Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.1K
13.6K
208
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 663
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 435
ER
Общий
6.66%
Суточный
4.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 059 постов
Смотреть все посты
Пост от 21.08.2026 21:19
142
0
2
አርሰናል ከኮቨንትሪ ሲቲ - ቋሚ አሰላለፍ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2026/27 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከደቂቃዎች በኋላ በይፋ ይጀመራል፡፡

የአምናው የሊጉ ባለክብር አርሰናል በፍራንክ ላምፓርድ የሚመራውን የሻምፒዮንሺፑ ሻምፒዮን ኮቨንትሪ ሲቲ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኤሚሬትስ ያስተናግዳል፡፡

ሁለቱ ክለቦች ቋሚ አሰላለፋቸውን ይፋ ያደረጉ ሲሆን፤ የመድፈኞቹ የክረምቱ ፈራሚ ክሪስቶስ ሶሊስ በቋሚነት ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

ዴቪድ ራያ፣ ቤን ዋይት፣ ሞስኬራ፣ ጋብሬል ማጋሌሽ፣ ካላፊዮሪ፣ ዴክለን ራይስ፣ ሊውስ ስኬሊ፣ ኦዴጋርድ፣ ሳካ፣ ሶሊስ እና ካይ ሀቨርት በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ምርጥ 11 ውስጥ ተካትተዋል፡፡

ራሽወርዝ፣ ቫን ኤዊክ፣ ቶማስ፣ አሜንዳ፣ ዶሲልቫ፣ ግሪምስ፣ ኦኒዬካ፣ ቻውና፣ ቶማስ አሳንቴ፣ ሲምስ አርሰናልን በሚገጥመው የኮቨንትሪ ሲቲ ቋሚ አሰላለፍ የተካተቱ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

የፋና ስፖርት የፌስቡክ እና ቴሌግራም ገጾችን ይወዳጁ

ፌስቡክ https://web.facebook.com/fanasport
ቴሌግራም ?? telemetr.me/FMCSport
Пост от 21.08.2026 20:56
1
0
0
ከሊጎች ሁሉ የሚልቀው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዓለማችን ታላቁ፤ ተወዳጁ እና በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ተመልካች ያለው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲሱ የውድድር ዘመን ዛሬ በይፋ ጅማሮውን ያደርጋል።

በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በጉጉት የሚጠብቁት ይህ ሊግ ዛሬ የደረሰበት የኃያልነት እና የተወዳጅነት ማማ ላይ ከመድረሱ በፊት በርካታ ታሪካዊ ምዕራፎችን አሳልፏል።

በፈረንጆቹ እስከ 1992 ድረስ የእንግሊዝ እግር ኳስ በዋናነት በ"እንግሊዝ እግር ኳስ ሊግ አንደኛ ዲቪዚዮን" ስር ነበር የሚተዳደረው።

ሆኖም በወቅቱ የነበሩ ታላላቅ ክለቦች ከቴሌቪዥን ስርጭት እና ከስፖንሰርሺፕ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ራሱን የቻለ ሊግ ለመመስረት በመወሰናቸው 22 ክለቦችን በማሳተፍ በፈረንጆቹ 1992 በይፋ ተመሰረተ፡፡

ከፈረንጆቹ 1992 ጀምሮ ማንቼስተር ዩናይትድ 13 የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን በማንሳት በሊጉ ታሪክ ቀዳሚው ክለብ ነው።

በዚህ የሊግ ውድድር አርሰናል ሙሉ የውድድር ዘመኑን ያለ ምንም ሽንፈት አጠናቅቆ የዋንጫ ባለቤት በመሆን ደማቅ ታሪክ ጽፎበታል።

https://web.facebook.com/share/p/1DV7tHdpp8/
Пост от 21.08.2026 18:58
363
0
0
አርሰናልን የተቀላቀልኩት ዋንጫዎችን ለማሸነፍ ነው - ኤዝሪ ኮንሳ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል እንግሊዛዊውን ተከላካይ ኤዝሪ ኮንሳ ከአስቶን ቪላ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

የ28 ዓመቱ ተጫዋች ለመድፈኞቹ ፊርማውን ካኖረ በኋላ በሰጠው አስተያየት፥ እዚህ የተገኘሁት ለአሸናፊነት ነው፤ ዋንጫዎችን ማሸነፍ እፈልጋለሁ ሲል ተደምጧል፡፡

በዓለማችን ካሉ ምርጥ ክለቦች አንዱ የሆነውን አርሰናል መቀላቀል ለእኔ ትልቅ ክብር ነው ያለው ተጫዋቹ፤ የክለቡን ስኬት ለማስቀጠል ያለኝን ሁሉ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ ሲል ተደምጧል፡፡

ኮንሳ በሰሜን ለንደኑ ክለብ ለአራት ዓመታት የሚያቆየውን ውል የፈረመ ሲሆን፤ 15 ቁጥር ማሊያ እንደሚለብስ ክለቡ ይፋ አድርጓል፡፡

የፋና ስፖርት የፌስቡክ እና ቴሌግራም ገጾችን ይወዳጁ

ፌስቡክ 👉 https://web.facebook.com/fanasport
ቴሌግራም 👉 telemetr.me/FMCSport
Изображение
Пост от 21.08.2026 18:58
1
0
0
አርሰናልን የተቀላቀልኩት ዋንጫዎችን ለማሸነፍ ነው - ኤዝሪ ኮንሳ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል እንግሊዛዊውን ተከላካይ ኤዝሪ ኮንሳ ከአስቶን ቪላ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

የ28 ዓመቱ ተጫዋች ለመድፈኞቹ ፊርማውን ካኖረ በኋላ በሰጠው አስተያየት፥ እዚህ የተገኘሁት ለአሸናፊነት ነው፤ ዋንጫዎችን ማሸነፍ እፈልጋለሁ ሲል ተደምጧል፡፡

በዓለማችን ካሉ ምርጥ ክለቦች አንዱ የሆነውን አርሰናል መቀላቀል ለእኔ ትልቅ ክብር ነው ያለው ተጫዋቹ፤ የክለቡን ስኬት ለማስቀጠል ያለኝን ሁሉ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ ሲል ተደምጧል፡፡

ኮንሳ በሰሜን ለንደኑ ክለብ ለአራት ዓመታት የሚያቆየውን ውል የፈረመ ሲሆን፤ 15 ቁጥር ማሊያ እንደሚለብስ ክለቡ ይፋ አድርጓል፡፡

የፋና ስፖርት የፌስቡክ እና ቴሌግራም ገጾችን ይወዳጁ

ፌስቡክ 👉 https://web.facebook.com/fanasport
ቴሌግራም 👉 telemetr.me/FMCSport
Пост от 21.08.2026 13:06
1
0
0
ስታዲየሞችን በስቱዲዮዋችን!

ዛሬ ከምሽቱ⏱️ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ ዞላ ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር 'በሞዛይክ ስፖርት' ፋና ኤፍ ኤም 98.1 ላይ በቀጥታ ስርጭት ወደ እናንተ ይደርሳል

የ2026/27 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻ ጨዋታ

🥅 ኤምሬትስ ስቴድየም

🔴 አርሰናል ከ ኮቨንትሪ ሲቲ 🔵

✍️ ሀሳብና ግምታችሁን አጋሩን!
Пост от 21.08.2026 09:36
624
0
1
ቶተንሀም ሆትሰፐር ሳቪንሆን ለማስፈረም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቶተንሃም ሆትስፐር ሳቪንሆን ከማንቼስተር ሲቲ ለማስፈረም ተስማምቷል፡፡

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ለ22 ዓመቱ ብራዚላዊ የመስመር አጥቂ ዝውውር 75 ሚሊየን ፓውንድና ብቃቱ እየታየ የሚጨመር 10 ሚሊየን ፓውንድ የሚከፍል ይሆናል።

ሳቪንሆ ከስፐርስ ጋር ለረጅም ጊዜ ውል ከመፈራረሙ በፊት የሕክምና ምርመራውን በመጠባበቅ ላይ መሆኑን ቢቢሲ ስፖርት ዘግቧል፡፡

ተጫዋቹ ለማንቼስተር ሲቲ ባደረጋቸው 36 ጨዋታዎች 4 ግቦችን በማስቆጠር፤ 2 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል፡፡

የፋና ስፖርት የፌስቡክ እና ቴሌግራም ገጾችን ይወዳጁ

ፌስቡክ https://web.facebook.com/fanasport
ቴሌግራም telemetr.me/FMCSport
Изображение
Пост от 21.08.2026 07:29
1
0
0
ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የውድድር ዘመን ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ሻምፒዮኑ አርሰናል ከኮቨንትሪ ሲቲ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል።

ባለፈው የውድድር ዓመት የሊጉን ዘውድ የተቀዳጀው የሰሜን ለንደኑ ክለብ በተከታታይ ዓመት ሻምፒዮን ለመሆን በፍራንክ ላምፓርድ የሚመራውን ኮቨንትሪ ሲቲ በመግጠም ጉዞውን ይጀምራል።

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸውን ለማጠናከር በክረምቱ የዝውውር መስኮት እንደ ብሩኖ ጉማሬሽ፣ ክሪስቶስ ሶሊስ እና ኤዝሪ ኮንሳ ያሉ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸው ቀላቅለዋል።

በሌላ በኩል ማንቸስተር ሲቲዎች ከአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ጋር ከተለያዩ በኋላ በቀድሞ ምክትላቸው ኤንዞ ማሬስካ እየተመሩ አዲስ ምዕራፍ ይጀምራሉ።

የግብ ማሽኑን ኧርሊንግ ሃላንድን የያዘው ሲቲ፡ ኤሊዮት አንደርሰንን ጨምሮ አዳዲስ ተጫዋቾችን በማስፈረም ጠንካራ ተፎካካሪነቱን ለማስቀጠል ተዘጋጅቷል።

ሞሐመድ ሳላህን ጨምሮ ከወሳኝ ተጫዋቾቹ ጋር የተለያየው ሊቨርፑል በአንዶኒ ኢራኦላ እየተመራ የውድድር ዓመቱን ይጀምራል።

በማይክል ካሪክ የሚመራው ማንቸስተር ዩናይትድ በበኩሉ ባለፈው የውድድር ዘመን ያሳየውን መሻሻል ለማስቀጠል በሊጉ ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች በመጨመር ወደ ፉክክሩ ይመለሳል።

ባለፈው የውድድር ዓመት ደካማ ጊዜ ያሳለፈው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ በአዲሱ አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ እየተመራ በደረጃ ሰንጠረዡ ወደ ፊት በመምጣት ጠንካራ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ሀል ሲቲ ከማንቸስተር ዩናይትድ፣ ኒውካስል ዩናይትድ ከሊቨርፑል እና ፉልሃም ከቼልሲ እንዲሁም ማንቸስተር ሲቲ ከቦርንማውዝ ሌሎች የመጀመሪያ ሳምንት ተጠባቂ ፍልሚያዎች ናቸው።

በዮናስ ጌትነት
Смотреть все посты