Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.0K
13.6K
205
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 540
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 574
ER
Общий
6.72%
Суточный
4.3%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 029 постов
Смотреть все посты
Пост от 13.08.2026 18:45
16
0
1
አቶ እያሱ ወሰን የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆነው ዳግም ተመረጡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 07፣ 2018 ዓ.ም (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ባካሄደው 20ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አቶ እያሱ ወሰን ለቀጣይ አራት ዓመታት ፌዴሬሽኑን እንዲመሩ በድጋሚ መርጧል።

ፌዴሬሽኑ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በሀገር ውስጥ ማካሄድና የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ የዳኞች አሰራርና የአሰልጣኝነት ፈቃድ አሰጣጥ ሥርዓት እንዲስተካከል አቅጣጫ ተቀምጧል።

የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ እያሱ ወሰን አዲሱ አመራር በኦሊምፒክና በዓለም አቀፍ መድረኮች ውጤታማ የሚሆኑ አትሌቶችን ለማፍራትና ፌዴሬሽኑን በፋይናንስ ራሱን እንዲችል በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን 20ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ከፕሬዚዳንቱ በተጨማሪ ስድስት የሥራ አስፈፃሚ አባላትን በመምረጥ ተጠናቅቋል።
Пост от 13.08.2026 00:04
1
0
0
ፒኤስጂ የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፒኤስጂ በአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ አስቶንቪላን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆኗል።

የፒኤስጂን የማሸነፊያ ግቦች ኪቪቻ ክቫረትስኬሊያ እና ዴዝሪ ዱዌ አስቆጥረዋል።

አስቶንቪላን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ብሪያን ማጆ ከመረብ አሳርፏል።

ፒኤስጂ በተከታታይ ለሁለተኛ ጊዜ የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ዋንጫን አሳክቷል።
Пост от 12.08.2026 21:14
1
0
0
የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ አሰላለፍ ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ አሰላለፍ ይፋ ሆኗል፡፡

የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ አሸናፊው ፒኤስጂ እና በዩሮፓ ሊግ አሸናፊው አስቶንቪላ መካከል ይደረጋል፡፡

ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኦስትሪያ ሬድ ቡል አሬና መደረግ ይጀምራል፡፡
Пост от 12.08.2026 19:31
1
0
0
ፒኤስጂ ከአስቶንቪላ - ተጠባቂው ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት በፒኤስጂ እና አስቶንቪላ መካከል ይደረጋል፡፡

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ አሸናፊው የፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ እና የዩሮፓ ሊግ አሸናፊው አስቶንቪላ ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡

ፒኤስጂ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ዋንጫን ለማንሳት የሚያደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡

አስቶንቪላ በፈረንጆቹ 1982 ያሳካውን የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ዋንጫ ከበርካታ ዓመታት ጥበቃ በኋላ ዋንጫውን ለማንሳት ብርቱ ፉክክር ያደርጋል፡፡

ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኦስትሪያ ሬድ ቡል አሬና የሚደረገውን ተጠባቂ ጨዋታ ሶማሊያዊው ዳኛ ኦማር አርታን በመሐል ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል፡፡
Пост от 12.08.2026 09:30
989
0
3
በዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን አቀባበል ተደረገለት

‎አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)በአሜሪካ ኦሪገን በዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን አቀባበል ተደረገለት፡፡

ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው 2 ወርቅ፣ 3 ብር እና 1 ነሐስ በድምሩ 6 ሜዳልያዎችን በማግኘት ከዓለም 5ኛ ከአፍሪካ ደግሞ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን ማጠናቀቋ ይታወሳል።

ሻምፒዮናው በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ ሄይዋርድ ፊልድ ከሐምሌ 29 ቀን እስከ ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መካሄዱ አይዘነጋም፡፡
Пост от 10.08.2026 19:19
985
0
2
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌ ለ39 ተጫዋቾች ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌ በመጪው መስከረም ወር ለሚያደርጋቸው የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የምድብ 10 የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎች ዝግጅት 39 ተጫዋቾችን ጠርተዋል።

የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌ ለዝግጅቱ ጥሪ ካደረጉላቸው ተጫዋቾች መካከል ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የሚገኙ ስድስት ተጫዋቾች ተካትተውበታል።

ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ዓርብ ነሐሴ 8 ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በመሰባሰብ ዝግጅታቸውን እንዲጀምሩ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።

ብሔራዊ ቡድኑ በመጪው መስከረም ወር በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የምድብ 10 የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎቹን ያደርጋል።
👍 5
Пост от 10.08.2026 09:43
1
0
0
የራሽፎርድ ቆይታ

ከደቂቃዎች በኋላ በኤክስትራ ታይም ስፖርት ቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን

#ስፖርት_ፖድካስት
#ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #PoodkaastiiFaanaa #fanadigitalmedia فانا_عربي_بودكاست
Смотреть все посты