Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Тарифы
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.1K
13.6K
209
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 664
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 491
ER
Общий
6.79%
Суточный
4.61%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 109 постов
Смотреть все посты
Пост от 02.09.2026 00:40
1
0
0
ቶተንሃም ሆትስፐር ሙድሪክን ከቼልሲ አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቶተንሃም ሆትስፐር ዩክሬናዊውን ተጫዋች ሙድሪክን ከቼልሲ አስፈርሟል።

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር ተጫዋቹን ወደ ስብስቡ የቀላቀለው በውሰት ውል ነው።

የ25 ዓመቱ ተጫዋች በውሰት ውሉ መሰረት ለአንድ የውድድር ዓመት ያህል በሰሜን ለንደኑ ክለብ የሚቆይ ይሆናል።

ሙድሪክ በፈረንጆቹ 2023 ቼልሲን በ70 ሚሊየን ዩሮ መቀላቀሉ ይታወሳል።

ቶተንሃም ሆትሰፐር በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ሳንድሮ ቶናሊ፣ ማቲያስ ፈርናንዴዝ፣ ሳቪኒሆ፣ ሮበርትሰን እና ኦማር ማርሙሽን የመሳሰሉ ተጫዋቾችን ማስፈረሙ ይታወሳል።

በአሰልጣኝ ሮቤርቶ ዲዘርቢ የሚመራው ቶተንሃም ሆትስፐር በሊጉ ያደረጋቸውን ተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች መሸነፉ አይዘነጋም።
Пост от 01.09.2026 23:45
1
0
0
ማንቼስተር ሲቲ ንዳዬን ከኤቨርተን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲ ሴኔጋላዊውን ተጫዋች ኢሊማን ንዳዬ ከኤቨርተን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

ንዳዬ በማንቼስተር ሲቲ ቤት ለአምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል።

ማንቼስተር ሲቲ ለ26 ዓመቱ ተጫዋች ዝውውር 65 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ አድርጓል።

ንዳዬ ለኤቨርተን ባደረጋቸው 67 ጨዋታዎች 15 ግቦችን አስቆጥሮ 4 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።
Пост от 01.09.2026 19:21
335
0
1
ማንቼስተር ሲቲ ኤንዞ ፈርናንዴዝን ከቼልሲ ለማሰፈረም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲ አርጀንቲናዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ኤንዞ ፈርናንዴዝ ከቼልሲ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሷል።

ማንቼስተር ሲቲ ለ25 ዓመቱ ተጫዋች ዝውውር 125 ሚሊየን ፓውንድ እንደሚከፍል ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።

ኤንዞ በፈረንጆቹ 2023 በ105 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ሒሳብ ከፖርቹጋሉ ክለብ ቤኔፊካ የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

በአቤል ነዋይ
Пост от 01.09.2026 16:24
1
0
0
ባርሴሎና ጋብሬል ጄሱስን ከአርሰናል አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ባርሴሎና ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ጋብሬል ጄሱስን ከአርሰናል ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ባርሴሎና ለተጨዋቹ ዝውውር 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ አድርጓል፡፡

ጋብሬል ጄሱስ በስፔኑ ክለብ እስከ ፈረንጆቹ 2029 ድረስ የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

የ29 ዓመቱ ተጫዋች ለአርሰናል 123 ጨዋታዎችን አድርጎ 32 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

ጋብሬል ጄሱስ አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ሲያሳካ የስብስቡ አካል ነበር፡፡

ተጫዋቹ ከአርሰናል በተጨማሪ ለማንቼስተር ሲቲ ተጫውቶ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

ከማንቼስተር ሲቲ ጋር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ፣ የኤፍ ኤ ካፕ፣ የካራባኦ እና የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫዎችን ማሳካቱ አይዘነጋም፡፡
Пост от 31.08.2026 18:27
1
0
0
ሊዮኔል ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ራሱን አገለለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊዮኔል ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ራሱን ማግለሉን ይፋ አድርጓል።

ሜሲ ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ጋር የዓለም ዋንጫ እና የኮፓ አሜሪካ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል።

ሜሲ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን 207 ጨዋታዎችን አድርጎ 125 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን ÷ 68 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ደግሞ አመቻችቶ አቀብሏል።
Пост от 31.08.2026 16:35
1
0
0
ሊቨርፑል ባርኮላን ከፒኤስጂ አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊቨርፑል ፈረንሳዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ብራድሊ ባርኮላን ከፒኤስጂ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ፈረንሳዊው ተጫዋች በመርሲሳይዱ ክለብ ለአምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

ሊቨርፑል ለዝውውሩ 125 ሚሊየን ዩሮ ክፍያ የፈጸመ ሲሆን፤ የተጫዋቹ ብቃት እየታየ ደግሞ ተጨማሪ 20 ሚሊየን ዩሮ ክፍያ የሚከፍል ይሆናል።

የ23 ዓመቱ ተጫዋች በፒኤስጂ በነበረው ቆይታ 153 ጨዋታዎችን አድርጎ 39 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

በሌላ በኩል ማንቼስተር ሲቲ ብራዚላዊውን የመስመር ተጫዋች አላን ኤሊያስን ከፓልሜራስ አስፈርሟል፡፡

አላን በማንቼስተር ሲቲ ቤት ለአምስት ዓመታት የሚያቆውን ውል መፈራረሙ ነው የተገለጸው፡፡

ማንቼስተር ሲቲ ለ22 ዓመቱ ተጫዋች 40 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሂሳብ ወጪ አድርጓል፡፡

አላን ለፓልሜራስ ባደረጋቸው 96 ጨዋታዎች 9 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ኤሊዮት አንደርሰን፣ እና አዩብ ቡአዲን ማስፈረሙ ይታወሳል፡፡
Пост от 31.08.2026 10:41
931
0
2
አስቶን ቪላ ከአርሰናል - የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር የአምናው ሻምፒዮን አርሰናል ከሜዳው ውጭ አስቶን ቪላን ይገጥማል፡፡

መድፈኞቹ ኮቨንትሪ ሲቲን በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን የጀመሩ ሲሆን፤ ባለሜዳው ቪላ በበኩሉ በብራይተን በሰፊ የግብ ልዩነት ሽንፈት ማስተናገዱ ይታወሳል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሁለት ጊዜ ድል የቀናቸው ሲሆን፤ በቀሪው አንድ ጨዋታ ነጥብ ተጋርተዋል፡፡

ሁለቱን ቡድኖች የሚያገናኘው የሊጉ የሁለተኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ይደረጋል፡፡
Смотреть все посты