Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Тарифы
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
54.1K
13.6K
380
258
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 601
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 366
ER
Общий
6.47%
Суточный
4.35%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 54 057 постов
Смотреть все посты
Пост от 15.09.2026 13:40
30
0
1
አቶ ኢሳያስ ጂራ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) አቶ ኢሳያስ ጂራ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል።

ብቸኛ ተወዳዳሪ ሆነው የቀረቡት እና ላለፉት 8 ዓመታት የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሆነው የመሩት አቶ ኢሳያስ ጂራ ከተሰጡ 88 ድምጾች 81 ድምጽ በማግኘት ለ3ኛ ጊዜ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት በመሆን መመረጥ ችለዋል፡፡

አቶ ኢሳያስ ጂራ ለቀጣዮቹ አራት ዓመታት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆነው የሚቀጥሉ ይሆናል፡፡
Пост от 15.09.2026 13:24
1
0
0
የ2028 የሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ የሚካሄድበት ስታዲየም ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2028 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር የፍጻሜ ጨዋታ የሚካሄድበት ስታዲየም ይፋ ተደርጓል፡፡

በዚህም የ2028 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር የፍጻሜ ጨዋታ በአልያንዝ አሬና ስታዲየም እንደሚደረግ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር አሳውቋል፡፡

አልያንዝ አሬና ለ3ኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታን የሚያስተናግድ ይሆናል፡፡

ከዚህ ቀደም በአልያንዝ አሬና ስታዲየም በፈረንጆቹ 2012 እና 2025 የሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ መደረጉ ይታወሳል፡፡

በተጨማሪም የ2029 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር የፍጻሜ ጨዋታ በካምፕ ኑ ስታዲየም እንደሚካሄድ ተመላክቷል፡፡

ካምፕኑ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታን ለሶስተኛ ጊዜ የሚያስተናግድ ይሆናል፡፡

ከዚህ በፊት ካምፕኑ በፈረንጆቹ 1989 እና 1999 የፍጻሜ ጨዋታን ማስተናገዱ አይዘነጋም፡፡

የ2027 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በስታዲዮ ሜትሮፖሊታኖ እንደሚካሄድ ይታወቃል፡፡
Пост от 13.09.2026 20:56
46
0
1
አትሌት ልቅና አምባው የ5 ሺህ ሜትር የአልቲሜት ሻምፒዮና አሸናፊ ሆነች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በአልቲሜት ሻምፒዮና የመጨረሻ ቀን በተካሄደው የሴቶች 5 ሺህ ሜትር የፍፃሜ ውድድር አትሌት ልቅና አምባው ውድድሩን በበላይነት በማጠናቀቅ የሻምፒዮናው አሸናፊ ሆናለች።

አትሌቷ ርቀቱን 14 ደቂቃ፣ 30 ሰከንድ፣ 36 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ጊዜ በቀዳሚነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያ ማሸነፍ ችላለች።

ሌላኛው አትሌት ፋንታዬ በላይነህ 3ኛ ደረጃን ይዛ በማጠናቀቅ የነሐስ ሜዳሊያ አሸንፋለች።

አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ 4ኛ፣ አትሌት አለሺኝ ባወቀ 5ኛ እንዲሁም አትሌት ሰናይት ጌታቸው 7ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

አውስትራሊያዊቷ አትሌት ጄሲካ ሂል በሁለተኛነት ውድድሯን አጠናቃለች።
👍 1
Пост от 13.09.2026 20:30
250
0
1
ተጠባቂው የማንቼስተር ደርቢ በሲቲ የበላይነት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በ199ኛው የማንቼስተር ደርቢ ከ66 ደቂቃ በላይ በ10 ተጫዋቾች የተጫወተው ማንቼስተር ሲቲ 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ምሽት 12 ሰዓት ላይ በኦልድትራፎርድ በተደረገው የ4ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ በሀላንድ ብቸኛ ግብ ሙሉ 3 ነጥብ ይዞ ተመልሷል፡፡

ዩናይትዶች በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ፊል ፎደን በቀይ ካርድ ከሜዳ መሰናበቱን ተከትሎ ያገኙትን የተጫዋች ብልጫ እድል ባለመጠቀማቸው በሜዳቸውና በደጋፊዎቻቸው ፊት ሽንፈት አስተናግደዋል፡፡
Пост от 12.09.2026 23:57
1 211
0
2
አርሰናል ሰንደርላንድን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በ4ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል ሰንደርላንድን 2 ለ ዐ አሸንፏል።

በስታዲየም ኦፍ ላይት በተደረገው ጨዋታ የመድፈኞቹን ግቦች ብሩኖ ጊማሬሽ እና ቡካዮ ሳካ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥረዋል።

ሰንደርላንድ ጨዋታውን መምራት የሚችልበትን ፍጹም ቅጣት ምት ኢንዞ ሊ ፊ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
👍 8
Пост от 12.09.2026 13:06
1 851
0
3
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ 7 ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በአራተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት 7 ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዚህም ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

በሊጉ እስካሁን ድረስ ሁሉንም ጨዋታዎች ያሸነፈው አርሰናል ተከታታይ 4ኛ ድሉን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡

ባለሜዳው ሰንደርላንድ በበኩሉ ወደ ድል ለመመለስ የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሁሉም ውድድር እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል አራቱን በማሸነፍ የበላይነት አለው፡፡ በቀሪው አንድ ጨዋታ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል፡፡

ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ቼልሲ በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ ሃል ሲቲን ያስተናግዳል፡፡

ከሁለት ተከታታይ ድል በኋላ በ3ኛ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ ሽንፈት የገጠመው ቼልሲ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

እስካሁን በሊጉ ያልተሸነፈው ተጋጣሚው ሃል ሲቲ በበኩሉ ያለመሸነፍ ጉዞውን ለማጠናከር ይፋለማል፡፡

በተመሳሳይ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ፉልሃምን ያስተናግዳል፡፡

በ3ኛ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ የመጀመሪያ ድሉን ያሳካው ሊቨርፑል ተከታታይ ድሉን ለማሳካት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡

ተጋጣሚው ፉልሃም በበኩሉ የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል ለማሳካት ወደ ሜዳ ይገባል፡፡

ቦርንማውዝ ከብሬንትፎርድ፣ አስቶንቪላ ከኖቲንግሃም ፎረስት እንዲሁም ክሪስታል ፓላስ ከኢፕስዊች ታውን በተመሳሳይ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡

ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ቶተንሃም ሆትስፐር ከኤቨርተን ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
👍 1
Пост от 10.09.2026 10:25
476
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድ ከሳባህ ኤፍኬ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የመጀመሪያ ዙር መርሐ ግብር ዛሬ ስድስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

የሦስት ጊዜ የመድረኩ ባለክብር ማንቼስተር ዩናይትድ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከአዘርባጃኑ ሳባህ ኤፍኬ ጋር ያደርጋል፡፡

ከሁለት የውድድር ዓመት በኋላ ወደ መድረኩ የተመለሱት ዩናይትዶች ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኦልድትራፎርድ በሚያደርጉት ጨዋታ የውድድር ዓመቱን ይጀምራሉ፡፡

ባየርን ሙኒክ ከቦዶ ግሊምት፣ ኮሞ ከአርቢ ሌፕዚግ፣ ስላቪያ ፕራሃ ከሎንስ በተመሳሳይ 4 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡

ከእነዚህ ጨዋታዎች አስቀድሞ ምሽት 1 ሰዓት ከ45 ላይ ፌነርባቼ ከሮማ እንዲሁም ፒኤስቪ ከሻካታር ዶኔስክ ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Смотреть все посты