Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.0K
13.6K
205
108
71.6K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 561
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 332
ER
Общий
5.55%
Суточный
4.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 978 постов
Смотреть все посты
Пост от 21.07.2026 13:09
1
0
0
የመቻል እግር ኳስ ክለብ ውበቱ አባተን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመቻል እግር ኳስ ክለብ ውበቱ አባተን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ፡፡

አሰልጣኙ ከመቻል እግር ኳስ ክለብ ጋር ለሁለት ዓመታት የሚያቆይ ውል ተፈራርመዋል፡፡

በውሉ መሠረት አሰልጣኙ ክለቡን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ተፎካካሪ ከማድረግ ባለፈ ዋንጫ የማሳካት ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ጨምሮ ሰበታ ከተማ፣ ፋሲል ከነማ፣ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሀዋሳ ከተማ፣ አዳማ ከተማ እንዲሁም ከሀገር ውጪ የሱዳኑ አል ሀሊ ሸንዲ እና የደቡብ ሱዳኑን ጃሙስ ክለብን አሰልጥኗል፡፡

በሰለሞን በቀለ
Пост от 20.07.2026 14:49
369
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ ትይናን ቶምፕሰንን ከቶተንሃም አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ወጣቱን የክንፍ ተጫዋች ትይናን ቶምፕሰን ከቶተንሃም ሆትስፐር ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ዩናይትድ የ18 ዓመቱን እንግሊዛዊ ለማዘዋወር ብቃቱ እየታየ የሚጨመር 4 ሚሊየን ፓውንድ ጨምሮ 8 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡

ተጫዋቹ ባለፈው የውድድር ዓመት በሰሜን ለንደኑ ክለብ ከ18 ዓመት በታች ቡድን ባደረጋቸው ጨዋታዎች 13 ግቦችን አስቆጥሮ ስድስት ግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል፡፡
Пост от 20.07.2026 10:18
233
0
1
ለሜሲ ያማል!

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኒውዮርክ ሰማይ ስር የእግር ኳስ ታሪክ አዲስ ንጉስ መውለዱን ለዓለም አውጇል። የሊዮኔል ሜሲን የመጨረሻ ዳንስ ለመመልከት በተሰበሰበው የዓለም ሕዝብ ፊት ሳይጠበቅ የመጣው የስፔን የአዳጊዎች ስብስብ የክብር ዘውዱን ነጥቋል። ይህ ድል የስፔን ብቻ አይደለም፤ በሜሲ እጅ ገላውን ታጥቦ ያደገው የላሚን ያማል የንግስና ዘመን ይፋዊ ማብሰሪያ ጭምር…

https://www.fanamc.com/archives/319099
Пост от 20.07.2026 01:08
388
0
2
ስፔን የ23ኛው የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሆነች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የ23ኛው የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆናለች፡፡

በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጋራ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በዛሬው ዕለት ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡

ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ስፔንና አርጀንቲና የመደበኛ ጨዋታ ክፍለ ጊዜውን ያለምንም ግብ አቻ በማጠናቀቃቸው ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ አምርተዋል፡፡

በተጨማሪ ደቂቃውም ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ማንሳት ችላለች፡፡

የስፔንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ፌራን ቶሬስ ከመረብ ያሳረፈ ሲሆን ÷ በዚህም ስፔን በታሪኳ ለ2ኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማሳካት ችላለች፡፡
Пост от 20.07.2026 00:21
1
0
0
አርጀንቲና 0- 0 ስፔን ፦ የመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ውጤት

የፍጻሜ ጨዋታው ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል።

ኢንዞ ፈርናንዴዝ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
Пост от 19.07.2026 21:22
335
0
1
የ23ኛው ዓለም ዋንጫ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ23ኛው ዓለም ዋንጫ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት በኒውዮርክ ሜትላይፍ ስታዲየም እየተካሄደ ነው። ላለፉት 39 ቀናት በአሜሪካ፣ ካናዳና ሜክሲኮ ጣምራ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 23ኛው የዓለም ዋንጫ ስፔንና አርጀንቲና ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሚያደርጉት የፍጻሜ ጨዋታ ይጠናቀቃል። ከፍጻሜ ጨዋታው በፊትም የመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱ በሜትላይፍ ስታዲየም በተለያዩ ሁነቶች በደማቅ…

https://www.fanamc.com/archives/319094
Пост от 19.07.2026 13:04
1
0
0
ስፔን ከአርጀንቲና…ዓለም በጉጉት የሚጠብቀው የፍጻሜ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ፍጻሜውን ያገኛል፡፡

በፍጻሜ ጨዋታው በወጣት ተጫዋቾች የተደራጀው የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከአርጀንቲና አቻው ጋር ኒውዮርክ በሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም ይፋለማሉ፡፡

በአሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላፎንቴ የምትመራው ስፔን እስካሁን ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በአንዱም ሳትሸነፍ በተጋጣሚዎቿ ላይ 13 ግቦችን አስቆጥራለች፤ የተቆጠረባት ደግሞ አንድ ግብ ብቻ ነው፡፡

ስፔን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በፈረንጆቹ 2010 ደቡብ አፍሪካ ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ ማሸነፏ የሚታወስ ሲሆን ÷ በድጋሚ በመድረኩ ለመንገስ ዛሬ በፍጻሜው ከአርጀንቲና ጋር የምታደርገው ፍልሚያ በጉጉት ይጠበቃል፡፡

አርጀንቲና እስካሁን ድረስ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በተጋጣሚዎቿ ላይ 19 ግቦችን ያስቆጠረች ሲሆን ÷ 7 ግቦች ደግሞ ተቆጥረውባታል፡፡

ኳታር ያዘጋጀችውን የ2022 የዓለም ዋንጫን ያነሳችው አርጀንቲና በተከታታይ ዋንጫውን ለማሸነፍ የምታደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡

ስፔን በታሪኳ ለ2ኛ ጊዜ እንዲሁም አርጀንቲና ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ለማሸነፍ የሚያደርጉት ትንቅንቅ በእግር ኳስ ቤተሰቡ ዘንድ በጉጉት ይጠበቃል፡፡

በፍጻሜ ተፋላሚዎቹ ተሸንፈው ጉዟቸው የተገታው እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ትናንት ምሽት 6 ሰዓት ላይ ባደረጉት ፍልሚያ እንግሊዝ 6 ለ 4 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡

https://www.fanamc.com/archives/319057
Смотреть все посты