Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
19.9K
13.6K
186
100
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 472
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
1 919
ER
Общий
5.05%
Суточный
3.7%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 864 постов
Смотреть все посты
Пост от 05.07.2026 09:57
57
0
1
በዩጂን ዳይመንድ ሊግና በፒችትሪ የጎዳና ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የፕሪፎንቴይን ክላሲክ - ዩጂን ዳይመንድ ሊግ እና በአሜሪካ የፒችትሪ የጎዳና ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል።

በአሜሪካዋ ዩጂን በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ የሁለት ማይል ርቀት ውድድር አትሌት አለሺኝ ባወቀ በቀዳሚነት አጠናቅቃለች፡፡

አትሌቷ ውድድሩን በበላይነት ያጠናቀቀችው የወቅቱ ፈጣን የሆነ ሰዓት 9 ደቂቃ ከ20 ሴኮንድ ከ02 ማይክሮ ሴኮንድ በማስመዝገብ ነው፡፡

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሒሩት መሸሻ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ውድድሯን ጨርሳለች፡፡

በዚሁ ርቀት የተሳተፉት አትሌት ማርታ አለማየሁ 4ኛ፣ አትሌት የኔዋ ንብረት 7ኛ እንዲሁም አትሌት አሳየች አይቼው 8ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቅቀዋል።

በሌላ በኩል የአሜሪካ የነጻነት ቀን ክብረ በዓል አካል ሆኖ በተካሄደው በ57ኛው የፒችትሪ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ በ31:02 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሯን በበላይነት አጠናቅቃለች።

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት መልክናት ውዱ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን ጨርሳለች፡፡
Пост от 05.07.2026 09:32
1
0
0
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ የመዝጊያ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ጨዋታ በዛሬው ዕለት ይደረጋል፡፡

በዚህም የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በሚያደርጉት ጨዋታ የውድድር ዓመቱ ፍጻሜውን ያገኛል፡፡

የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ቀን 10 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋል።

ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ወደ 71 ከፍ ማድረግ ይችላል፡፡

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ድል የሚያደርግ ከሆነ ደግሞ ነጥቡን 54 በማድረስ 5ኛ ደረጃን ይዞ ውድድር ዓመቱን የሚያጠናቅቅ ይሆናል፡፡

ምድረ ገነት ሽረ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና አርባ ምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊጉ የወረዱ ቡድኖች ናቸው፡፡
Пост от 05.07.2026 09:12
1
0
0
ብራዚል ከኖርዌይ፤ እንግሊዝ ከሜክሲኮ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜውን ለመቀላቀል የሚደረጉ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡

የአምስት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊ ብራዚል ምሽት 5 ሰዓት ላይ ከኖርዌይ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ብራዚል ጃፓንን እንዲሁም ተጋጣሚዋ ኖርዌይ ደግሞ ኮትዲቫርን በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡

በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ውድድር 4 ግቦችን ያስቆጠረው ቪኒሸስ ጁኒየር በብራዚል ብሔራዊ ቡድን በኩል ተጠባቂው ተጫዋች ነው፡፡

በሌላ በኩል አምስት ግቦችን ማስቆጠር የቻለው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ ሌላኛው በዛሬው ጨዋታ የሚጠበቅ ተጫዋች ነው፡፡

በሌላ መርሐ ግብር አዘጋጇ ሀገር ሜክሲኮ ሌሊት 9 ሰዓት ላይ ከእንግሊዝ ጋር ትገናኛለች፡፡

አንድም ግብ ሳይቆጠርባት ሁሉንም ጨዋታዎች በማሸነፍ እዚህ የደረሰችው ሜክሲኮ በዛሬው ጨዋታ ለእንግሊዝ ትልቅ ፈተና ትሆናለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን እንዲሁም ሜክሲኮ ኢኳዶርን በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡

እንግሊዝ ከፈረንጆቹ 1966 በኋላ የዓለም ዋንጫን ለማሳካት የምታደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ወደ ሜዳ የምትገባ ይሆናል፡፡

አምስት ግቦችን በማስቆጠር ለወርቅ ጫማው እየተፋለመ የሚገኘው እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሃሪ ኬን በጨዋታው ይጠበቃል፡፡
Пост от 04.07.2026 22:06
46
0
1
ሞሮኮ ካናዳን በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሞሮኮ አዘጋጇን ካናዳ 3 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡

የሞሮኮን የማሸነፊያ ግቦች ኡናሂ (ሁለት) እና ራሂሚ ከመረብ አሳርፈዋል።
Пост от 04.07.2026 04:06
17
0
1
አርጀንቲና ኬፕ ቨርዴን በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አርጀንቲና ኬፕ ቨርዴን 3 ለ 2 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቅላለች።

ቡድኖቹ የመደበኛውን ጊዜ በአቻ ውጤት አጠናቅቀው ወደ ተጨማሪ ጊዜ አምርተው ነበር።

በጨዋታው የአርጀንቲናን ግቦች ሜሲ፣ ማርቲኔዝ እና ቦርጀስ (በራስ ላይ) አስቆጥረዋል።

የኬፕ ቨርዴን ግቦች ዱአርቴ እና ካርባል ከመረብ አሳርፈዋል።

ሊዮኔል ሜሲ በዚህ የዓለም ዋንጫ ውድድር ያስቆጠረውን ግብ ሰባት አድርሷል።
Пост от 04.07.2026 00:10
2
0
1
ግብጽ አውስትራሊያን በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ግብጽ አውስትራሊያን በመለያ ምት በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቅላለች።

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች በመደበኛና ተጨማሪ ጊዜ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት በማጠናቀቃቸው ወደ መለያ ምት አምርተዋል።

አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠ የመለያ ምትም ግብጽ 4 ለ 2 በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀል ችላለች።

ግብጽ ሞሮኮን በመከተል 16ቱን የተቀላቀለች 2ኛዋ የአፍሪካ ሀገር ሆናለች።
Пост от 03.07.2026 14:11
915
0
2
አርጀንቲና ከኬፕ ቨርዴ…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የ32ቱ ጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ ሦስት ጨዋታዎች ይጠናቀቃል፡፡

ምድቧን በበላይነት እየመራች 32ቱን የተቀላቀለቸው አርጀንቲና ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ከኬፕ ቨርዴ ጋር ትጫወታለች፡፡

ለዋንጫው በቀዳሚነት ከሚጠበቁ ብሔራዊ ቡድኖች መካከል አንዷ የሆነችው የሊዮኔል ሜሲ ሀገር አርጀንቲና የዛሬውን ጨዋታ የማሸነፍ ቅድመ ግምት አግኝታለች፡፡

የመጀመሪያ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን እያደረገች የምትገኘው አፍሪካዊቷ ሀገር ኬፕ ቨርዴ በምድብ ጨዋታዎች ሳትሸነፍ 2ኛ ደረጃን ይዛ 32ቱን ጥሎ ማለፍ መቀላቀሏ ይታወሳል፡፡

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሸናፊ ወደ ሩብ ፍጻሜ ለመግባት በሚደረገው ፍልሚያ ከግብጽ እና አውስትራሊያ አሸናፊ ጋር የሚጫወት ይሆናል፡፡

ከኪሊያን ምባፔ ጋር በእኩል 6 ግቦች በውድደሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን እየመራ የሚገኘው ሊዮኔል ሜሲ በዛሬው ጨዋታ ልዩነት ፈጣሪ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

https://web.facebook.com/share/p/18MziWojc2/
Смотреть все посты