ድርቅና ረሃብን ለመቆጣጠር የተደረጉ እንቅስቃሴዎች (1966-1983)
የሠፈራ መርሃ ግብር በወለጋ
--
ከ1966---1978 የወለጋ ህዝብ ለሰፈራ የተቀበላቸዉ ተረጂ ወገኖቻችን 252,174 ነበሩ:: ከእነዚህ ሠፋሪዎች ውስጥ 59 በመቶ የሚሆኑት የሰፈሩት በወለጋ፣ 19 በመቶ ኢሉባቡር 14 በመቶ ከፋ፣ እና 8 በመቶ ጎጃም ነው። ብዙ ሕዝብ የሠፈረበት አከባቢ በወለጋ በ1977 ዓም 246,268፣ በ1978 ዓም 252,714 በ1979 ዓም 128,717 በ198 ዓም 128,311 በ1981 ዓም 124,884 ነው።
የሰፈራ መርሃ ግብር በስፋት የተጀመረው በ1977 ዓም የሠፈራ ባለሥልጣን በአዋጅ ከዕማማኮ ጋር ከተዋሃደ በኋላ ነው። መጀመሪያ በጅባትና ሜጫ አውራጃ ሀሮሌና በደሌ በሚባሉት ቀበሌዎች ሠፈራ በስፋት የተሠራ ስሆን በ1977 ዓም ከወሎ 300,000 ሕዝብ ለማስፈር ተወስኖ እንቅስቃሴ ተጀመረ። ሰፈራው ሁለት ዓይነት ስሆን አንዱ ስግሰጋ ነበር። ማለትም ባሉ ገበሬ ማህበሮች ውስጥ ሰፋሪዎችን በትርፍ ቦታ መሰግሰግ ነበር። ሁለተኛው ደግሞ ድንግሉ መሬት ላይ የሚደረገው ሰፋፊ ሠፈራ ነው።
በ1981ዓ/ም ቆጠራ 124,884 የሚሆኑ ሰፋሪዎች ጠፍተዉ ወደ መጡበት ተመልሰዋል÷ወይም ኮብልለዋል:: የቀድሞዉ እማማኮ (ማለትም የዕርዳታ ማስተባበርያና ማቋቋሚያ ኮሚሽን) ኮሚሽኔር በነበሩት አቶ ሺመልስ አዱኛ" ድርቅና ረሀብን ለመቋቋም የተደረጉ ጥረቶችና እንቅስቃሴዎች ከ1966-1983" በሚል ተዘጋጅቶ በ1997 የታተመዉ ጥናት ሰፋሪዎቹ አዲሱን የሰፈራ መንደራቸውን ስለሚለቁበት ጉዳይ 8 ምክንያቶችን ዘርዝረዉ ጽፈዋል::
ምንጭ: ድርቅና ረሃብን ለመቆጣጠር የተደረጉ እንቅስቃሴዎች (1966-1983) በሽመልስ አዱኛ
Horn Insight HI