Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.0K
13.6K
205
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 515
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 152
ER
Общий
5.89%
Суточный
4.4%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 20 048 постов
Смотреть все посты
Пост от 19.08.2026 14:12
372
0
3
አርሰናል ኤዝሪ ኮንሳን ለማስፈረም ተቃረበ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል እንግሊዛዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ኤዝሪ ኮንሳን ከአስቶንቪላ ለማስፈረም ተቃርቧል፡፡

አርሰናል የ28 ዓመቱን ተጫዋች የግሉ ለማድረግ መቃረቡን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ተጫዋቹ በክረምቱ የዝውውር መስኮት በአርሰናል ሲፈለግ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡

ኤዝሪ ኮንሳ በ2019/20 የውድድር ዓመት አስቶንቪላን የተቀላቀለ ሲሆን አስካሁን ድረስ ለቪላ 286 ጨዋታዎችን አድርጓል፡፡
Пост от 19.08.2026 12:25
263
0
2
ማንቼስተር ዩናይትድ ካርሎስ ባሌባን ለማስፈረም ተቃረበ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ካሜሩናዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ካርሎስ ባሌባን ከብራይተን ለማስፈረም ተቃርቧል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ ለተጫዋቹ ዝውውር 60 ሚሊየን ፓውንድ ማቅረቡን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

የ22 ዓመቱ ተጫዋች በማንቼስተር ዩናይትድ ለበርካታ ጊዜ ሲፈለግ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡

ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በብራይተን ቆይታው 112 ጨዋታዎችን አድርጓል፡፡

የመሐል ሜዳ ክፍሉን እያጠናከረ የሚገኘው ማንቼስተር ዩናይትድ ዩሪ ቴሌማንስ እና አንድሬ ሳንቶስ አስቀድሞ ማስፈረሙ ይታወሳል፡፡
Пост от 19.08.2026 11:59
1
0
0
ፖል ፖግባ ከሞናኮ ጋር ተለያየ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሞናኮ ከፈረንሳዊው ተጫዋች ፖል ፖግባ ጋር መለያየቱን ይፋ አድርጓል፡፡

ፖግባ ከአበረታች ንጥረ ነገር ጋር በተያያዘ ለ19 ወራት ከእግር ኳስ ታግዶ ከቆየ በኋላ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በሞናኮ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

ፈረንሳዊው አማካይ ፖል ፖግባ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለሞናኮ 6 ጨዋታዎችን ብቻ ነው ያደረገው፡፡

የ33 ዓመቱ ተጫዋች በጉዳት ምክንያት ለሞናኮ የሚጠበቀውን ያህል ግልጋሎት መስጠት አልቻለም፡፡

ፖግባ ከቀናት በፊት ልምምድ ላይ አዲስ ጉዳት ማስተናገዱን ተከትሎ ክለቡ ውሉን ለማቋረጥ ጠይቆ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ሞናኮ ፖግባ በቀጣይ የእግር ኳስ ሕይወቱ መልካም ነገር እንዲገጥመው በመመኘት ከተጫዋቹ ጋር ተለያይቷል፡፡

የማንቼስተር ዩናይትድ እና የጁቬንቱስ የቀድሞ ኮከብ ከሀገሩ ፈረንሳይ ጋር በ2018 የዓለም ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል፡፡

የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ቀጣይ ማረፊያ የሚጠበቅ ይሆናል፡፡
Пост от 18.08.2026 20:06
1
0
0
ሮድሪ ባርሴሎናን ተቀላቀለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አማካይ ሮድሪጎ ሄርናንዴዝ ባርሴሎናን ተቀላቀለ፡፡

ሮድሪ በሰባት ዓመታት የማንቼስተር ሲቲ ቆይታው አንድ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግና አራት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን ጨምሮ በርካታ ዋንጫዎችን ከክለቡ ጋር ማሳካት ችሏል፡፡

የባሎንዶር አሻናፊ የሆነው ሮድሪ በካታላኑ ክለብ እሰከ ፈረንጆቹ 2030 የሚያቆየውን ውል ፈርሟል፡፡

የቀድሞ የቪያሪያል፣ አትሌቲኮ ማድሪድ እና ማንቼስተር ሲቲ ተጫዋች ለሃንሲ ፍሊኩ ባርሴሎና ሌላ የስኬት ኃይል እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

በአቤል ነዋይ
Пост от 18.08.2026 17:24
1
0
0
ፓትሪክ ቪዬራ የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው አሰልጣኝ ፓትሪክ ቪዬራ የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ፡፡

የ50 ዓመቱ አሰልጣኝ ፓትሪክ ቪዬራ በሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን የሚያቆየውን የአራት ዓመት ውል ተፈራርሟል፡፡

ቪዬራ በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ብሔራዊ ቡድኑን ፍጻሜ ማድረስ እና ለ2030 የዓለም ዋንጫ ማሳለፍ ይጠበቅበታል፡፡

ፓትሪክ ቪዬራ ከዚህ ቀደም ኒውዮርክ ሲቲ፣ ኒስ፣ ክሪስታል ፓላስ፣ ስትራስቡርግ እና ዥኖአን ማሰልጠኑ ይታወሳል፡፡
Пост от 16.08.2026 22:46
85
0
1
ባርሴሎና ሮድሪን ከማንቼስተር ሲቲ ለማስፈረም ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ባርሴሎና ስፔናዊውን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ሮድሪ ከማንቼስተር ሲቲ ለማስፈረም ተስማምቷል።

ሮድሪ በባርሴሎና ለ4 ዓመታት የሚያቆየውን ውል እንደሚፈራረም ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።

የ30 ዓመቱ ተጫዋች በማንቼስተር ሲቲ ቤት ቆይታው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል።
Пост от 16.08.2026 19:40
183
0
1
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ 2ኛ ጨዋታውን የሚያደርግበት ቀን ታወቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ 2ኛ ጨዋታውን የሚያደርግበት ቀን ታወቀ፡፡

በዚህም መሰረት በ2027 የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 10 ሁለተኛ የምድብ ጨዋታውን ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር በባህር ዳር ስታዲየም መስከረም 19 ቀን 2019 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ የሚያከናውን ይሆናል።

ካፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የሜዳ ጨዋታውን በባህር ዳር ስታዲየም እንዲያከናውን ጊዜያዊ ፈቃድ መስጠቱ ይታወሳል።

ዋልያዎቹ ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዎች ዝግጅታቸውን መጀመራቸው ይታወቃል፡፡
Смотреть все посты