Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.0K
13.6K
205
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 572
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 877
ER
Общий
6.78%
Суточный
3.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 996 постов
Смотреть все посты
Пост от 05.08.2026 11:57
193
0
1
አርሰናል ብሩኖ ጉማሬሽን ለማስፈረም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል ብራዚላዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ብሩኖ ጉማሬሽን ከኒውካስል ዩናይትድ ለማስፈረም ተስማምቷል።

አርሰናል ለተጫዋቹ ዝውውር 75 ሚሊየን ፓውንድ የሚከፍል ይሆናል።

ጉማሬሽ በሚቀጥሉት ቀናት የሕክምና ምርመራውን በማድረግ ዝውውሩን በማጠናቀቅ አርሰናልን የሚቀላቀል ይሆናል።

ከብሩኖ ጉማሬሽ የሽያጭ ትርፍ ላይ የቀድሞ ክለብ ሊዮን ከሰባት እስከ ስምንት ሚልየን ፓውንድ እንደሚያገኝ ዘአትሌቲክ ዘግቧል።

በሚኪያስ አየለ
Пост от 05.08.2026 11:07
425
0
2
21ኛው የዓለም ከ20 አመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀምራል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 21ኛው የዓለም ከ20 አመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው ዕለት በአሜሪካ ኦሪገን መካሄድ ይጀምራል፡፡

በሻምፒዮናው በ46 የውድድር ዘርፎች ከ147 ሀገራት የተወጣጡ 1 ሺህ 800 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ተመላክቷል፡፡

ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በ5 ሺህ ሜትር፣ 3ሺህ ሜትር፣ 1 ሺህ 500 ሜትር እና በ800 ሜትር በሁለቱም ፆታዎች ትሳተፋለች፡፡

በተጨማሪም በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል እና በ400 ሜትር በሴቶች እንዲሁም በርምጃ ውድድር ደግሞ በሁለቱም ፆታዎች የምትሳተፍ ይሆናል፡፡

ዛሬ በመክፈቻው ዕለት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የፍጻሜ እና የማጣሪያ ውድድራቸውን ያደርጋሉ።

ምሽት 4 ከ 43 ላይ በ800 ሜትር ወንዶች ማጣሪያ ነጋሄ እያሱ እና የሮሳን ግርማ ሲካፈሉ፤ በሴቶች ደግሞ በዚሁ ርቀት ምሽት 5 ከ 35 ሐብታም ገበየሁ እና ደራርቱ ሽብሩ ማጣሪያቸውን ያከናውናሉ።

ሌሊት 11 ከ 53 በሴቶች 5 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር እመቤት ጥላሁን እና አልማዝ ዮሃንስ የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ለማሸነፍ ብርቱ ፉክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡

ማለዳ 12 ከ 20 በወንዶች 5 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር ደግሞ ማማሩ ጎዴ እና ዳምጠው ከበደ የሚሳተፉ ይሆናል፡፡

ሻምፒዮናው በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ ሄይዋርድ ፊልድ ከሐምሌ 29 ቀን እስከ ነሀሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።

በወርቅነህ ጋሻሁን
Пост от 04.08.2026 20:58
328
0
3
ዛሬ የወጡ የአውሮፓ የተጫዋቾች ዝውውር መረጃዎች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሊጎች የ2026/27 የውድድር ዓመት ከመጀመሩ በፊት ክለቦች አዳዲስ ተጫዋቾችን ለማስፈረም የሚያደርጉት ፉክክር ቀጥሏል፡፡

👉 ብሩኖ ጉማሬሽ - የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ብሩኖ ጉማሬሽን ለማስፈረም ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ይበልጥ መቃረቡን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

መድፈኞቹ የ28 አመቱን ብራዚላዊ አማካይ ዝውውር ለማጠናቀቅ መቃረባቸውንና ተጫዋቹ የህክምና ምርመራውን ለማድረግ ከኒውካስል ፍቃድ እየጠበቀ ነው ተብሏል፡፡

👉 ቪኒ ጁኒየር - በተመሳሳይ በአርሰናል በጥብቅ የሚፈለገው ሌላኛው ብራዚላዊ ቪኒሺየስ ጁኒየር ከአሰልጣኝ ጆሴ ሞሪኒሆ ጋር መነጋገሩን ገልጿል፡፡

ተጫዋቹ በሰጠው አስተያየት፥ ሞሪኒሆ "ራሴን ሆኜ እንድጫወትና በክለቡ ደስተኛ እንድሆን ነግረውኛል" ብሏል፡፡

👉 ማንቼስተር ሲቲ ፔድሮ ኔቶን ከቼልሲ ለማስፈረም ከተጫዋቹ ወኪል ጋር መገናኘቱ ተነግሯል፡፡

ሲቲዎች ሳቪኒሆ ወደ ቶተንሃም ሆትስፐር የሚያቀና ከሆነ ፖርቹጋላዊውን ተጫዋች የማስፈረም ፍላጎት እንዳላቸው ነው የተዘገበው፡፡

👉 ቼልሲ የግራ መስመር ተከላካዩን ፔፕ ቻያ ከስፔኑ ክለብ ራዮ ቫዬካኖ ለማስፈረም ከጫፍ መድረሱ ተሰምቷል፡፡

👉 የ28 አመቱ ተጫዋች በግል ጥቅማ ጥቅሞች ዙሪያ ከምዕራብ ለንደኑ ክለብ ጋር የተስማማ ሲሆን፥ የህክምና ምርመራውን በቀጣይ ቀናት ውስጥ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡

👉 ኖቲንግሃም ፎረስት በኒውካስል ዩናይትድ የሚፈለገውን የማንቼስተር ሲቲ አማካይ ቲጃኒ ራዪንደርስ ለማስፈረም ፍላጎት አሳይቷል፡፡

በአቤል ነዋይ
Пост от 04.08.2026 09:20
322
0
1
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ኦሪገን ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ውድድሩ የሚካሄድበት ስፍራ አሜሪካ ኦሪገን ደርሷል።

በዘንድሮው የዓለም ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ5 ሺህ ሜትር፣ 3ሺህ ሜትር፣ 1 ሺህ 500 ሜትር እና በ800 ሜትር በሁለቱም ፆታዎች ትሳተፋለች፡፡

በተጨማሪም በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል እና በ400 ሜትር በሴቶች እንዲሁም በርምጃ ውድድር ደግሞ በሁለቱም ፆታዎች የምትሳተፍ ይሆናል፡፡

ሻምፒዮናው በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ ከሐምሌ 29 ቀን እስከ ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡

ውድድሩ በዓለም አትሌቲክስ ታሪክ ታዋቂ በሆነው ሄይዋርድ ፊልድ ስታዲየም የሚካሄድ ስለመሆኑ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
Пост от 31.07.2026 10:23
1
0
0
የኤሲሚላን የቀድሞ ተጫዋች ፍራንኮ ባሬዚ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጣሊያናዊው የኤሲሚላን የቀድሞ ተጫዋች ፍራንኮ ባሬዚ በ66 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

ፍራንኮ ባሬዚ የጣሊያን ብሔራዊ ቡድንን ከፈረንጆቹ 1982 እስከ 1994 ያገለገለ ሲሆን ለሀገሩ 81 ጨዋታዎችን አድርጓል፡፡

ባሬዚ በፈረንጆቹ 1982 ከጣሊያን ብሔራዊ ቡድን ጋር የዓለም ዋንጫን አሳክቷል፡፡

20 ዓመታትን በኤሲሚላን ቤት በተጫዋችነት ያሳለፈው ፍራንኮ ባሬሲ ለ15 ዓመታት ቡድኑን በአምበልነት መምራቱ ይታወሳል፡፡

በኤሲሚላን ቆይታው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ እና የጣሊያን ሴሪ አን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡

ፍራንኮ ባሬዚ ለጣሊያኑ ክለብ ኤሲሚላን በሁሉም ውድድሮች 719 ጨዋታዎችን አድርጎ 33 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
Пост от 30.07.2026 15:16
1 604
0
1
ቼልሲ ማክሰንስ ላክሩዋን ከክሪስታል ፓላስ አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ፈረንሳዊውን ተከላካይ ማክሰንስ ላክሩዋ ከክሪስታል ፓላስ አስፈርሟል፡፡

የ26 አመቱ ተጫዋች በ52 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ነው ስታምፎርድ ብሪጅ የደረሰው፡፡

በፈረንጆቹ 2024 ከጀርመኑ ክለብ ዎልፍስበርግ በ15 ነጥብ 5 ሚሊየን ፓውንድ ክሪስታል ፓላስን የተቀላቀለው ተጫዋቹ ለፓላስ 55 ጨዋታዎችን አድርጓል፡፡

ተጫዋቹ በሴልኸረስት ፓርክ ቆይታው የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ፣ የኤፍ ኤ እና የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫዎችን ማሸነፍ ችሏል፡፡

ላክሩዋ በ2026ቱ የአለም ዋንጫ ለፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በሶስት ጨዋታዎች ተሰልፎ ተጫውቷል፡፡

ማክሰንስ ላክሩዋ ከሞርጋን ሮጀርስ እና ማርኮ ፓሌስትራ ቀጥሎ ሶስተኛው የዣቢ አሎንሶ የክረምቱ ፈራሚ ሆኗል፡፡
Пост от 29.07.2026 17:00
819
0
1
ጆርዳን ሄንደርሰን ከብሬንትፎርድ ጋር ተለያየ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የመሐል ሜዳ ተጫዋች ጆርዳን ሄንደርሰን ከብሬንትፎርድ ጋር ተለያይቷል፡፡

የ36 ዓመቱ ተጫዋች በፈረንጆቹ 2025 ከአያክስ አምስተርዳም የፕሪሚየር ሊጉን ክለብ ብሬንትፎርድን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

ሄንደርሰን ከአንድ የውድድር ዓመት ቆይታ በኋላ በስምምነት ከብሬንትፎርድ ጋር መለያየቱን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ተጫዋቹ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ቼልሲን ለመቀላቀል ከስምምነት የደረሰ ሲሆን እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆየውን ውል ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
Смотреть все посты