተዋል።

ትናንት በተካሄደው በዚህ ውድድር የተሳተፈችው ሌላኛዋ አትሌት ቤተልሔም ኦላና 6ኛ ደረጃ ይዛ አጠናቅቃለች።

በወንዶች ምድብ አትሌት አብዲሳ ፈይሳ በ7:44.83 በመግባት ሶስተኛ፣ አትሌት ኤርሚያስ ግርማ በ7:51.80 አምስተኛ፣ አትሌት ለሚ ተሾመ በ7:55.07 ሰባተኛ ደረጃ በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቅቀዋል።
Изображение
Пост от 08.02.2026 21:34
1 489
0
3
ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 2 ለ 1 አሸንፏል።

የማንቼስተር ሲቲን ግቦች በርናርዶ ሲልቫ እና ሀላንድ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥረዋል።

ባለሜዳውን ሊቨርፑል ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ከመረብ ያሳረፈው ዶሚኒክ ሶቦዝላይ በጨዋታው መገባደጃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።

ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የዘጠኝ ነጥብ ልዩነት ወደ ስድስት ማጥበብ ችሏል።

ፕሪሚየር ሊጉን አርሰናል በ56 ነጥቦች ሲመራ፥ ማንቼስተር ሲቲ በ6 ነጥቦች ዝቅ ብሎ ይከተላል።

አስቶን ቪላ በ47፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ44፣ ቼልሲ በ43 እንዲሁም ሊቨርፑል በ39 ነጥብ ከ3 እስከ 6 ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
Изображение
Изображение
👍 12
👎 2
Пост от 08.02.2026 19:29
1 662
0
1
የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ15 የስፖርት አይነቶች በጅማ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 10ኛው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል ተጠናቋል፡፡

አዘጋጁ ጅማ ዩኒቨርሲቲ 21 የወርቅ ሜዳልያዎችን ጨምሮ 128 ሜዳልያዎችን በመሰብሰብ እንዲሁም አምስት ዋንጫዎችን በማንሳት ውድድሩን በበላይነት ማጠናቀቅ ችሏል፡፡

በመዝጊያ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ፥ የፌስቲቫሉ ዋነኛ ዓላማ ስብዕናው የተገነባ፣ ስነምግባር ያለውና የአካል ጤንነቱ የዳበረ ዜጋ መፍጠር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲዎች የየአካባቢያቸውን ባህልና ወግና የሚያንጸባርቁ ሁነቶችን በማስተዋወቅ ለፌስቲቫሉ ድምቀት በመሆናቸው ምስጋና ይገባቸዋል ነው ያሉት፡፡

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ታይተው፣ ተሰምተውና ተቀምሰው የማይጠገቡ ባህሎች ያሏቸው ህዝቦች ሀገር መሆኗን ያንጸባረቀ ፌስቲቫል መሆኑን ተናግረዋል።

ስፖርተኞቹ በጅማ ከተማ ቆይታቸው ከስፖርታዊ ክንውኖች ባሻገር በዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አቀፍ የበጎ ፍቃድ አገልግሎቶች ላይ መሳተፋቸውን አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ስፖርት ማህበር ፕሬዚዳንት አባይ በላይሁን በፌስቲቫሉ ላይ የባህል ልውውጥ መካሄዱን ገልጸው፥ የታየውን አብሮነትና ስፖርታዊ ፍቅር ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ 11ኛውን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል እንዲያዘጋጅ ተመርጧል፡፡

በወርቅአፈራው ያለው
Изображение
Пост от 08.02.2026 19:07
1 451
0
1
ክሪስታል ፓላስ ብራይተንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ክሪስታል ፓላስ ብራይተንን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ዛሬ ቀን 11 ሰዓት ላይ በአሜክስ ስታዲየም በተደረገው የኤም-23 ደርቢ ጨዋታ የእንግዳውን ቡድን ክሪስታል ፓላስ የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ኢስማኤላ ሳር አስቆጥሯል፡፡

ሊቨርፑል ማንቼስተር ሲቲን የሚያስተናግድበት የሳምንቱ ተጠባቂና የመጨረሻ መርሐ ግብር ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በአንፊልድ ይጀምራል፡፡
Изображение
Изображение
👍 4
Смотреть все посты