Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Тарифы
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
54.0K
13.6K
380
258
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 611
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 591
ER
Общий
7.07%
Суточный
4.53%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 54 047 постов
Смотреть все посты
Пост от 12.09.2026 13:06
864
0
2
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ 7 ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በአራተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት 7 ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዚህም ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

በሊጉ እስካሁን ድረስ ሁሉንም ጨዋታዎች ያሸነፈው አርሰናል ተከታታይ 4ኛ ድሉን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ባለሜዳው ሰንደርላንድ በበኩሉ ወደ ድል ለመመለስ የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሁሉም ውድድር እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል አራቱን በማሸነፍ የበላይነት አለው፡፡ በቀሪው አንድ ጨዋታ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል፡፡

ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ቼልሲ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ሃል ሲቲን ያስተናግዳል፡፡

ከሁለት ተከታታይ ድል በኋላ በ3ኛ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ ሽንፈት የገጠመው ቼልሲ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

እስካሁን በሊጉ ያልተሸነፈው ተጋጣሚው ሃል ሲቲ በበኩሉ ያለመሸነፍ ጉዞውን ለማጠናከር ይፋለማል፡፡

በተመሳሳይ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ፉልሃምን ያስተናግዳል፡፡

በ3ኛ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ የመጀመሪያ ድሉን ያሳካው ሊቨርፑል ተከታታይ ድሉን ለማሳካት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡

ተጋጣሚው ፉልሃም በበኩሉ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል ለማሳካት ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

ቦርንማውዝ ከብሬንትፎርድ፣ አስቶንቪላ ከኖቲንግሃም ፎረስት እንዲሁም ክሪስታል ፓላስ ከኢፕስዊች ታውን በተመሳሳይ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡

ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ቶተንሃም ሆትስፐር ከኤቨርተን ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Пост от 10.09.2026 10:25
476
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ ከሳባህ ኤፍኬ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የመጀመሪያ ዙር መርሐ ግብር ዛሬ ስድስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

የሦስት ጊዜ የመድረኩ ባለክብር ማንቼስተር ዩናይትድ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከአዘርባጃኑ ሳባህ ኤፍኬ ጋር ያደርጋል፡፡

ከሁለት የውድድር ዓመት በኋላ ወደ መድረኩ የተመለሱት ዩናይትዶች ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኦልድትራፎርድ በሚያደርጉት ጨዋታ የውድድር ዓመቱን ይጀምራሉ፡፡

ባየርን ሙኒክ ከቦዶ ግሊምት፣ ኮሞ ከአርቢ ሌፕዚግ፣ ስላቪያ ፕራሃ ከሎንስ በተመሳሳይ 4 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡

ከእነዚህ ጨዋታዎች አስቀድሞ ምሽት 1 ሰዓት ከ45 ላይ ፌነርባቼ ከሮማ እንዲሁም ፒኤስቪ ከሻካታር ዶኔስክ ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Пост от 10.09.2026 02:12
436
0
1
አርሰናል ናፖሊን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታዎች አርሰናል ናፖሊን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የአርሰናልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ማርቲን ኦዴጋርድ አስቆጥሯል።

በሌላ ጨዋታ የወቅቱ ሻምፒዮን ፒኤስጂ ስሎቫን ብራቲስላቫን 6 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።

የፒኤስጂን የማሸነፊያ ግቦች ፌራን ቶሬስ (3)፣ ኦስማን ዴምቤሌ (2) እንዲሁም ቀሪዋን አንድ ግብ ደግሞ ሩሂዝ ከመረብ አሳርፈዋል።

ሊቨርፑል አትሌቲኮ ማድሪድን 2 ለ 1 ፣ባርሴሎና ፌይኖርድን 5 ለ 1 እንዲሁም ስፖርቲንግ ሊዝበን ጋላታሳራይን 3 ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።
Пост от 09.09.2026 17:17
1
0
0
የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በ7 ከተሞች ይደረጋል

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በ7 ከተሞች ይደረጋል አለ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር፡፡

ሊግ ካምፓኒው ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጸው፤ የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በ7 ከተሞች በሚገኙ ሰባት ስታዲየሞች ይካሄዳል፡፡

አዲስ አበባ ስታዲየም፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም፣ ባህር ዳር ከተማ ስታዲየም፣ አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ አባያ ካሞፓስ ስታዲየም፣ ሆሳዕና አብዬ ኤርሳሞ ስታዲየም እና ሀላባ ስታዲየም ሊጉ የሚደረግባቸው ስታዲየሞች ናቸው።

የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር የእጣ ማውጣት ሥነ ስርዓት መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም እንደሚከናወን ተመላክቷል፡፡

መስከረም 30 ቀን 2019 ዓ.ም አዲሱ የውድድር ዓመት የሚጀምር ይሆናል፡፡

በእንዳልካቸው ወዳጄ
Пост от 06.09.2026 18:11
213
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድና ኤቨርተን አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሦስተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ እና ኤቨርተን 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

የማንቼስተር ዩናይትድን ግቦች ብሪያን ምቤሞ እና ቤንጃሚን ሼሽኮ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

የኤቨርተንን የአቻነት ግቦች ደግሞ ታይሪክ ጆርጅ እና ሚትላንድ ኔልስ አስቆጥረዋል፡፡
Пост от 06.09.2026 08:04
668
0
1
አርሰናል ከቼልሲ - የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 01፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጠናቀቃል።

በዚህም ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ አርሰናል በሜዳው ኢምሬትስ ቼልሲን ያስተናግዳል፡፡

የሊጉን የዋንጫ ቅድመ ግምት አግኝቶ የውድድር ዓመቱን የጀመረው አርሰናል በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፉ ይታወሳል።

በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመሩት መድፈኞቹ በሊጉ ሦስተኛ ተከታታይ ድላቸውን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገቡ ይሆናል።

በአሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ እየተመራ የውድድር ዓመቱን የጀመረው ቼልሲ በሊጉ ተከታታይ 3ኛ ድሉን ለማሳካት እያለመ ወደ ኢምሬትስ ያቀናል፡፡

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ እንደ ተጋጣሚው አርሰናል ሁሉ በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል ማድረጉ አይዘነጋም፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሁሉም ውድድር እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል አራቱን በማሸነፍ የበላይነት አለው።

በቀሪው አንድ ጨዋታ ደግሞ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው።

ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ኤቨርተንን ይገጥማል።

https://www.facebook.com/share/p/199HoiXvV6/?mibextid=wwXIfr
Пост от 06.09.2026 08:03
1
0
0
አርሰናል ከቼልሲ - የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 01፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጠናቀቃል።

በዚህም ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ አርሰናል በሜዳው ኢምሬትስ ቼልሲን ያስተናግዳል፡፡

የሊጉን የዋንጫ ቅድመ ግምት አግኝቶ የውድድር ዓመቱን የጀመረው አርሰናል በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፉ ይታወሳል።

በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመሩት መድፈኞቹ በሊጉ ሦስተኛ ተከታታይ ድላቸውን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገቡ ይሆናል።

በአሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ እየተመራ የውድድር ዓመቱን የጀመረው ቼልሲ በሊጉ ተከታታይ 3ኛ ድሉን ለማሳካት እያለመ ወደ ኢምሬትስ ያቀናል፡፡

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ እንደ ተጋጣሚው አርሰናል ሁሉ በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል ማድረጉ አይዘነጋም፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሁሉም ውድድር እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል አራቱን በማሸነፍ የበላይነት አለው።

በቀሪው አንድ ጨዋታ ደግሞ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው።

ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ኤቨርተንን ይገጥማል።

https://www.facebook.com/share/p/199HoiXvV6/?mibextid=wwXIfr
Смотреть все посты