Каталог каналов Новое Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Мониторинг Новое Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
736
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 316
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
267
ER
Общий
13.69%
Суточный
15%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 736 постов
Смотреть все посты
Пост от 19.11.2025 17:00
46
0
0
(ባለጠጋው ጌታ ) ማቴ 20:1-16 #የምህረትና የፀጋ ባለጠግነት በፊሊሞን ነጋ @cgfsd
Видео/гифка
5
Пост от 19.11.2025 05:52
147
0
1
(የለፋበት ያቀዋል)  ቤተሰቦቼን ሁልጊዜ የምለምናቸው ልመና ውሻ ማሳደግ እፈልጋለሁ ፍቀዱልኝ የሚል ነበር ። ቤተሰቦቼ ደስተኛ ባይሆኑም እንኳን እንዳሳድግ  ፈቀዱልኝ ። የስምንት አመት ልጅ ነበርኩኝ ። ስለተፈቀደልኝ ደስታዬ ወደር አልነበረውም ። ውሻ ማፈላለግ ጀመርኩ ። ራቅ ያለ ሰፈር ስዞር አንድ ከተወለደ ብዙም ያልቆዬ ቡችላ አገኸው ።  ከባለቤቶቹ ጋር በልጅነት ልመና አንጀታቸውን በልቼ እንድወስድ ተፈቀደልኝ ። እየፈነደኩኝ ከቡችላም ያነሰችውን ውሻ ይዤ ወደቤቴ ተመለስኩ ። የውሻ ቤት ለማሰራት አናጢ ባለሙያ አስመጥተን ከአባቴ ጋር አሰራን ። አባቴ ለውሻ ዋና ነገሩ አስተዳደጉ እሱ ተጠንቀቅ አለኝ ። በመንደራችን የሚፈራ ውሻ ወዳለበት ቤት የውሻ አስተዳደግ ልምድ ለመቅሰም መመላለስ ያዝኩ ። እንዴት ውሻውን እንዳሳደገ ደጋግሜ እየጠየኩ እስኪደክመው ድረስ ለቀናት አሳለቸሁት ። እንዴት እንዳሳደገው ነገረኝ "  ጉድጓድ ቆፈርኩ ከዛ ላይ በጉድጓዱ ላይ ትልልቅ የመኪና ጎማ ደራረብኩበት ፣ ውሻ በቂ አየር እንዲያገኝ አድርጌ አስገባሁት ። ሰው ሳያየው ሰፋ ባለው ጉድጓድ ውስጥ አደገ ። ከዛ ከ2 ወር በኋላ ማንም የማይጠጋው አራስ ነብር ይሆናል አለኝ "።  አመስግኜ ወደቤቴ ተመለስኩ ። ከአባቴ ጋር ሰው በማይጠጋበት አካባቢ ሰፊ ጉድጓድ ቆፍረን ትልልቅ ጎማ ደራርብን ለተወሰነ ጊዜ በዛ ተደብቆ እንዲቆይ አደረግነው ። እንደተባለ ሃይለኛ የሚፈራ ውሻ ሲሆን ለውጡን አስተዋልን ። ምግብ መመገብ ስላለበት ጠዋት ት/ቤት ከመሄዴ በፊት ከሰፈራችን 8 ደቂቃ መንገድ የሚያስኬድ ስጋ ቤት እየተመላለስኩ በ2 ብር ሳንባ ኮንትራት ለውሻው አመጣ ነበር ። እየወፈረና ሰውነቱም የምግብ ፍለጎቱ ሲጨምር እንዳንዴ ከቄራም ይመጣለታል ።  ማታ ሶስት ሰአት ከመተኛቴ በፊት  እፈታዋለው ጠዋት አስራ ሁለት ሰአት ስጋው ላመጣለት ስወጣ  አስሬው ወጣለሁ ። ከአባቴና ከእኔ በቀር ማንም አለመደም ነበር ። አንዳንድ ጊዜ ሰንሰለት እየበጠሰ ሰው ይተናኮል ነበር ። በማደጉ ፣ በመወፈሩ ደስታኛ ሆንኩ ። ክረምት ሲመጣ ዘመድ ጥየቃ ወደ አዲስ አበባ ለረፍት ተጓዝኩ ። የክረምት ቆይታዬን ጨርሼ ወደ መስከረም ወደ ቤት ስመለለስ ። ያ ለአንድ አመት ያሳደኩት ተወዳጁና አስፈሪው ውሻዬ ቤት ውስጥ የለም ። የመሰለኝ እንደ ሁልጊዜው ሰንሰለት በጥሶ ወጥቶ መስሎኝ ጠበኩ የለም ። ቤተሰቦቼን ስጠይቅ ሩቅ ቦታ ወደስደው እንደጣሉት ነገሩኝ ። እንዲህ ነው የሚባል ምንም ምክኒያት አልሰጡኝም ። ለእኔ የልብ ስብራት ነበር ። የለፋበት ያቀዋል  በጠዋት ተነስቶ ስጋ እያመጣ የመገበው ፣ እያጠበ ፣ለረጅም ወራት ያሳደገ የደከመበት ያቀዋል ። ህመሙም ደስታውም የለፋበትን ሰው ጋር አለ ። እግዚአብሔር ግን እንዲህ አለው፤ “አንተ እንዲበቅል ወይም እንዲያድግ ላልደከምክበት ለዚህ ቅል እጅግ አዝነሃል፤ በአንድ ሌሊት በቀለ፤ በአንድ ሌሊትም ደረቀ።  ታዲያ፣ እኔ ቀኝና ግራቸውን ለይተው መናገር የማይችሉ፣ ከአንድ መቶ ሃያ ሺህ በላይ ሰዎችና አያሌ እንስሶች ለሚኖሩባት ለታላቋ ከተማ ለነነዌ ማዘን አይገባኝምን?” ዮናስ 4:10-11 የነነዌ መትረፍ ለእግዚአብሔር የለፋበት ህዝብ ነው ምክኒያቱም ፈጥሮታልና ። ዮናስ ደግሞ ነነዌ እንዲመለሱ አልፈለገም ። የነነዌ መትረፍ የእግዚአብሔር ትግስት ፣ እነርሱን በትዕግስት የመፈለግ ውጤት ነው ። ዛሬም የሰዎች መዳን በእግዚአብሔር አይን ሲታይ የለፋበት ያቀዋል ነው ። እግዚአብሔር ሰው እንዲድን ተግቷል ፤  ደም ዋጋ የተከፈለበት ፤እግዚአብሔር ፍቅሩን ያፈሰሰበት ታሪክ ነው ። የሰዎች መዳን ለእግዚአብሔር የለፋበት ያቀዋል ነው ። @cgfsd
16
🔥 7
👍 1
Пост от 18.11.2025 11:35
184
0
1
አባካኙ ልጅና አባካኙ አባት ! አባካኙ ልጅ የአባቱን ገንዘብ በተነው የአባቱን ንብረት መንገድ ላይ ትርፍ ለሌው ጉዳይ አባክኖት ቀረ ። አባካኙ አባት ግን ልቡን ፣ርህራሄውንና ትግስቱን ልጁን በመፈለግ ልጁ ላይ አባከነው  ።አባካኙ አባት ያፈሰሰው(ያባከነው) ፍቅር የማይጠፋ ባዶ እጅ የማያስቀር ነው ።
18
😢 2
Пост от 17.11.2025 22:45
253
0
4
ለሰው ሁሉን አለመቻል ፀጋ ነው ! ✍️ ዲአመ
🥰 18
12
👍 3
Пост от 10.11.2025 09:28
280
0
1
በአንድ ሰው መተላለፍ ምክንያት ሞት በዚህ ሰው በኩል የነገሠ ከሆነ የእግዚአብሔርን የተትረፈረፈ ጸጋና የጽድቅ ስጦታ የተቀበሉት በአንዱ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እንዴት አብልጠው በሕይወት አይነግሡ! ሮሜ 5 :17 ሞት ብቻውን ነገሰ ኢየሱስ አብሮ ነጋሽ አደረገን የመዳን ውበቱ ኢየሱስ ጋር አብሮ መክበሩ ነው። ኢየሱስ ጋር አብሮ መክበር ለአክባሪው ማንነት በፍፁም መገዛት እየተገዙ መክበር ነው ። @cgfsd
19
🥰 2
Пост от 09.11.2025 14:54
301
0
4
የማይተረጎም መውደድ በርከት ያሉ የእብራይስጥ ቃላት ወደ ተለያዮ ቋንቋዎች ሲተረጓሙ አንዳንድ ቃላት ግን በቀጥታ ከእብራይስጥ የተወሰዱ ቃላቶች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይገኛሉ፤ ሃሌሉያ፣ ኪሩብ እና ሆሳእናን እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል። የቅዱሳት መጽሐፍት ተርጓሚዎች "ሄሴድ"(חֶסֶד chesed) ለሚለው ቃልም ተመሳሳይ መንገድን ቢጠቀሙ መልካም ነበር ይባላል። በቀጥታ ቃሉን ቢጠቀሙ የቃሉን የትርጓሜ ሃብት የሚያሳይ ከመሆኑ የተነሳ እንደወረደ ቢቀመጥ ብለው የሚመኙ ብዙዎች ናቸው። ለዚህ ቃል አቻ የሚሆን ትርጓሜ የለውም ተብሎም ይሞገታል። ሲተረጓም "ምኅረት፣ ቸርነት፣ መልካምነት፣ ርኅራኄ፣ ዘላለማዊ ፍቅርና ወዘተ" ተብሎ ነው በአማርኛችን የተተረጓመው። ነገር ግን ሄሴድ የሚልን ቃል በተወሰኑ የአማርኛ ቃላቶች መወሰን ቃሉ የተሸከመውን ትልቅ ነገረ መለኮታዊ ሃሳብና እግዚአብሔራዊ ማንነት መጨቆን ይመስላል ይላሉ ከሃሳቡ ተነስተው። ትርጓሜው ውቅያኖስን በኩባያ የመጨለፍ ያህል ነው። የብሉይ ኪዳን ተንታኙ ቻድ በርድ እንደምሣሌ መዝሙር 36 ላይ ሄሴድ ሶስቴ የሚመጣበትን መንገድ ያስረዳል። (ቁ5) እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ [ሄሴድህ] እስከ ሰማያት ይደርሳል፤ ታማኝነትህም እስከ ጠፈር ይመጥቃል። (ቁ7)አምላክ ሆይ፤ ምሕረትህ [ሄሴድህ] እንዴት ክቡር ነው! የሰዎች ልጆች ሁሉ፣ በክንፎችህ ጥላ ሥር መጠጊያ ያገኛሉ። (ቁ10) ለሚያውቁህ ምሕረትህ [ሄሴድህ]፣ ልባቸውም ለቀና ጽድቅህ ዘወትር አይቋረጥባቸው። መዝሙር 36፥5፣ 7ና 10 (አጽንዖት የተጨመረ) . ሄሴድ ለትርጓሜ አዳጋች የሆነ የያሕዌን ፍቅርን የሚገልጽ ነው። ምሕረት የሚለው ቃል ሊሸከመው አይችልም። ሄሴድ የእግዚአብሔርን ቃልኪዳናዊ ታማኝነት አንድያ ልጁን በመስቀል እስከማንጠልጠል ያደረሰ ነው። በመስቀሉ የተገለጠ የእግዚአብሔር ልብ ነው። እስከ ምድረ ጥግ የሚከታተለን ፍቅር፣ የሚያነሳንና እንደ መልካም እረኛ በትከሻው የሚሸከመን ብሎም ወደ ቤት የሚወስደን አይነት ፍቅር ነው። ሄሴድ የሚለውን ቃል በተሟላ መልኩ ሊገልጸውና ሊያብራራው የሚችል አንድ ስም ብቻ አለ፤ ክርስቶስ ይባላል። እርሱ አብ ስጋ ይሆን ዘንድ የላከው እውነተኛ ሄሴድ ነው። የእግዚአብሔርን ሃሳብ በስጋ የገለጠ የፍቅርና ርህርሄ፣ የእንክብካቤና ቸርነት ሁሉ ቁንጮ ነው። የያሕዌ ሄሴድ በክርስቶስ ተገለጠ! እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህንና ፍቅርህን ዐስብ [ሄሴድህን] ዐስብ፤ እነዚህ ከጥንት የነበሩ ናቸውና። መዝሙር 25፥6 (አጽንኦት የተጨመረ) መልካም ሰንበት! (ከቻድ በርድ Unveiling Mercy: 365 Daily Devotions Based on Insights from Old Testament Hebrew የተወሰደ) ✍️ አማኑኤል አሰግድ
14
🔥 1
Пост от 06.11.2025 10:23
409
0
0
ሞት ለእኛ  በዲያብሎስ የተረገጥንበት ነው ። ሞት ለክርስቶስ ዲያብሎስን ድል የነሳበት፣ የሞት ኋይሉን የሻረበት ነው ። በዚህ አኳኋን ሞቱ ንግስናውን (ንጉስነቱን) የገለጠበት ነው ።      ማስያስ (ዲያቆን ሚክያስ አስረስ) @cgfsd
14
🔥 4
Смотреть все посты