Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.7K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 464
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 125
ER
Общий
5.16%
Суточный
3.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 743 постов
Смотреть все посты
Пост от 23.06.2026 22:02
2
0
1
ፖርቹጋል ኡዝቤኪስታንን 5 ለ ዐ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ 2ኛ ዙር ጨዋታ ፖርቹጋል ኡዝቤኪስታንን 5 ለ ዐ አሸነፈች፡፡

ምሽት 2 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ የፖርቹጋልን ግቦች ክርስቲያኖ ሮናልዶ (2)፣ ሜንዴዝ፣ ሊያዮ እና ኔማቶቭ (በራሱ መረብ ላይ) አስቆጥረዋል፡፡

ፖርቹጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ6 የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል፡፡
Пост от 23.06.2026 21:10
1
0
0
ሮናልዶ አዳዲስ ታሪክ በጻፈበት ጨዋታ ፖርቹጋል 3 ለ 0 እየመራች ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ 2ኛ ዙር ጨዋታ ፖርቹጋል ኡዝቤኪስታንን 3 ለ 0 እየመራች የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቅቃለች፡፡

ምሽት 2 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ የፖርቹጋልን ግቦች ክርስቲያኖ ሮናልዶ (2) እና ሜንዴዝ አስቆጥረዋል፡፡

ፖርቹጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ6 የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል፡፡

በተጨማሪም በዓለም ዋንጫው ያስቆጠራቸውን የግቦች መጠን ወደ 10 ከፍ በማድረግ በመድረኩ የምንጊዜም የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኗል፡፡

41 ዓመት ከ138 ቀናት ዕድሜው ላይ የሚገኘው ተጫዋቹ በዓለም ዋንጫ ውድድር ግብ ያስቆጠረ 2ኛው በዕድሜ ትልቁ ተጫዋች ሆኗል ፡፡

ሮጀር ሚላ ከዚህ ቀደም በ42 ዓመት ከ39 ቀናት በዓለም ዋንጫ ግብ በማሰቆጠር በዕድሜ ትልቁ ተጫዋች በመሆን በቀዳሚነት የተቀመጠው ተጫዋች ነው፡፡

የአምስት ጊዜ የባሎንዶር አሸናፊው ሮናልዶ በእግር ኳስ ሕይወቱ ያስቆጠረውን የግብ ብዛት 975 አድርሷል፡፡
Пост от 23.06.2026 20:36
198
0
1
በ6 የዓለም ዋንጫ ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች - ሮናልዶ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፖርቹጋላዊው ኮከብ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በስድስት የዓለም ዋንጫ ውድድር ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል፡፡

ምሽት 2 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው የዓለም ዋንጫ የምድብ 2ኛ ዙር ጨዋታ ፖርቹጋል ኡዝቤኪስታንን በሮናልዶ እና ሜንዴዝ ግቦች 2 ለ 0 እየመራች ነው፡፡

የፖርቹጋል የመሪነት ግብ ያስቆጠረው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በስድስት የዓለም ዋንጫ ውድድር ግብ ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ጽፏል፡፡

ክርስቲያኖ ሮናልዶ በዓለም ዋንጫው ያስቆጠራቸውን የግቦች መጠን ወደ 9 ከፍ አድርጓል፡፡

ሮናልዶ በእግር ኳስ ሕይወቱ ያስቆጠረውን የግብ ብዛት 974 አድርሷል፡፡
Пост от 23.06.2026 11:47
1
0
0
ዶኩ በድጋሚ የቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ስብስብን ይቀላቀላል

‎አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመጀመሪያ ልጁ ሲወለድ ለማየት ብሔራዊ ቡድኑን በመተው ወደ ለንደን ያቀናው ጄሬሚ ዶኩ በድጋሚ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ስብስብ ይመለሳል፡፡

ከዓለም ዋንጫ የብሔራዊ ቡድኑን ስብስብ ጥሎ መውጣቱን ተከትሎ በርካታ ትችቶችን ያስተናገደው ዶኩ ፕሬይዝ የተባለ የወንድ ልጅ አባት ሆኗል፡፡

ተጫዋቹ ልጁ ሲወለድ ከባለቤቱ ጎን ለመሆን በመወሰኑ በአንጻሩ ከብዙሃኑ አድናቆትን አትርፏል፡፡

ቤልጂየም ከዚህ በኋላ በምታደርጋቸው የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች የዶኩን ግልጋሎት የምታገኝ ይሆናል፡፡

ቤልጂየም የምድብ 3ኛ ጨዋታዋን ከኒውዝላንድ ጋር የፊታችን ቅዳሜ ታደርጋለች፡፡

እስካሁን በውድድሩ አንድም ጨዋታ ድል ያላደረገቸው ቤልጂየም በምድቡ 2 ነጥብ ይዛ 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡
Пост от 23.06.2026 11:15
1
0
0
@FMCSport
Пост от 23.06.2026 10:56
1
0
0
እንግሊዝ ከጋና…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ ዛሬ ምሽት እንግሊዝ ከጋና ይገናኛሉ፡፡

በምድብ 12 የሚገኙት እንግሊዝ እና ጋና በምድቡ የመጀመሪያ ጨዋታዎቻቸውን ማሸነፍ የቻሉ ሲሆን፥ የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ የሚያሸንፈው ብሔራዊ ቡድን 32ቱን መቀላቀሉን ያረጋግጣል፡፡

በአሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል የሚመራው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ክሮሽያን ባሸነፈበት ጨዋታ ባሳየው ድንቅ እንቅስቃሴ በውድድሩ ውጤታማ ጊዜን ያሳልፋሉ ተብለው ከሚጠበቁ ቡድኖች መካካል አንዱ ሆኗል፡፡

አንቱዋን ሴሜኒዮን የመሳሰሉ ከዋክብት የያዘችው ምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ጋና ለሦስቱ አናብስት ብርቱ ፈተና እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡

በዚሁ ምድብ ውድድራቸውን በሽንፈት የጀመሩት ክሮሽያ እና ፓናማ በዓለም ዋንጫው የመጀመሪያ ነጥብ ለማግኘት እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ቀደም ብሎ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በምድብ 11 የምትገኘው ፖርቹጋል ከኡዝቤኪስታን ጋር ትጫወታለች፡፡

https://web.facebook.com/share/p/199n2iFihD/
Пост от 22.06.2026 22:19
1
0
0
አርጀንቲና ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ 2ኛ ጨዋታ አርጀንቲና ኦስትሪያን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች።

የአርጀንቲናን ሁለቱንም የማሸነፊያ ግቦች ሊዮኔል ሜሲ ከመረብ አሳርፏል።

ይህን ተከትሎም አርጀንቲና ስድስት ነጥቦችን በመሰብሰብ ከወዲሁ ወደ ጥሎ ማለፉ መቀላቀሏን አረጋግጣለች።

ሜሲ በዓለም ዋንጫ ታሪክ 18 ግቦችን በማስቆጠር የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረ ወሰንን መስበር ችሏል።
Смотреть все посты