Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «WALTA TV»

WALTA TV
20.0K
13.6K
205
109
72.1K
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://www.facebook.com/wmcc
Подписчики
Всего
36 553
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
2 363
ER
Общий
6.44%
Суточный
3.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 19 987 постов
Смотреть все посты
Пост от 28.07.2026 17:17
625
0
2
የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀምርበት ቀን ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር የሚጀምርበት ቀን ይፋ ሆኗል፡፡

በዚህም መሰረት አዲሱ የውድድር ዓመት መስከረም 30 ቀን 2019 ዓ.ም እንደሚጀምር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ለሊጉ ተሳታፊ ክለቦች በዛሬው ዕለት አሳውቋል።
Пост от 28.07.2026 15:32
395
0
1
ማንቼስተር ሲቲ የጆስኮ ግቫርዲዮልን ውል አራዘመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋቹን ጆስኮ ግቫርዲዮል ውል ለተጨማሪ ዓመታት ማራዘሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ክሮሺያዊው የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች በውሉ መሰረት እስከ ፈረንጆቹ 2031 ድረስ በማንቼስተር ሲቲ ቤት የሚቆይ ይሆናል፡፡

ጆስኮ ግቫርዲዮል በ2023 በ90 ሚሊየን ዩሮ ማንቼስተር ሲቲን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

የ24 ዓመቱ ተጫዋች ከማንቼስተር ሲቲ ጋር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ፣ የዓለም ክለቦች ዋንጫ እና የአውሮፓ ሱፐር ካፕን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡

ግቫርዲዮል ማንቼስተር ሲቲን ከተቀላቀለ ወዲህ ለቡድኑ 122 ጨዋታዎችን አድርጎ 13 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
Пост от 28.07.2026 12:52
265
0
4
ዚነዲን ዚዳን የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዚነዲን ዚዳን የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ፡፡

ፈረንሳዊው አሰልጣኝ ዚነዲን ዚዳን ከአምስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ኃላፊነት ተመልሷል፡፡

ከ2026 የዓለም ዋንጫ መጠናቀቅ በኋላ ከአሰልጣኝ ዲዴ ዴሻምፕ ጋር የተለያየው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ተጫዋቹ ዚነዲን ዚዳንን አሰልጣኙ አድርጓል፡፡

የ54 ዓመቱ አሰልጣኝ ዚነዲን ዚዳን እስከ 2030 የዓለም ዋንጫ ድረስ የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡

የዚዳን የመጀመሪያ የነጥብ ጨዋታ ፈረንሳይ ከቱርክዬ ጋር በኔሽንስ ሊግ የምታደርገው መርሐ ግብር ይሆናል፡፡

የሪያል ማድሪድ የቀድሞ አሰልጣኝ ዚዳን በተከታታይ ሦስት ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በማንሳት ቀዳሚውና ብቸኛው አሰልጣኝ ነው፡፡

ዚዳን በተጫዋችነት ዘመኑ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንን ከፈረንጆቹ 1994 እስከ 2006 ያገለገለ ሲሆን፤ በፈረንጆቹ 1998 የዓለም ዋንጫን ከሀገሩ ጋር ማሳካቱ ይታወሳል፡፡

በተጫዋችነት ዘመኑ በፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን፣ በሪያል ማድሪድ እና በጁቬንቱስ ስኬታማ ጊዜ ያሳለፈው ዚዳን የባሎንዶር ሽልማት ማሸነፉም አይዘነጋም፡፡
Пост от 27.07.2026 14:36
164
0
2
ማንቼስተር ዩናይትድ ዌልሳዊውን ግብ ጠባቂ ኪት ማርጌሰን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ኪት ማርጌሰንን ከስዋንሲ ሲቲ ለማስፈረም በቡድኖቹ መካከል ከስምምነት ላይ ተደርሶ ዝውውሩ ተጠናቅቋል፡፡

የ20 ዓመቱ ግብ ጠባቂ ኪት ማርጌሰን የመጀመሪያ ኢንተርናሽናል ጨዋታውን ባሳለፍነው መጋቢት ወር ለሀገሩ ዌልስ ከ 21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ተሰልፎ ተጫውቷል።

የስዋንሲ ሲቲ አካዳሚ ፍሬ ለሆነው ግብ ጠባቂ ዝውውርም ማንቼስተር ዩናይትዶች የካሳ ክፍያ ለሻምፒዮንሺፑ ክለብ እንደሚከፍሉ ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትዶች ቡድናቸውን ለማጠናከር በዝውውር መስኮቱ በንቃት እየተሳተፉ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
Пост от 26.07.2026 15:31
1 774
0
2
አቶ ቢኒያም ነገሱ የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አቶ ቢኒያም ነገሱ የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን በዛሬው ዕለት መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዷል፡፡

በዚህም አቶ ቢኒያም ነገሱ ፌዴሬሽኑን ለሚቀጥሉት 4 ዓመታት በፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ በአብላጫ ድምጽ ተመርጠዋል።

አቶ ቢኒያም ከምርጫው በኋላ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በሰጡት አስተያየት፤ የኢትዮጵያ ብስክሌት በዓለም ቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ለማድረግ እሰራለሁ ብለዋል።

በሰለሞን በቀለ
Пост от 22.07.2026 21:18
386
0
2
ኢንተር ሚያሚ ካሴሚሮን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሜጀር ሊግ ሶከሩ ኢንተር ሚያሚ ብራዚላዊውን አማካይ ካሴሚሮን አስፈርሟል፡፡

የሪያል ማድሪድና ማንቼስተር ዩናይትድ የቀድሞ ኮከብ ካሴሚሮ ኢንተር ሚያሚን በፈረንጆቹ እስከ 2027 በሚቆይ ኮንትራት የተቀላቀለ ሲሆን÷ ውሉ እስከ 2029 ሊታደስ የሚችልበት ሁኔታ መኖሩን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡

የ34 ዓመቱ ካሴሚሮ በያዝነው ክረምት ከማንቼስተር ዩናይትድ ጋር መለያየቱ ይታወሳል፡፡

ተጫዋቹ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ሀገሩ ብራዚልን ወክሎም ተጫውቷል፡፡
Пост от 21.07.2026 13:09
775
0
1
የመቻል እግር ኳስ ክለብ ውበቱ አባተን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመቻል እግር ኳስ ክለብ ውበቱ አባተን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ፡፡

አሰልጣኙ ከመቻል እግር ኳስ ክለብ ጋር ለሁለት ዓመታት የሚያቆይ ውል ተፈራርመዋል፡፡

በውሉ መሠረት አሰልጣኙ ክለቡን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ተፎካካሪ ከማድረግ ባለፈ ዋንጫ የማሳካት ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ጨምሮ ሰበታ ከተማ፣ ፋሲል ከነማ፣ ኢትዮጵያ ቡና፣ ሀዋሳ ከተማ፣ አዳማ ከተማ እንዲሁም ከሀገር ውጪ የሱዳኑ አል ሀሊ ሸንዲ እና የደቡብ ሱዳኑን ጃሙስ ክለብን አሰልጥኗል፡፡

በሰለሞን በቀለ
Смотреть все посты