Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Тарифы
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.1K
13.6K
209
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 677
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 314
ER
Общий
6.31%
Суточный
4.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 105 постов
Смотреть все посты
Пост от 31.08.2026 18:27
1
0
0
ሊዮኔል ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ራሱን አገለለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊዮኔል ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ራሱን ማግለሉን ይፋ አድርጓል።

ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ጋር የዓለም ዋንጫ እና የኮፓ አሜሪካ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል።

ሜሲ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን 207 ጨዋታዎችን አድርጎ 125 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን ÷ 68 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ደግሞ አመቻችቶ አቀብሏል።
Пост от 31.08.2026 16:35
1
0
0
ሊቨርፑል ባርኮላን ከፒኤስጂ አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊቨርፑል ፈረንሳዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ብራድሊ ባርኮላን ከፒኤስጂ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ፈረንሳዊው ተጫዋች በመርሲሳይዱ ክለብ ለአምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

ሊቨርፑል ለዝውውሩ 125 ሚሊየን ዩሮ ክፍያ የፈጸመ ሲሆን፤ የተጫዋቹ ብቃት እየታየ ደግሞ ተጨማሪ 20 ሚሊየን ዩሮ ክፍያ የሚከፍል ይሆናል።

የ23 ዓመቱ ተጫዋች በፒኤስጂ በነበረው ቆይታ 153 ጨዋታዎችን አድርጎ 39 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

በሌላ በኩል ማንቼስተር ሲቲ ብራዚላዊውን የመስመር ተጫዋች አላን ኤሊያስን ከፓልሜራስ አስፈርሟል፡፡

አላን በማንቼስተር ሲቲ ቤት ለአምስት ዓመታት የሚያቆውን ውል መፈራረሙ ነው የተገለጸው፡፡

ማንቼስተር ሲቲ ለ22 ዓመቱ ተጫዋች 40 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሂሳብ ወጪ አድርጓል፡፡

አላን ለፓልሜራስ ባደረጋቸው 96 ጨዋታዎች 9 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ኤሊዮት አንደርሰን፣ እና አዩብ ቡአዲን ማስፈረሙ ይታወሳል፡፡
Пост от 31.08.2026 10:41
931
0
2
አስቶን ቪላ ከአርሰናል - የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር የአምናው ሻምፒዮን አርሰናል ከሜዳው ውጭ አስቶን ቪላን ይገጥማል፡፡

መድፈኞቹ ኮቨንትሪ ሲቲን በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን የጀመሩ ሲሆን፤ ባለሜዳው ቪላ በበኩሉ በብራይተን በሰፊ የግብ ልዩነት ሽንፈት ማስተናገዱ ይታወሳል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ድል የቀናቸው ሲሆን፤ በቀሪው አንድ ጨዋታ ነጥብ ተጋርተዋል፡፡

ሁለቱን ቡድኖች የሚያገናኘው የሊጉ የሁለተኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ይደረጋል፡፡
Пост от 30.08.2026 17:00
658
0
1
ባርሴሎና ጋብሬል ጄሱስን ለማስፈረም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ባርሴሎና ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ጋብሬል ጄሱስን ከአርሰናል ለማስፈረም ተስማምቷል።

ባርሴሎና ለተጨዋቹ ዝውውር 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ያቀረበ ሲሆን፣ በአርሰናል በኩል ጥያቄው ተቀባይነት ማግኘቱን ስካይ ስፖርት ዘግቧል።

ብራዚላዊው ተጫዋች የሕክምና ምርመራውን ለማድረግ እና በይፋ ውሉን ለመፈረም በነገው ዕለት ወደ ስፔን የሚያመራ ይሆናል።
Пост от 30.08.2026 11:44
293
0
1
ቼልሲ አርጀንቲናዊውን ግብ ጠባቂ ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ አርጀንቲናዊውን ግብ ጠባቂ ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝን ከአስቶንቪላ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝ በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለቼልሲ ለሁለት ዓመት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

ቼልሲ ለ33 ዓመቱ ግብ ጠባቂ ዝውውር 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ አድርጓል፡፡

ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝ በአስቶንቪላ በነበረው ቆይታ ለቡድኑ 256 ጨዋታዎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ቼልሲ በክረምቱ የተጫቾች የዝውውር መስኮት ዳኒ ዌልቤክ እና ጆርዳን ሄንደርሰንን የመሳሳሉ ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች ማስፈረሙ ይታወሳል፡፡

በሁለተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ዛሬ ቀን 10 ሰዓት ላይ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ብራይተንን ያስተናግዳል፡፡
Пост от 30.08.2026 10:35
1
0
0
ዩናይትድ የመጀመሪያ ድሉን ለማሳካት

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሁለተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።

በዚህም ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልድትራፎርድ ኢፕስዊች ታውንን ያስተናግዳል።

በመጀመሪያ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ በሃል ሲቲ ሽንፈት የገጠመው ማንቼስተር ዩናይትድ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል ለማሳካት ወደ ሜዳ ይገባል።

ማንቼስተር ዩናይትድ ከዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ በተመለሰው ሃል ሲቲ መሸነፉን ተከትሎ የቡድኑ ብቃት ላይ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል።

በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የሚመሩት ቀያይ ሰይጣኖቹ በቀጣይ ጨዋታዎች የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ይጠበቃል።

በ2025/26 የውድድር ዘመን በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ስር መሻሻሎችን ማሳየቱ ይታወሳል።

ማንቼስተር ዩናይትድ በ2025/26 የውድድር ዓመት በካሪክ ስር ያሳየውን መሻሻል በዚህኛው የውድድር ዓመት ይበልጥ እንዲያሳድገውም በደጋፊዎች ዘንድ ይጠበቃል።

https://www.facebook.com/share/p/1BUSa1gHy1/?mibextid=wwXIfr
Пост от 30.08.2026 08:18
387
0
1
በሲድኒ ማራቶን አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲድኒ ማራቶን ኢትዮዽያዊው አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፏል።

ትናንት ምሽት ለ24ኛ ጊዜ በተካሄደው የማራቶን ውድድር አትሌት አዲሱ ጎበና 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ42 ሰከንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል።

አትሌቱ የገባበት ሰዓትም የቦታው ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።

በውድድሩ ጭምዴሳ ደበሌ 2ኛ፣ ጀማል መኮንን 5ኛ እንዲሁም የባለፈው ዓመት የርቀቱ አሸናፊ ኃይለማርያም ኪሮስ 6ኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን ጨርሰዋል።

በሴቶች ደግሞ ኬንያዊቷ አትሌት ፒርስ ጅፕችርችር በቀዳሚነት ውድድሩን አጠናቅቃለች።

በርቀቱ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሹሬ ደምሴ፣ ሄቨን ሀይሉ እና መሰረት አበባየሁ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ውድድራቸውን ማጠናቀቃቸውን ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
Смотреть все посты