Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.1K
13.6K
207
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 579
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 435
ER
Общий
6.66%
Суточный
4.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 053 постов
Смотреть все посты
Пост от 21.08.2026 07:29
1
0
0
ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የውድድር ዘመን ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ሻምፒዮኑ አርሰናል ከኮቨንትሪ ሲቲ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል።

ባለፈው የውድድር ዓመት የሊጉን ዘውድ የተቀዳጀው የሰሜን ለንደኑ ክለብ በተከታታይ ዓመት ሻምፒዮን ለመሆን በፍራንክ ላምፓርድ የሚመራውን ኮቨንትሪ ሲቲ በመግጠም ጉዞውን ይጀምራል።

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸውን ለማጠናከር በክረምቱ የዝውውር መስኮት እንደ ብሩኖ ጉማሬሽ፣ ክሪስቶስ ሶሊስ እና ኤዝሪ ኮንሳ ያሉ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸው ቀላቅለዋል።

በሌላ በኩል ማንቸስተር ሲቲዎች ከአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ጋር ከተለያዩ በኋላ በቀድሞ ምክትላቸው ኤንዞ ማሬስካ እየተመሩ አዲስ ምዕራፍ ይጀምራሉ።

የግብ ማሽኑን ኧርሊንግ ሃላንድን የያዘው ሲቲ፡ ኤሊዮት አንደርሰንን ጨምሮ አዳዲስ ተጫዋቾችን በማስፈረም ጠንካራ ተፎካካሪነቱን ለማስቀጠል ተዘጋጅቷል።

ሞሐመድ ሳላህን ጨምሮ ከወሳኝ ተጫዋቾቹ ጋር የተለያየው ሊቨርፑል በአንዶኒ ኢራኦላ እየተመራ የውድድር ዓመቱን ይጀምራል።

በማይክል ካሪክ የሚመራው ማንቸስተር ዩናይትድ በበኩሉ ባለፈው የውድድር ዘመን ያሳየውን መሻሻል ለማስቀጠል በሊጉ ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች በመጨመር ወደ ፉክክሩ ይመለሳል።

ባለፈው የውድድር ዓመት ደካማ ጊዜ ያሳለፈው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ በአዲሱ አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ እየተመራ በደረጃ ሰንጠረዡ ወደ ፊት በመምጣት ጠንካራ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ሀል ሲቲ ከማንቸስተር ዩናይትድ፣ ኒውካስል ዩናይትድ ከሊቨርፑል እና ፉልሃም ከቼልሲ እንዲሁም ማንቸስተር ሲቲ ከቦርንማውዝ ሌሎች የመጀመሪያ ሳምንት ተጠባቂ ፍልሚያዎች ናቸው።

በዮናስ ጌትነት
Пост от 20.08.2026 21:35
1
0
0
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዳዲስ የጨዋታ እና የዳኝነት ህጎች

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የውድድር ዓመት ነገ ምሽት ሻምፒዮኑ አርሰናል አዲስ አዳጊውን ኮቨንተሪ ሲቲን በሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጀምራል፡፡ በሊጉ በአዲሱ የውድድር ዓመት የሚተገበሩ የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ቦርድ አዳዲስ የጨዋታ እና የዳኝነት ህጎች ይፋ ተደርገዋል፡፡ በዚህም መሰረት በጨዋታ መሃል ጉዳት አስተናግዶ ከሜዳ የሚወጣ ተጫዋች ቢያንስ ለአንድ ደቂቃ ያህል ከሜዳ ውጪ ሆኖ ይቆያል፤ ከዚህ…

https://www.fanamc.com/archives/321002
Пост от 20.08.2026 16:53
104
0
1
ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተመልሷል

የሊጉን ሁሉንም የጨዋታ መርሐ ግብር ውጤቶችና የቅድመ ጨዋታ ትንታኔዎችን በሁሉም የፋና ዲጂታል አማራጮች ይከታተሉ!

የፋና ስፖርት የፌስቡክ እና ቴሌግራም ገጾችን ይወዳጁ

ፌስቡክ 👉 https://web.facebook.com/fanasport
ቴሌግራም 👉 telemetr.me/FMCSport
Пост от 19.08.2026 21:53
56
0
2
አቶ ኢሳያስ ጅራ ብቸኛ እጩ ሆነው ቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አቶ ኢሳያስ ጅራ ለኢትዮዽያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ብቸኛ እጩ ሆነው ቀረቡ።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም እንደሚካሄድ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት ምርጫ አስፈጻሚ ኮሚቴው እጩዎችን እስከ ነሀሴ 4 ቀን 2018ዓ.ም ድረስ መመዝገቡን ገልጿል።

ኮሚቴው ነሐሴ 5 ፣ 11 እና 13 ባደረጋቸው ስብሰባዎች የቀረቡ እጩዎችን ሰነድ የምርመራ እና የማጣራት ተግባር ማከናወኑን አመልክቷል።

በዚህም መሰረት ለእጩ ፕሬዚዳንታዊ ተወዳዳሪነት የቀረቡት ብቸኛ ተወዳዳሪ አቶ ኢሳያስ ጅራ ቦሾ መሆናቸውን ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
Пост от 19.08.2026 17:41
890
0
2
አርሰናል ኤዝሪ ኮንሳን ከአስቶንቪላ ለማስፈረም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል እንግሊዛዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ኤዝሪ ኮንሳን ከአስቶንቪላ ለማስፈረም ተስማምቷል፡፡

መድፈኞቹ የዊሊያም ሳሊባ እና ጁሪያን ቲምበርን ጉዳት ተከትሎ ኤዝሪ ኮንሳን ወደ ስብባቸው ለመቀላቀል መስማማታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ተጫዋቹ በነገው ዕለት የህክምና ምርመራውን ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ኤዝሪ ኮንሳ በ2019/20 የውድድር ዓመት አስቶንቪላን የተቀላቀለ ሲሆን እስካሁን ድረስ ለቪላ 286 ጨዋታዎችን አድርጓል፡፡

ኮንሳ አሰቶንቪላ ቪላ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት የዩሮፓ ሊግ ዋንጫ እንዲያሳካ እና የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታን እንዲያገኝ ትልቁን ሚና ተጫውቷል፡፡

አስቶንቪላ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ኮንሳን ጨምሮ ዩሪ ቴሌማንስ፣ ሞርጋን ሮጀርስ እና ሉካስ ዲኜን ለተለያዩ ክለቦች አሳልፎ ሰጥቷል፡፡

የአርጀንቲናዊው ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ የቪላ ቆይታ አጠራጣሪ መሆኑን ተከትሎ ጃፓናዊውን ግብ ጠባቂ ዛዮን ሱዙኪን በዛሬው ዕለት አስፈርሟል፡፡

በአብረሃም አበራ
Пост от 19.08.2026 14:12
802
0
3
አርሰናል ኤዝሪ ኮንሳን ለማስፈረም ተቃረበ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል እንግሊዛዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ኤዝሪ ኮንሳን ከአስቶንቪላ ለማስፈረም ተቃርቧል፡፡

አርሰናል የ28 ዓመቱን ተጫዋች የግሉ ለማድረግ መቃረቡን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ተጫዋቹ በክረምቱ የዝውውር መስኮት በአርሰናል ሲፈለግ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡

ኤዝሪ ኮንሳ በ2019/20 የውድድር ዓመት አስቶንቪላን የተቀላቀለ ሲሆን እስካሁን ድረስ ለቪላ 286 ጨዋታዎችን አድርጓል፡፡
👍 1
Пост от 19.08.2026 12:25
263
0
2
ማንቼስተር ዩናይትድ ካርሎስ ባሌባን ለማስፈረም ተቃረበ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ካሜሩናዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ካርሎስ ባሌባን ከብራይተን ለማስፈረም ተቃርቧል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ ለተጫዋቹ ዝውውር 60 ሚሊየን ፓውንድ ማቅረቡን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

የ22 ዓመቱ ተጫዋች በማንቼስተር ዩናይትድ ለበርካታ ጊዜ ሲፈለግ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡

ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በብራይተን ቆይታው 112 ጨዋታዎችን አድርጓል፡፡

የመሐል ሜዳ ክፍሉን እያጠናከረ የሚገኘው ማንቼስተር ዩናይትድ ዩሪ ቴሌማንስ እና አንድሬ ሳንቶስ አስቀድሞ ማስፈረሙ ይታወሳል፡፡
Смотреть все посты