Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Тарифы
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.1K
13.6K
209
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 675
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 380
ER
Общий
6.49%
Суточный
4.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 098 постов
Смотреть все посты
Пост от 30.08.2026 17:00
658
0
1
ባርሴሎና ጋብሬል ጄሱስን ለማስፈረም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ባርሴሎና ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ጋብሬል ጄሱስን ከአርሰናል ለማስፈረም ተስማምቷል።

ባርሴሎና ለተጨዋቹ ዝውውር 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ያቀረበ ሲሆን፣ በአርሰናል በኩል ጥያቄው ተቀባይነት ማግኘቱን ስካይ ስፖርት ዘግቧል።

ብራዚላዊው ተጫዋች የሕክምና ምርመራውን ለማድረግ እና በይፋ ውሉን ለመፈረም በነገው ዕለት ወደ ስፔን የሚያመራ ይሆናል።
Пост от 30.08.2026 11:44
293
0
1
ቼልሲ አርጀንቲናዊውን ግብ ጠባቂ ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ አርጀንቲናዊውን ግብ ጠባቂ ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝን ከአስቶንቪላ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝ በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለቼልሲ ለሁለት ዓመት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

ቼልሲ ለ33 ዓመቱ ግብ ጠባቂ ዝውውር 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ አድርጓል፡፡

ኢሚሊያኖ ማርቲኔዝ በአስቶንቪላ በነበረው ቆይታ ለቡድኑ 256 ጨዋታዎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ቼልሲ በክረምቱ የተጫቾች የዝውውር መስኮት ዳኒ ዌልቤክ እና ጆርዳን ሄንደርሰንን የመሳሳሉ ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች ማስፈረሙ ይታወሳል፡፡

በሁለተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ዛሬ ቀን 10 ሰዓት ላይ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ብራይተንን ያስተናግዳል፡፡
Пост от 30.08.2026 10:35
1
0
0
ዩናይትድ የመጀመሪያ ድሉን ለማሳካት

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሁለተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።

በዚህም ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልድትራፎርድ ኢፕስዊች ታውንን ያስተናግዳል።

በመጀመሪያ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ በሃል ሲቲ ሽንፈት የገጠመው ማንቼስተር ዩናይትድ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል ለማሳካት ወደ ሜዳ ይገባል።

ማንቼስተር ዩናይትድ ከዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ በተመለሰው ሃል ሲቲ መሸነፉን ተከትሎ የቡድኑ ብቃት ላይ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል።

በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የሚመሩት ቀያይ ሰይጣኖቹ በቀጣይ ጨዋታዎች የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ይጠበቃል።

በ2025/26 የውድድር ዘመን በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ስር መሻሻሎችን ማሳየቱ ይታወሳል።

ማንቼስተር ዩናይትድ በ2025/26 የውድድር ዓመት በካሪክ ስር ያሳየውን መሻሻል በዚህኛው የውድድር ዓመት ይበልጥ እንዲያሳድገውም በደጋፊዎች ዘንድ ይጠበቃል።

https://www.facebook.com/share/p/1BUSa1gHy1/?mibextid=wwXIfr
Пост от 30.08.2026 08:18
387
0
1
በሲድኒ ማራቶን አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሲድኒ ማራቶን ኢትዮዽያዊው አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፏል።

ትናንት ምሽት ለ24ኛ ጊዜ በተካሄደው የማራቶን ውድድር አትሌት አዲሱ ጎበና 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ42 ሰከንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል።

አትሌቱ የገባበት ሰዓትም የቦታው ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።

በውድድሩ ጭምዴሳ ደበሌ 2ኛ፣ ጀማል መኮንን 5ኛ እንዲሁም የባለፈው ዓመት የርቀቱ አሸናፊ ኃይለማርያም ኪሮስ 6ኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን ጨርሰዋል።

በሴቶች ደግሞ ኬንያዊቷ አትሌት ፒርስ ጅፕችርችር በቀዳሚነት ውድድሩን አጠናቅቃለች።

በርቀቱ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሹሬ ደምሴ፣ ሄቨን ሀይሉ እና መሰረት አበባየሁ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ውድድራቸውን ማጠናቀቃቸውን ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
Пост от 27.08.2026 20:36
1 688
0
9
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ድልድል ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2026/27 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ድልድል የእጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት በዛሬው ዕለት በሞናኮ ተካሂዷል፡፡

ለሦስተኛ ዓመት በሊግ የውድድር ቅርጽ በሚካሄደው የ2026/27 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ጨዋታዎች አርሰናል ከሪያል ማድሪድ በኢምሬትስ ይገናኛሉ፡፡

በዚህም መሰረት የአርሰናል ተጋጣሚዎች፡- ሪያል ማድሪድ፣ ባየርን ሙኒክ፣ ቦሩሺያ ዶርትመንድ፣ ሪያል ቤቲስ፣ ሊል፣ ናፖሊ፣ ሳባህ እና ስላቪያ ፕራሃ ሆነዋል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ በበኩሉ ከባርሴሎና እና ፒኤስጂ ጋር ይገናኛል፡፡

ስፖርቲንግ ክለብ፣ ፖርቶ፣ ናፖሊ፣ አር ቢ ሌፕዚግ፣ ኤኢኬ አቴንስ እና ሎንስ ሌሎች የውሃ ሰማያዊዎቹ ተጋጣሚዎች ናቸው፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ ከባየርን ሙኒክ እና አትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ይገናኛል፡፡

የማንቼስተር ዩናይትድ ተጋጣሚዎች፡- ባየርን ሙኒክ፣ አትሌቲኮ ማድሪድ፣ ሮማ፣ ስፖርቲንግ ክለብ፣ አር ቢ ሌፕዚግ፣ ቪያሪያል፣ ኮሞ፣ ሳባህ፣

የአምናው ሻምፒየን ፒ ኤስ ጂ ተጋጣሚዎች፡- ባርሴሎና፣ ጋላታሳራይ፣ ስሎቫን ብራቲስላቫ፣ ማንቼስተር ሲቲ፣ አስቶን ቪላ፣ ቪያሪያል፣ ኮሞ ናቸው፡፡

ሪያል ማድሪድ በበኩሉ ከአርሰናል በተጨማሪ ኢንተር ሚላን፣ ፒኤስቪ፣ ሮማ፣ አር ቢ ሌፕዚግ፣ ሻካታር ዶኔስክ፣ ላስክ እና ኤኢኬ አቴንስን የሚገጥም ይሆናል፡፡

የሊቨርፑል ተጋጣሚዎች፡- አትሌቲኮ ማድሪድ፣ ኢንተር ሚላን፣ ፖርቶ፣ ሎንስ፣ ቪያሪያል፣ ክለብ ብሩጅ፣ ፈነርባቼ እና ላስክ ሆነዋል፡፡

የባርሴሎና ተጋጣሚዎች፡- ፒ ኤስ ጂ፣ ማንቼስተር ሲቲ፣ አስቶን ቪላ፣ ኮሞ፣ ፌይኖርድ፣ ስፖርቲንግ ክለብ፣ ጋላታሳራይ እንዲሁም ሳባህ ናቸው፡፡

https://web.facebook.com/share/p/1ELnLat6vP/
Пост от 27.08.2026 08:48
1 011
0
1
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የዕጣ ድልድል ዛሬ ይፋ ይሆናል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የ2026/27 የውድድር ዓመት የዕጣ ድልድል በዛሬው ዕለት ይፋ ይሆናል፡፡

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ከ2024/25 የውድድር ዓመት ወዲህ የቀደመ የጨዋታ ቅርጹን በመቀየር በሊግ ቅርጽ የተሳታፊ ቡድኖችን ቁጥር ወደ 36 በማሳደግ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

ያለፉትን ሁለት ዓመታት የፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ በተከታታይ ሻምፒዮን በመሆን በመድረኩ አስደናቂ ጊዜ አሳልፏል፡፡

በአዲሱ የውድድር ዓመት ፒኤስጂ ሻምፒዮን የሚሆን ከሆነ በተከታታይ ሦስት ጊዜ የማሸነፍ ክብረ ወሰንን ከሪያል ማድሪድ ጋር የሚጋራ ይሆናል፡፡

https://www.facebook.com/share/p/1EahfDDLmb/?mibextid=wwXIfr
Пост от 27.08.2026 00:02
132
0
2
በግማሽ ማራቶን ውድድር አዲስ የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገበው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ አቀባበል ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር በወንዶች አዲስ የዓለም ክብረወሰን ያስመዘገበው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ እና በሴቶች የውድድሩን አዲስ የቦታ ክብረወሰን በማስመዝገብ ያሸነፈችው አትሌት ፎቴን ተስፋይ አቀባበል ተደረገላቸው።

አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ 56:51 በሆነ ጊዜ በመግባት በዩጋንዳዊው አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ ተይዞ የነበረውን 57:20 የዓለም ክብረወሰን በግማሽ ማራቶን በማሻሻል አዲሱን የዓለም ምርጥ ሰዓት ማስመዝገቡ ይታወሳል።

በሴቶች ውድድር ደግሞ አትሌት ፎቴን ተስፋይ 1:03:57 በሆነ ጊዜ በመግባት የውድድሩን የቦታ ክብረወሰን በማሻሻል በአንደኝነት ማሸነፏ አይዘነጋም።

ሁለቱ አትሌቶች አዲስ አበባ ሲገቡ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህንን ጨምሮ ሌሎች የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በፌዴራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ አጃቢነት ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
Смотреть все посты