Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Тарифы
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.1K
13.6K
272
165
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 645
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 310
ER
Общий
6.3%
Суточный
4.72%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 124 постов
Смотреть все посты
Пост от 05.09.2026 21:33
117
0
1
አስቶንቪላ እና ሃል ሲቲ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አስቶንቪላ እና ሃል ሲቲ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡

ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ጨዋታቸውን አጠናቅቀዋል፡፡

አስቀድሞ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ ኮቨንትሪ ሲቲን 1 ለ 0 እንዲሁም ክሪስታል ፓላስ ፉልሃምን 3 ለ 2 አሸንፈዋል፡፡

ሊድስ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከሰንደርላንድ በተመሳሳይ 1 አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር ከኖቲንግሃም ፎረስት ያለምንም ግብ አቻ ሲለያይ ፤ ኒውካስል ዩናይትድ ከቦርንማውዝ 2 አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 05.09.2026 19:12
1
0
0
ማንቼስተር ሲቲ ኮቨንትሪ ሲቲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ ኮቨንትሪ ሲቲን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በኢትሃድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የማንቼስተር ሲቲን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ማንቼስተር ሲቲ ተከታታይ ሦስተኛ ድሉን አሳክቷል፡፡

በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ክሪስታል ፓላስ ፉልሃምን 3 ለ 2 ሲያሸንፍ፣ ሊድስ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከሰንደርላንድ በተመሳሳይ 1 አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር ከኖቲንግሃም ፎረስት ያለምንም ግብ አቻ ሲለያይ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ኒውካስል ዩናይትድ ከቦርንማውዝ 2 አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ሃል ሲቲ ከ አስቶንቪላ የሚገናኙ ይሆናል፡፡
Пост от 05.09.2026 16:40
1
0
0
ኒውካስል ዩናይትድ እና ቦርንማውዝ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኒውካስል ዩናይትድ እና ቦርንማውዝ 2 አቻ ተለያይተዋል፡፡

ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ በተደረገው ጨዋታ የኒውካስል ዩናይትድን ግቦች ባርንስ እና ራምሴ አስቆጥረዋል፡፡

የቦርንማውዝን ግቦች ደግሞ ታቨርነር እና ቲያው በራሱ ግብ ላይ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

የሊጉ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ሲቲ ከኮቨንትሪ ሲቲ፣ ብሬንትፎርድ ከሰንደርላንድ፣ ብራይተን ከ ሊድስ ዩናትድ እንዲሁም ፉልሃም ከክሪስታል ፓላስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ሃል ሲቲ ከ አስቶንቪላ የሚገናኙ ይሆናል፡፡
Пост от 05.09.2026 02:00
1 136
0
1
ሊቨርፑል የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል አሳካ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 3ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሊቨርፑል ኢፕስዊች ታውንን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ሁለት ግቦች አሌክሳንደር አይሳክ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሯል።

በጨዋታው ኮዲ ጋክፖ ሁለቱንም ለግብ የሚሆኑ ኳሶች አመቻችቶ ያቀበለው ተጫዋች ነው።

ከሁለት ተከታታይ የአቻ ውጤት በኋላ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድሉን ያሳካው ሊቨርፑል ነጥቡን ወደ አምስት ከፍ አድርጓል።

ተጋጣሚው ኢፕስዊች ታውን በበኩሉ ተከታታይ ሁለተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል።
👍 3
Пост от 04.09.2026 10:29
42
0
1
ሊቨርፑል ከኢፕስዊች ታውን

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሦስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት በሚደረግ አንድ ጨዋታ ይጀምራል፡፡

በዚህም ሊቨርፑል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከኢፕስዊች ታውን ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

በአንዶኒ ኢራኦላ የሚመራው ሊቨርፑል የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ሊቨርፑል በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሁለት አቻ በሆነ ተመሳሳይ ውጤት ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡

ተጋጣሚው ኢፕስዊች ታውን በበኩሉ ወደ ድል ለመመለስ የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡

በመጀመሪያ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ ድል የቀናው ኢፕስዊች ታውን በሁለተኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በማንቼስተር ዩናይትድ 5 ለ 2 በሆነ ሰፊ ውጤት መሸነፉ አይዘነጋም፡፡
Пост от 03.09.2026 21:08
1
0
0
ሪቻርልሰን ከቶተንሃም ስብስብ ውጪ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብራዚላዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሪቻርልሰን ከቶተንሃም ሆትስፐር ስብስብ ውጪ ሆኗል።

አሰልጣኝ ሮቤርቶ ዲ ዘርቢ በቅርቡ ሪቻርልሰን ክለቡን ለመልቀቅ ጥያቄ ማቅረቡን መግለጻቸው የሚታወስ ነው።

የ29 ዓመቱ ተጫዋች በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ስሙ ከኤቨርተንን ጋር ሲያያዝ ቆይቷል።

ሪቻርልሰን ለቶተንሃም ሆትስፐር 103 ጨዋታዎችን አድርጎ 27 ግቦችን አስቆጥሯል።

የተጫዋቹ ቀጣይ ማረፊያ የት ይሆናል የሚለው ይጠበቃል።
Пост от 03.09.2026 21:07
1
0
0
ጋብሬል ማርቲኔሊ አል ሂላልን ተቀላቀለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሳዑዲ አረቢያው ክለብ አል ሂላል ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ጋብሬል ማርቲኔሊን ከአርሰናል ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

አል ሂላል ለጋብሬል ማርቲኔሊ ዝውውር 60 ሚሊየን ፓውንድ ለአርሰናል መክፈሉን ቢቢሲ ዘግቧል።

ጋብሬል ማርቲኔሊ በ2025/26 የውድድር ዓመት ከአርሰናል ጋር የሊጉን ዋንጫ ማንሳቱ ይታወሳል።

የማርቲኔሊ የዝውውር ሂሳብ የአርሰናል የተጫዋች ሽያጭ ክብረ ወሰን በመሆን ተመዝግቧል።

አሌክስ ኦክስሌድ ቻምበርሊን በፈረንጆቹ 2017 ሊቨርፑልን በ35 ሚሊየን ፓውንድ በመቀላቀል የክለቡ የተጫዋች ሽያጭ ክብረ ወሰን ይዞ መቆየቱ ይታወሳል።
Смотреть все посты