Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Тарифы
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.1K
13.6K
272
165
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 634
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 331
ER
Общий
6.36%
Суточный
4.76%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 135 постов
Смотреть все посты
Пост от 06.09.2026 18:11
213
0
1
ማንቼስተር ዩናይትድና ኤቨርተን አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሦስተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ እና ኤቨርተን 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

የማንቼስተር ዩናይትድን ግቦች ብሪያን ምቤሞ እና ቤንጃሚን ሼሽኮ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

የኤቨርተንን የአቻነት ግቦች ደግሞ ታይሪክ ጆርጅ እና ሚትላንድ ኔልስ አስቆጥረዋል፡፡
Пост от 06.09.2026 08:04
668
0
1
አርሰናል ከቼልሲ - የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 01፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጠናቀቃል።

በዚህም ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ አርሰናል በሜዳው ኢምሬትስ ቼልሲን ያስተናግዳል፡፡

የሊጉን የዋንጫ ቅድመ ግምት አግኝቶ የውድድር ዓመቱን የጀመረው አርሰናል በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፉ ይታወሳል።

በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመሩት መድፈኞቹ በሊጉ ሦስተኛ ተከታታይ ድላቸውን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገቡ ይሆናል።

በአሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ እየተመራ የውድድር ዓመቱን የጀመረው ቼልሲ በሊጉ ተከታታይ 3ኛ ድሉን ለማሳካት እያለመ ወደ ኢምሬትስ ያቀናል፡፡

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ እንደ ተጋጣሚው አርሰናል ሁሉ በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል ማድረጉ አይዘነጋም፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሁሉም ውድድር እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል አራቱን በማሸነፍ የበላይነት አለው።

በቀሪው አንድ ጨዋታ ደግሞ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው።

ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ኤቨርተንን ይገጥማል።

https://www.facebook.com/share/p/199HoiXvV6/?mibextid=wwXIfr
Пост от 06.09.2026 08:03
1
0
0
አርሰናል ከቼልሲ - የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ

አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 01፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጠናቀቃል።

በዚህም ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ አርሰናል በሜዳው ኢምሬትስ ቼልሲን ያስተናግዳል፡፡

የሊጉን የዋንጫ ቅድመ ግምት አግኝቶ የውድድር ዓመቱን የጀመረው አርሰናል በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፉ ይታወሳል።

በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመሩት መድፈኞቹ በሊጉ ሦስተኛ ተከታታይ ድላቸውን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገቡ ይሆናል።

በአሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ እየተመራ የውድድር ዓመቱን የጀመረው ቼልሲ በሊጉ ተከታታይ 3ኛ ድሉን ለማሳካት እያለመ ወደ ኢምሬትስ ያቀናል፡፡

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ እንደ ተጋጣሚው አርሰናል ሁሉ በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል ማድረጉ አይዘነጋም፡፡

ሁለቱ ቡድኖች በሁሉም ውድድር እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል አራቱን በማሸነፍ የበላይነት አለው።

በቀሪው አንድ ጨዋታ ደግሞ አቻ መለያየታቸው የሚታወስ ነው።

ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ኤቨርተንን ይገጥማል።

https://www.facebook.com/share/p/199HoiXvV6/?mibextid=wwXIfr
Пост от 06.09.2026 02:45
245
0
1
በዳይመንድ ሊግ 3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ገመቹ ጎዳና አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በብራስልስ ዳይመንድ ሊግ 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ገመቹ ጎዳና አሸንፏል።

አትሌት ገመቹ 8 ደቂቃ ከ08 ሰከንድ ከ67 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል።

አትሌቱ ከ12 ቀናት በፊት በፖላንድ ሲሌሲያ በተካሄደው የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር አንደኛ ስለመውጣቱም ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
Пост от 06.09.2026 02:28
13
0
1
በዳይመንድ ሊግ 3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ገመቹ ጎዳና አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በብራስልስ ዳይመንድ ሊግ 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ገመቹ ጎዳና አሸንፏል።

አትሌት ገመቹ 8 ደቂቃ ከ08 ሰከንድ ከ67 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል።

አትሌቱ ከ12 ቀናት በፊት በፖላንድ ሲሌሲያ በተካሄደው የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር አንደኛ ስለመውጣቱም ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
Пост от 05.09.2026 21:33
117
0
1
አስቶንቪላ እና ሃል ሲቲ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አስቶንቪላ እና ሃል ሲቲ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡

ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ጨዋታቸውን አጠናቅቀዋል፡፡

አስቀድሞ በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ሲቲ ኮቨንትሪ ሲቲን 1 ለ 0 እንዲሁም ክሪስታል ፓላስ ፉልሃምን 3 ለ 2 አሸንፈዋል፡፡

ሊድስ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከሰንደርላንድ በተመሳሳይ 1 አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር ከኖቲንግሃም ፎረስት ያለምንም ግብ አቻ ሲለያይ ፤ ኒውካስል ዩናይትድ ከቦርንማውዝ 2 አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
Пост от 05.09.2026 19:12
1
0
0
ማንቼስተር ሲቲ ኮቨንትሪ ሲቲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ ኮቨንትሪ ሲቲን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በኢትሃድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የማንቼስተር ሲቲን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ማንቼስተር ሲቲ ተከታታይ ሦስተኛ ድሉን አሳክቷል፡፡

በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ክሪስታል ፓላስ ፉልሃምን 3 ለ 2 ሲያሸንፍ፣ ሊድስ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከሰንደርላንድ በተመሳሳይ 1 አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር ከኖቲንግሃም ፎረስት ያለምንም ግብ አቻ ሲለያይ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ኒውካስል ዩናይትድ ከቦርንማውዝ 2 አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡

የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ሃል ሲቲ ከ አስቶንቪላ የሚገናኙ ይሆናል፡፡
Смотреть все посты