Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.0K
13.6K
205
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 521
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 152
ER
Общий
5.89%
Суточный
4.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 045 постов
Смотреть все посты
Пост от 18.08.2026 20:06
1
0
0
ሮድሪ ባርሴሎናን ተቀላቀለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አማካይ ሮድሪጎ ሄርናንዴዝ ባርሴሎናን ተቀላቀለ፡፡

ሮድሪ በሰባት ዓመታት የማንቼስተር ሲቲ ቆይታው አንድ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግና አራት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን ጨምሮ በርካታ ዋንጫዎችን ከክለቡ ጋር ማሳካት ችሏል፡፡

የባሎንዶር አሻናፊ የሆነው ሮድሪ በካታላኑ ክለብ እሰከ ፈረንጆቹ 2030 የሚያቆየውን ውል ፈርሟል፡፡

የቀድሞ የቪያሪያል፣ አትሌቲኮ ማድሪድ እና ማንቼስተር ሲቲ ተጫዋች ለሃንሲ ፍሊኩ ባርሴሎና ሌላ የስኬት ኃይል እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

በአቤል ነዋይ
Пост от 18.08.2026 17:24
1
0
0
ፓትሪክ ቪዬራ የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው አሰልጣኝ ፓትሪክ ቪዬራ የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ፡፡

የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ ፓትሪክ ቪዬራ በሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን የሚያቆየውን የአራት ዓመት ውል ተፈራርሟል፡፡

ቪዬራ በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ብሔራዊ ቡድኑን ፍጻሜ ማድረስ እና ለ2030 የዓለም ዋንጫ ማሳለፍ ይጠበቅበታል፡፡

ፓትሪክ ቪዬራ ከዚህ ቀደም ኒውዮርክ ሲቲ፣ ኒስ፣ ክሪስታል ፓላስ፣ ስትራስቡርግ እና ዥኖአን ማሰልጠኑ ይታወሳል፡፡
Пост от 16.08.2026 22:46
85
0
1
ባርሴሎና ሮድሪን ከማንቼስተር ሲቲ ለማስፈረም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ባርሴሎና ስፔናዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ሮድሪ ከማንቼስተር ሲቲ ለማስፈረም ተስማምቷል።

ሮድሪ በባርሴሎና ለ4 ዓመታት የሚያቆየውን ውል እንደሚፈራረም ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።

የ30 ዓመቱ ተጫዋች በማንቼስተር ሲቲ ቤት ቆይታው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል።
Пост от 16.08.2026 19:40
183
0
1
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ 2ኛ ጨዋታውን የሚያደርግበት ቀን ታወቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ 2ኛ ጨዋታውን የሚያደርግበት ቀን ታወቀ፡፡

በዚህም መሰረት በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 10 ሁለተኛ የምድብ ጨዋታውን ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር በባህር ዳር ስታዲየም መስከረም 19 ቀን 2019 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ የሚያከናውን ይሆናል።

ካፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የሜዳ ጨዋታውን በባህር ዳር ስታዲየም እንዲያከናውን ጊዜያዊ ፈቃድ መስጠቱ ይታወሳል።

ዋልያዎቹ ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዎች ዝግጅታቸውን መጀመራቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 16.08.2026 19:00
115
0
1
አርሰናል የኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል ማንቼስተር ሲቲን 3 ለ 0 በማሸነፍ የኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኗል።

የአርሰናልን የማሸነፊያ ግቦች ካላፊዮሪ፣ ሀቨርትዝ እና ኦዴጋርድ አስቆጥረዋል።

አርሰናል በታሪኩ 18ኛ የኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫውን አሳክቷል።
Пост от 16.08.2026 09:45
118
0
1
አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኮሚዩኒቲ ሺልድ የፍጻሜ ጨዋታ አርሰናል እና ማንቼስተር ሲቲ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

አርሰናል የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ በማሳካት ማንቼስተር ሲቲ ደግሞ የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን በማሸነፍ በኮሚዩኒቲ ሺልድ የፍጻሜ ጨዋታ ተገናኝተዋል፡፡

አርሰናል በኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫ ታሪክ 17 ጊዜ ሻምፒዮን ሲሆን፤ ተጋጣሚው ማንቼስተር ሲቲ በበኩሉ 7 ጊዜ ዋንጫውን አሳክቷል፡፡

አርሰናል ለመጨረሻ ጊዜ የኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫን ያሳካው በ2023/24 የውድድር ዓመት ሲሆን ማንቼስተር ሲቲ ደግሞ በ2024/25 ዋንጫውን ለመጨረሻ ጊዜ ማንሳቱ ይታወሳል፡፡

በኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫ ታሪክ ማንቼስተር ዩናይትድ 21 ጊዜ ሻምፒዮን በመሆን ቀዳሚው ክለብ ነው፡፡

በአርሰናል እና ማንቼስተር ሲቲ መካከል የሚደረገው የኮሚዩኒቲ ሺልድ የፍጻሜ ጨዋታ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ይደረጋል፡፡
Пост от 15.08.2026 16:43
1
0
0
የባሕር ዳር ስታዲየም ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ማስተናገድ የሚያስችለውን የካፍ ፍቃድ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባሕር ዳር ስታዲየም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ዝቅተኛ መመዘኛ በማሟላት ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ማስተናገድ የሚያስችለውን ፍቃድ አግኝቷል፡፡ የአማራ ክልል ባሕል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ጋሻው ተቀባ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት፥ የካፍን መስፈርቶች በመከተል ስታዲየሙ ለዓለም አቀፍ ውድድሮች ብቁ እንዲሆን በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ በተለይም…

https://www.fanamc.com/archives/320764
Смотреть все посты