Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.5K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 890
Сегодня
-7
Просмотров на пост
Всего
1 819
ER
Общий
4.46%
Суточный
3.8%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 533 постов
Смотреть все посты
Пост от 24.05.2026 21:15
545
0
3
ሻምፒዮኑ አርሰናል ዋንጫውን ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው አርሰናል በዛሬው ዕለት ዋንጫውን ተረክቧል፡፡

ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል÷ በዚህ ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡

በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመራው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ የሊጉን የመጨረሻ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ከክሪስታል ፓላስ ጋር በማድረግ 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

በጨዋታው የአርሰናልን ግቦች ጄሱስ እና ማዱኬ ሲያስቆጥሩ ማቴታ የክሪስታል ፓላስን ግብ ከመረብ አሳርፏል።

በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የቡድን ግንባታ ሒደት ከ22 ዓመታት በኋላ ከሊጉ ዋንጫ ጋር የተገናኙት መድፈኞቹ ዛሬ ምሽት በሴልኸረስት ፓርክ ነው ዋንጫውን በክብር የተቀበሉት፡፡
👍 1
👏 1
Пост от 24.05.2026 20:10
893
0
2
ዌስትሃም ዩናይትድ ከ14 ዓመታት በኋላ ከፕሪሚየር ሊጉ ወረደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዌስትሃም ዩናይትድ ከ14 ዓመታት በኋላ ወልቭስ እና በርንሌይን ተከትሎ ከፕሪሚየር ሊጉ ወርዷል።

በፈረንጆቹ 2012/13 የውድድር ዓመት ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ያደገው የለንደኑ ክለብ ወደ ሻምፒዮንሺፕ ተሰናብቷል።

በውድድር ዓመቱ አብዛኛውን ጊዜ ከሊጉ ላለመውረድ ሲጫወት የነበረው ቶተንሃም በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል።
Пост от 24.05.2026 20:09
711
0
2
ቼልሲ ከአውሮፓ ውድድሮች ውጪ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ከቀጣይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ መድረክ ውድድሮች ውጪ ሆኗል።

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2025/26 የውድድር ዓመት ዛሬ ፍጻሜውን አግኝቷል።

በዚህም መሰረት ሻምፒዮኑን አርሰናል ጨምሮ ማንቼስተር ሲቲ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ፣ አስቶን ቪላ እና ሊቨርፑል በቀጣይ ዓመት በሻምፒየንስ ሊጉ የሚሳተፉ የእንግሊዝ ክለቦች ናቸው።

ቦርንማውዝ እና ሰንደርላንድ የዩሮፓ ሊግ ተሳታፊ መሆናቸውን ሲያረጋግጡ፥ ብራይተን የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ተሳታፊ መሆኑን አረጋግጧል።

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ 10ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ ከቀጣይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ መድረክ ውድድሮች ውጪ ሆኗል።
Пост от 24.05.2026 19:08
765
0
1
የመጨረሻው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ የመጀመሪያው አጋማሽ...

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመጨረሻው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያው አጋማሽ ጨዋታ በአርሰናል፣ ማንቼስቴር ዩናይትድ፣ ማንቼስተር ሲቲና ሰንደርላንድ መሪነት ወደ እረፍት አምርቷል።

ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ክሪስታል ፓላስን የገጠመው የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል በጄሱስ ግብ 1 ለ 0 በመምረት ወደ መልበሻ ክፍል አምርቷል።

ማንቼስተር ሲቲ አስቶን ቪላ 1 ለ 0 በመምራት ወደ እረፍት ያመሩ ሲሆን÷ የሲቲን ግብ ሴሜንዮ አስቆጥሯል።

እንዲሁም ማንቼስተር ዩናይትድ ዶርጉና ምቤሞ ባስቆጠሯቸው ግቦች ብራይተንን 2 ለ 0 በመምራት ወደ እረፍት ወጥተዋል።

ሰንደርላንድ ቼልሲን 1 ለ 0 ፣ ቶተንሀም ኤቨርተንን 1 ለ 0 በመምራት ወደ መልበሻ ክፍል ያመሩ ሲሆን÷ ዌስትሀም እና ሊድስ ዩናይትድ እንዲሁም ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ያለ ግብ የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቅቀዋል።
👍 1
Пост от 24.05.2026 19:03
875
0
1
ብሩኖ ፈርናንዴሽ የፕሪሚየር ሊጉን ክብረወሰን የግሉ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብሩኖ ፈርናንዴሽ በአንድ የውድድር ዓመት 21 ግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል የሊጉን ክብረወሰን የግሉ አደረገ።

ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ የ2025/26 የውድድር ዓመት የመጨረሻ ጨዋታ ብራይተንን 2 ለ ዐ እየመራ የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቅቋል።

በጨዋታው ላይ ፖርቹጋላዊው አማካይ አንድ ግብ የሆነ ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።

በዚህም በውድድር ዓመቱ በጠቅላላ 21 ግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ከዚህ ቀደም በቲዬሪ ሄንሪ እና ኬቨን ዲብሮይነ የተያዘውን የ20 ግቦች ክብረወሰን አሻሽሏል።
👏 1
Пост от 24.05.2026 13:00
1 109
0
3
በኬፕ ታውን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳንላም ኬፕ ታውን የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸንፈዋል፡፡

በወንዶች አትሌት መሀመድ ኢሳ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ55 ሴኮንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል፡፡

በርቀቱ የተሳተፈው ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ይሁንልኝ አዳነ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ59 ሴኮንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ውድድሩን ጨርሷል፡፡

በሴቶች ደግሞ አትሌት ደራ ዲዳ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ18 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት በመግባት 1ኛ በመሆን አጠናቅቃለች፡፡

በርቀቱ የተሳተፉት ሌሎች ኢትየጵያዊያን አትሌቶች መስታወት ፍቅር እና ዋጋነሽ አማረ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን ጨርሰዋል፡፡
👍 1
Пост от 24.05.2026 09:57
1 208
0
1
ቶተንሃም ወይስ ዌስትሃም - ከሊጉ ማን ይወርዳል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዓመት ዛሬ ምሽት 12 ሰዓት በሚደረጉ ጨዋታዎች ፍጻሜውን ያገኛል፡፡

በዛሬ ዕለት ወልቭስ እና በርንሌይን ተከትሎ ወደ ሻምፒዮንሺፕ የሚወርደው ሦስተኛ ቡድን የሚለይባቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ፡፡

በአሰልጣኝ ሮቤርቶ ዲዘርቢ የሚመራው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር በሜዳው ኤቨርተንን ያስተናግዳል፡፡

ከፈረንጆቹ 1977 በኋላ ከእንግሊዝ ዋናው ሊግ የመውረድ ስጋት ያለበት የሰሜን ለንደኑ ክለብ ከጨዋታው አንድ ነጥብ የሚያገኝ ከሆነ በሊጉ መቆየቱን ያረጋግጣል፡፡

ሌላኛው የለንደን ክለብ ዌስትሃም ዩናይትድ ወደ ሻምፒዮንሺፕ የመውረድ ስጋት ያለበት ሲሆን፥ በሜዳው ከሊድስ ዩናይትድ ጋር ይፋለማል፡፡

ዌስትሃም ዩናይትድ በሊጉ ለመቆየት የራሱን ጨዋታ አሸንፎ የቶተንሃም ሆትስፐርን መሸነፍ ይጠብቃል።
Смотреть все посты