Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.1K
13.6K
209
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 699
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 347
ER
Общий
6.39%
Суточный
4.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 084 постов
Смотреть все посты
Пост от 26.08.2026 21:16
159
0
1
ለመድፈኞቹ ተስፋን የፈነጠቀው ክሪስቶስ ዞሊስ…

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ግሪካዊው የ24 ዓመት የመስመር ተጫዋች ክሪስቶስ ዞሊስ በአርሰናል የጀመረው አዲስ የእግር ኳስ ምዕራፍ በጥሩ አጀማመር ተውቧል።

ተጫዋቹ በ2026/27 የፕሪሚየር ሊግ መክፈቻ ጨዋታ አርሰናል ኮቨንትሪ ሲቲን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ፤ ለቡካዮ ሳካ የግብ እድል በመፍጠር ትኩረት ስቧል።

ዞሊስ የእግር ኳስ ሕይወቱን በግሪኩ ፓኦክ አካዳሚ አጎልብቶ ወደ ዋናው ቡድን በመድረስ በወጣትነቱ ራሱን ማሳየት ጀመረ። በፓኦክ ቆይታው በሁሉም ውድድሮች በ57 ጨዋታዎች 17 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

የፓኦክ ብቃቱ ድንበር ተሻግሮ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አቅሙን ለማሳየት መንገድ ከፍቶለታል፡፡
https://web.facebook.com/share/p/19X1iLVTMf/
Пост от 26.08.2026 15:39
1
0
0
ማንቼስተር ሲቲ ሞሮኳዊውን አማካይ አዩብ ቡአዲን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20 ቀን 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲ ሞሮኳዊውን ወጣት ተጫዋች አዩብ ቡአዲን በ85 ነጥብ 6 ሚሊየን ፓውንድ ሒሳብ ከፈረንሳዩ ክለብ ሊል ወደ ኢቲሃድ ማምጣቱን ይፋ አድርጓል።

የ18 ዓመቱ ወጣት ተጫዋች በክለቡ ለቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል መፈረሙ ነው የተገለፀው።

ማንቼስተር ሲቲ ለዝውውሩ 81 ነጥብ 4 ሚሊየን ፓውንድ ቅድመ ክፍያ የፈጸመ ሲሆን÷ ቀሪው 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ፓውንድ ደግሞ እንደተጫዋቹ አስተዋፅኦ እየታየ የሚከፈል መሆኑ ተመላክቷል።

በፈረንሳይ ሊግ ቆይታው ምርጥ ብቃቱን ማሳየት የቻለው ቡአዲ÷ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ሀገሩ ሞሮኮ እስከሩብ ፍፃሜ ስትደርስ በስድስት ጨዋታዎች በቋሚነት በመሰለፍ ድንቅ ብቃቱን ማሳየቱ ይታወሳል።
Пост от 26.08.2026 15:36
212
0
2
ኢትዮጵያ በአኖካ ዞን 5 ጨዋታዎች አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን አስመዘገበች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኬኒያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የአኖካ ዞን 5 የወጣቶች ጨዋታ በመጀመሪያ ቀን ኢትዮጵያ አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን አስመዝግባለች፡፡

ኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያዎቹን ያገኘችው በአትሌቲክስ እና በብስክሌት ውድድሮች ነው፡፡

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአኖካ ዞን አምስት ውድድር ላይ በአትሌቲክስ ዘርፍ ሦስት የወርቅ እና አንድ የብር ሜዳሊያዎችን አሸንፈዋል።

በ3 ሺህ ሜትር ሴቶች የአትሌቲክስ ውድድር ዮርዳኖስ ፅጋብ፣ ነጻነት ሰለሞን በሴቶች 800 ሜትር ውድድር እና በሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር የርምጃ ውድድር ኔይማን ኑረዲን ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ማምጣት ችለዋል፡፡

ዋሚ ዋጂራ በወንዶች 1 ሺህ 500 ሜትር ውድድር ለኢትጵያ የብር ሜዳሊያ አስመዘግቧል።

በወንዶች የብስክሌት የግል የሰዓት ሙከራ ውድድር ለገሰ ሰሎሞን የወርቅ ሜዳሊያ ሲያስገኝ፤ በሴቶች የግል የሰዓት ሙከራ ውድድር ማህደር ደስታ የብር ሜዳሊያ አስገኝታለች፡፡

ኢትዮጵያ በመድረኩ የመጀመሪያ ቀን ተሳትፎ በሁለት የስፖርት አይነቶች 4 የወርቅ እና 2 የብር በአጠቃላይ 6 ሜዳሊያዎችን ሰብስባለች።

በሌዊ በለጠ
Пост от 25.08.2026 23:01
253
0
2
ብሩኖ ፈርናንዴዝ የእንግሊዝ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብሩኖ ፈርናንዴዝ የእንግሊዝ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር የ2025/26 የውድድር ዓመት የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል።

ብሩኖ በውድድር ዓመቱ በሊጉ 21 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበሉ ይታወሳል።

በዚህም በሊጉ በርካታ ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በአንድ የውድድር ዓመት አመቻችቶ በማቀበል ቀዳሚው ተጫዋች መሆኑ አይዘነጋም።

ብሩኖ ፈርናንዴዝ ከፈረንጆቹ 2010 በኋላ ይህንን ሽልማት ያሸነፈ የመጀመሪያው የማንቼስተር ዩናይትድ ተጫዋች ሆኗል።

በፈረንጆቹ 2010 ዋይን ሩኒ ይህንን ሽልማት ማሸነፉ ይታወሳል።

በወጣቶች ዘርፍ ደግሞ የማንቼስተር ሲቲ ተጫዋች ኒኮ ኦሬሊይ የዓመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል።

በሌላ በኩል ዴቪድ ራያ፣ ጋብሬል ማጋሌሽ፣ ዊሊያም ሳሊባ፣ ጁሪያን ቲምበር፣ ኒኮ ኦሬሊይ፣ ብሩኖ ፈርናንዴዝ፣ ዴክላን ራይስ፣ ሪያን ሼርኪ፣ ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ፣ አንቷን ሴሜኒዮ እና ኢጎር ቲያጎ የዓመቱ ምርጥ ቡድን ውስጥ መካተት ችለዋል።
Пост от 24.08.2026 19:28
1
0
0
ኢትዮጵያ የ2028ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ ለካፍ ጥያቄ አቀረበች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የ2028ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ ጥያቄዋን ያቀረበችበትን ሰነድ ለአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስገብታለች፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢፌዴሪ መንግሥት ጋር በጋራ አስፈላጊ ሰነዶችን ያካተተ ዶክመንት ለካፍ ማስገባቱን አስታውቋል፡፡

በዚህም ኢትዮጵያ ትልቁን አህጉራዊ የእግር ኳስ ድግስ ለ4ኛ ጊዜ በስኬት ለማስተናገድና በአፍሪካ እግር ኳስ ያላትን ጉልህ ታሪክ ዳግም ለማደስ ዝግጁነቷን አረጋግጣለች።
Пост от 24.08.2026 09:47
1
0
0
አስፈሪው አርሰናል

ከደቂቃዎች በኋላ በኤክስትራ ታይም ስፖርት ቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን

#ስፖርት_ፖድካስት
#ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #PoodkaastiiFaanaa #fanadigitalmedia فانا_عربي_بودكاست
Пост от 24.08.2026 09:34
1
0
0
ቼልሲ የውድድር ዓመቱን በምዕራብ ለንደን ደርቢ ይጀምራል

‎አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የመጀመሪያ ሳምንት የመጨረሻ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት ቼልሲ ከሜዳው ውጭ ፉልሃምን ይገጥማል፡፡

በክረምቱ አዳዲስ አሰልጣኞችን የሾሙት ሁለቱ ክለቦች የውድድር ዓመቱን በድል ለመጀመር የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ቼልሲ ከሪያል ማድሪድ የተሰናበተውን አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ እንዲሁም ፉልሃም በተመሳሳይ ሪያል ማድሪድን በጊዜያዊነት ሲያሰለጥን የነበረውን አልቫሮ አርቤሎዋን በዚህ ክረምት መሾማቸው ይታወሳል፡፡

ምሽት 4 ሰዓት ላይ በክራቨን ኮቴጅ የሚደረገውን የምዕራብ ለንደን ደርቢ የ36 ዓመቱ ጆን ብሩክስ በመሃል ዳኝነት ይመሩታል፡፡

ትናንት ምሽት በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ ቦርንማውዝን 2 ለ 1 ሲያሸንፍ ሊቨርፑል ከኒውካስል ዩናይትድ 2 አቻ መለያየቱ ይታወቃል፡፡

የፋና ስፖርት የፌስቡክ እና ቴሌግራም ገጾችን ይወዳጁ

ፌስቡክ https://web.facebook.com/fanasport
ቴሌግራም ?? telemetr.me/FMCSport
Смотреть все посты