Каталог каналов Новое Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Мониторинг Новое Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
736
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 345
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
388
ER
Общий
20.07%
Суточный
13.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 736 постов
Смотреть все посты
Пост от 26.12.2025 22:46
113
0
3
(ጥሬ ፀሎት) ጥሬ ፀሎት የሚለው ቃል ፍሊፕ ያንሲን የሚጠቀመው ቃል ነው ። ያልተቀባባ ፀሎት ፣ ያልተሸፋፈነ ፀሎት እንደማለት ነው ። እግዚአብሔር ጥሬ ፀሎት ይወዳል ።  ጥሬ ፀሎት የሆንነውን ነን የምንልበት ፣ ያልቻልነውን አልቻልንም የምንልበት  ንፁህ ያልተቀባባ ፀሎት ነው ። የፈሪሳዊ ፀሎትና የቀራጩ ፀሎት በግልፅ የምናየው አይነተኛ ፀሎት ነው (ሉቃስ 18) ። ፈሪሳዊ ቅብ ፀሎት ያለበት ይመስላል ፣ በፀሎቱ ውስጥ ይመፃደቃል ፣ ራሱን በትዕቢት ይወጥራል ፣ ራሱን ከቀራጮች ጋር ያወዳድራል ። ቀራጩ ደግሞ አይኑን ቀና ማድረግ ከብዶት ፤ ደረቱን እየደቃ በድያለው ማረኝ ይላል  ። በጌታ ኢየሱስ ፊት ቀራጩ የፀለየው ፀሎት ጥሬ ፀሎት ነው ። በእግዚአብሔር ፊት ያልተቀባባ ፀሎት ነው ። የፈሪሳዊ ደግሞ ቅብ ፀሎት ራስን ፅድቅ ማስቆጠር የንግግር ችሎት የሚታይበት ፀሎት ነው ። በእግዚአብሔር ፊት ስንሆን በእግዚአብሔር ፊት እንደሆንን ማወቅ አለብን ። እግዚአብሔር ፊት የሚደበቅ የሚሰወር ምንም ነገር የለም ። በፊቱ ስንቀርብ እሱን በእርግጥም ስለሚያየን ራሳችን አጋልጠን መሆን አለበት ። ጥሬ ፀሎት በእግዚአብሔር እጅ ላይ መዋረድ ነው ። ፀሎት ላይ ስሌት ሳይሆን የሚያዋጣው ፍሰት ነው የተሻለው ። በእግዚአብሔር ፊት ማስላት ሳይሆን በእግዚአብሔር ፊት መፍሰስ  ነው ትልቁ ጉዳይ ለዚህም ነው ያልተቀባባ ጥሬ ፀሎት ያስፈለገው ። @cgfsd
🔥 8
5
Пост от 26.12.2025 18:17
178
1
0
Изображение
10
🔥 2
Пост от 24.12.2025 09:07
255
0
4
ከመስቀሉ ፊቱን የሚያዞር ሰው ከእግዚአብሔር ነው ፊቱን የሚያዞረው እግዚአብሔር የተገለጠው በዛ ስፍራ ስለሆነ ።         ጳውሎስ ፈቃዱ
🔥 18
8
👍 2
Пост от 23.12.2025 19:03
362
1
5
Видео/гифка
13
👍 2
Пост от 21.12.2025 22:59
432
0
4
(ሳለ-አይሰጥ ) ስጋ ተመጋቢ አልፎም አጥንት ወዳጅ የሆነ ሰው ስለ ሳለ-አይሰጥ በደንብ አድርጎ ያውቃል ። በሳለ-አይሰጥ አጥንት የማይማረር ተመጋቢ አይኖርም ። ይሔ አጥንት ስጋ ያለው ነው ፤ ሲታይ ደስ ይላል ፣ ብሉኝ ፣ ብሉኝ ያሰኛል ነገር ግን ለመብላት አይመችም ። ምንም እንኳን ስጋ ያለው ቢሆንም  ዙሪያ ያለው አጥንት ወጣ ገባ ያለ በመሆኑ ለመብላት አዳጋችና ከባድ ያረገዋል ። ስለዚህ ስጋ እያለው አይሰጥም በሚል ሀሳብ ይሔ አጥንት ሳለ-አይሰጥ የሚል ስያሜ ወጣለት ።  ስጋ እያለው አይሰጥም ! ሳለ-አይሰጥ ለመንፈሳዊ ህይወታችን ጥሩ ምሳሌ ሊሆን የሚችል ማሳያ ነው ። ጥሩ ነገር እያለን ፣ ፀጋ እያለን ፣ በጎ መንፈሳዊ ልምምዶች እያሉን ፤  ለሌላው ለማካፈል ፣ ለመቆረስ አለመመቸት የሳለ-አይሰጥ ምሳሌ ነው ። በጎ መንፈሳዊ ልምምድ ፣ ዕውቀት አለን ማለት ለሌላው የምንመች የምናካፍል ነን ማለት አይደለም ። ክርስቲያን የክርስቶስ ህይወትና ብርሃን እያለው ግን ለሌሎች የማይመች የባህሪ ችግር ካለበት ፤  ስጋ እያለው ለመብላት እንዳልተመቸው አጥንት ምሳሌ ይሆናል ። ክርስቲያን ነኝ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚቆረስ የሚበላ ህይወትና ባህሪ አለን? የሚለው የሁልጊዜ ጥያቄ ነው ። ከሳለ-አይሰጥ ጌታ ይጠብቀን ። @cgfsd
12
🔥 6
Пост от 21.12.2025 08:02
398
0
2
(ሶስቱ ዘፀአት ) ዘፀአት ትክክለኛ ትርጓሜው መውጣት ማለት ነው ። ይሔን ሀሳብ በይበልጥ የምናውቀው እስራኤላዊያን ከ430 ሰላሳ አመት ከግብፅ ባርነት የወጡትን መውጣት ያሳያል ። ሶስት ዘፀአት በመፀሃፍ ቅዱሳችን እንደነበረ በግልፅ እንመለከታለን ። የመጀመሪያው በግብፅ የነበረው ዘፀአት ነው ፣ ሁለተኛው በባቢሎን የታየው ዘፀአት ፣ ሶስተኛ ደግሞ በኢየሩሳሌም የሆነው ታላቁ ዘፀአት ነው ። የግብፅ ዘፀአት(መውጣት) እስራኤላዊያን እየደረሰባቸው ከነበረው አስከፊ ባርነት የወጡት መውጣት ነው ። በዚህ ዘፀአት ዋነኛ አላማው ከባርነት ህዝቡን ማላቀቅ ይሁን እንጂ  መጨረሻ ዋነኛው የሆነው በእስራኤል አምላክ እንዳለ በግብፅም ሆነ በቀሩት የአህዛብ መንግስታት መካከል የእግዚአብሔር ስም ታወቀ ፤ ስሙ ከፍ አለ ። የፀና ክንዱ ፤ የበረታች እጁ በሁሉ ታየ ። በዚህ መውጣት ዘፀአት ውስጥ በርካታ ተአምራት ተደርገዋል ከተአምራቱ ጀርባ ያለው ከግብፅ አማልክት በላይ እግዚአብሔር አምላክ እንደሆነ ታየበት ። በግብፅ የተደረጉት አስሩም መቅሰፍትና ተአምራት በግብፅ እንደ አምላክ ይቆጠሩ ነበር ። ለምሳሌ ጓጉንቸር ይመለካል ፣ ውሃ ወደ ደም ሲቀየር ውሃ ይመለክ ነበር ፣ በኩር ሲሞት በኩር ይመለክ ነበር ። በግብፅ ዘፀአት የተደረገው ተአምራት እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ እንደሆነ ስሙ የገነነበት ዘፀአት ነበር ። ከባርነት ተላቀው ባደረጉ የአርባ አመት ጉዞአቸው ውስጥ የእግዚአብሔር ያልተቋረጠ አቅርቦትና መጋቢነት ነበር ። መና ይመገባሉ ፣ የማያልቅ ልብስ ይለብሳሉ ። እግዚአብሔር ከበረበት ! ሁለተኛ ዘፀአት ደግሞ በባቢሎን የነበረው ዘፀአት ነው ። ህዝበ እስራኤል ወደ ባቢሎን ለሰባ አመታት በግዞት ተወስደዋል ።  በባቢሎን ቆይታቸው የኩራት የክብር መገለጫ የሆነው የኢየሩሳሌሙ መቅደስ ፈረሰ ፣ ህዝቡ ተሰደበ፣ የከተማው በር ቅጥሮች ፈረሱ ፣ ከተማው ወደመ ። በባቢሎን ምርኮ ሁነው ህጉን መማር ናፈቃቸው  ። እግዚአብሔር 70 አመቱ አልቆ በባቢሎን ፈንታ ፋርስ ሲነግስ ። እስራኤላዊያን መመለስ ጀመሩ ። የባብሊሎን ዘፀአት መንፈሳዊ ተሃድሶ ያለው ነበር ። ይሔ ዘፀአት የእግዚአብሔር ፊት ለመፈለግ የመጡበት ነበር ፣ መቅደሱን ለመስራት የተመለሱበት በዓላማ የወጡበት ዘፀአት ነበር ። በባቢሎን ዘፀአት ምንም እንኳን መከራ ቢኖረውም እግዚአብሔር ስሙ በእነ ዳንኤል የከረበት የእስራኤል አምላክ ተብሎ ስሙ የተጠራበት ነበር ።ከዚህ ዘፀአት ጀርባ የእግዚአብሔር ስም የከበረበት ነበር ። ሶስተኛው ዘፀአት በመፀሃፍ ቅዱሳችን የተገለጠው የኢየሩሳሌሙ አዲሱ ዘፀአት ወይም መውጣት ነው ። ይሔ መውጣት በክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ የተፈፀመ መውጣት ነው ። ሰው ተረግጦ ከተያዘበት የሀጢያት ፣ የሞት ፣ የሰይጣን ባረነት በክርስቶስ ህይወት ፣ ሞትና ትንሳኤ ሊወጣ ዘፀአት ሊሆን ተችሏል ። በዚህ ምክኒያት በዚሁም ዘፀአት መውጣት ውስጥ እግዚአብሔር ከበረ ሰውን የገዛውን የሀጢያትና የሞት ሰንሰለት ስለተበጠሰ እግዚአብሔ ስለ ፀጋው ክብር ከበረ ። ዘፀአት መውጣት  ለምን ሆነ  ? ለምን ?ወጡ ሲባል  በአላማ ተለይተው ለእግዚአብሔር ህዝብ ለመሆን ወጥተዋል (ዘፀአት) ሁኗል ይባላል ። ይሔ በክርስቶስ የተፈፀመው አዲሱና ታላቁ ዘፀአት አስደናቂዊ ነው ። ሉቃስ 9 ላይ እንደምናገኘው ታሪክ በኢየሱስ የተፈፀመው ዘፀአት ታላቅ መሆኑን እናያለን ። በግብፅ ዘፀአት የሚታወቀው ሙሴ ፣ በነብይነት የሚታወቀው ኤሊያስ በደብረታቦር ተራራ ኢየሱስ ጋር ሲገናኙ ከብዙ አመት በኋላ ቢሆንም  የተገለጡት ከኢየሱስ ጋር ያደረጉት ንግግር በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው መውጣት(ዘፀአት) ነው ፤ እንጂ ስለ ግብፁ ዘፀአት ትንታኔ አልሰጡም ። ከሁሉ እንደሚበልጥ ምስክር ናቸው ። በዚህ ዘፀአት የእግዚአብሔር ህዝብ መሆንን፣ ዘላለማዊ ተስፋ ፣ የመዳን ብድራት ታይቶበታል ። በክርስቶስ መውለድ ፣ ሞትና ትንሳኤ ያየነው ዘፀአት ታላቁ ዘፀአት (The Great Exodus )ነው ። በታላቁ ዘፀአት ታላቁ እግዚአብሔር ታላቅ እንደሆነ ታየ ። @cgfsd
10
👏 3
Пост от 20.12.2025 13:05
366
0
1
(ክርስቶስ ወገኔ ) የክርስቶስ ሰው መሆን እንደ ቀላል የማይታይ ክስተት ነው ። የፈጠረውን ፍጥረት ከመሆን ወዲያ ምን ጉድ አለ። አባቶች እንደፃፉት ፣ ዘማሪያን እንዳዜሙት በጠባብ ደረት በአጭር ቁመት ከመታየት በላይ ምን ይገርማል ። ይሔ ነገር ገርሞት ይሆናል ሉተር በቻለው መጠን የኢየሱስን ፍፁም ሰውነት ለማሳየት እንደሚታትር የተናገረው። ክርስቶስ ተዛምዶናል ! አዎን ከእኛ ወገን ሁኗል ። ሰው በመሆኑ የሰው ወገን ጋር ተካቷል የሰው ወገን በመሆን የሰው ሁሉ ዘመድ ሁኗል ። ግን ከሰው ሲዛመድ ከሰው ወገን ሲሆን ያለ ሀጠያት ነው ። በነገር ሁሉ እንደ ሰው ተፈትኗል  እንደ ሰው በነገር ሁሉ ሰው እንደሚያልፍ አልፏል ከሀጢያት በቀር (ዕብ 4:15)። ለዚህ ነው ክርስቶስ ወገን የሚባለው እንደ እኛው ስለሆነ ነው ።           ጳውሎስ ፈቃዱ ክርስቶስን " የኛ ሰው በሰማይ ይለዋል "። በጣም የምስማማበት  አገላለፅ ነው ። ክርስቶስ የኛ ወገን ነው ያው አሁን በሰማይ ያለን በአብ ዘንድ ስለ እኛ የታየ !! አዎ የኛ ወገን ።ደግሞ ወገንነቱ አንዴ ብቻ አይደለም ፤ የሚቀጥል ነው። በድካም ላለን አይዞን በርቱ ይላል ወገናችን የሰውነትን ድካም ያውቀዋል ።  ከሩቅ ቁሞ  አይደለም ሊያክመን የሞከረው እኛ መካከል አድሮ እኛን ሁኖ የተረዳን። ከዚህ ድካም ሊራራልን ይችላል በዚህ  ድካም እንዳንሰጠጥም ፀጋ እና ምህረትን ይሰጠናል እናም እንበረታለን ።  ታዋቂው ፀሃፊ ፊሊፕ ያንሲን በቁምላቸው ያላወቁት ኢየሱስ በማለት በተተረጎመው መፀሃፍ እንዲህ ይላሉ ።   " ኢየሱስ ከብዙ ነገሮች አንዱ ሰው የሆነው የኢዮብን ጥያቄ ለመመለስ ነው  ኢዬብ የስጋን አይን አለህን ብሎ ተከራክሯል ። " ፊሊፕ ያንሲን የኢዬብን ጥያቄ በኢየሱስ ተመልሷል ይሉናል ። ኢዬብ የስጋ አይን አለህን ማለቱ በስጋ አይን ታያለህን ስጋ ለብሰሃል የስጋን ድካም ሰው እንደሚያይ በዚህ ድካም ታያለህን እንደ ማለት ይመስላል ። አዎን ነዋ ወገን ሆን በስጋ አይን አየ ተረዳን ፣ መሰለን ፣ ከገባንበት  መውጫ በር ሆነን ። ተዛምዶን ሊጠጣ       ፅዋችን ቀዳ አምላክም ሰው ሆነ             እኛኑ ሊረዳ @cgfsd
12
🔥 6
Смотреть все посты