Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
1.0K
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 440
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
346
ER
Общий
19.04%
Суточный
13.1%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 1 041 поста
Смотреть все посты
Пост от 28.03.2026 19:11
122
0
3
...ሰው አምላክ ለመሆን በሚጣጣርበት አለም አምላክ ሰው ሆነ !
🥰 10
7
Пост от 27.03.2026 11:31
213
0
3
(መገለጡን መከተል)


መፀሃፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ከሚያሳስበን ነገሮች መሃል እግዚአብሔርን መፈለግ ዋነኛ የመፈጠራችንና የመዳናችን አላማ እንደሆነ ነው ። እግዚአብሔር ለመፈለግ ስናስብ በአዲስም ሆነ ብሉይ ኪዳን የተሻለ መንገድ እግዚአብሔር በተገለጠበት መንገድ እሱን መፈለግ ነው ። እግዚአብሔር መፈለግ ውል እንደሌለው ወይም  ወዳገኝበት አቅጣጫ ሁሉ እግዚአብሔርን አንፈልግም ምክኒያቱም እግዚአብሔርን ለመፈለግ ትክክለኛው መንገድ ራሱ እግዚአብሔር ነው ። እግዚአብሔር ከእኛ ረቂቅ በመሆኑ ራሱን በገለጠልን መንገድ ብቻ ነው የምናውቀው።

እግዚአብሔር በህዝቡ መሃል እንዲመለክ ፣ እንዲፈለግ ያደረገው ራሱን በመግለጥ ነው ። አብርሃምን እግዚአብሔር" እኔ ኤልሻዳይ ነኝ"በማለት ራሱን ገለጠለት (ዘፍ 17:1) አብርሃም የእግዚአብሔር አልሻዳይነት ማዕከል(center) ያደረገ ኑሮን ኖረ ። እግዚአብሔር ለሙሴ እኔ " የአባቶችህ የአብርሃም የይስሃቅ አምላክ እኔ ነኝ"  በማለት ራሱን ገለጠለት (ዘፀ3:6)።ሙሴም በተገለጠ መንገድ እግዚአብሔርን ፈለገው ።

እግዚአብሔር በብዙ ጎዳና ተናግር የነበረ ቢሆንም በተሻለ መንገድ በላቀ መንገድ በልጁ ተናገረ(ዕብ1:3) ።  እግዚአብሔር በልጁ  የተናገረው የሚገኘውን መዳንና ራሱን ማን  እንደሆነ ማንነቱን ነው ። የኢየሱስ ሰው መሆን አላማ ውስጥ ዋነኛው እግዚአብሔር በትክክል መግለጥ ነው ። እግዚአብሔር ራሱን በልጁ በኩል ገለጠልን ። እግዚአብሔር በተገለጠን መንገድ መፈለግ ትክክለኛው መፈለግ ነው ። እግዚአብሔር መፈለግ ስንል እግዚአብሔር ለማምለክ፣ ከእግዚአብሔር ህብረት ለማረግ ፣ እግዚአብሔር ለመምሰል ነው ። ለዚህ መፍትሔው ራሱን በተገለጠልን ደጋግሞ መፈለግ ነው ። መገለጡን መከተል መፈለጉን ትክክል ያረገዋል ።


@cgfsd
11
Пост от 26.03.2026 10:41
0
0
0
Пост от 26.03.2026 10:26
417
0
3
(ጵራቅሊጦስ በሰማይ ጵራቅሊጦስ በምድር)



በመፀሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ ጵራቅሊጦስ በሚለው ቃል ኢየሱስና መንፈስ ቅዱስ ተጠርተዋል ። መንፈስ ቅዱስ ከተጠራባቸው ስሞች መካከል አንዱ አፅናናኝ ወይም ጵራቅሊጦስ የሚል ነው (ዩሀ14:15-16) ። ጵራቅሊጦስ ማለት አፅናኝ የሚልም ትርጉም አለው ። መንፈስ ቅዱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ እንደተጠራ ሁሉ ጌታ ኢየሱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ ተጠርቷል (1ዩሀ 2:1) ። ኢየሱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ የተጠራው ጠበቃ በሚል ቃል ነው ። ጵራቅሊጦስ ትርጉሙ ውስጥ አፅናናኝ እንዳለ ሁሉም ሌላኛው ትርጉሙ ጠበቃ የሚል ፍቺ አለው ። ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ አፅናኝ ጵራቅሊጦስ ፤ ኢየሱስ ደግሞ ጠበቃ ጵራቅሊጦስ ተብለው ተጠርተዋል ።

ኢየሱስ በሰማይ ስለእኛ ያለ አጋዥ ጠበቃ ወገን ጵራቅሊጦስ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በእኛ ውስጥ ያለ የሚረዳን ረዳት አፅናኝ ጵራቅሊጦስ ፤ ይሔም በመሆኑ እጅግ አስደናቂ እርዳታ አለን ። የክርስትና ጉዞአችን በእግዚአብሔር ያለልክ የሚደገፍ በፀጋው የተትረፈረፈ እግዚአብሔር እኛ ጋር መሆኑን በብዙ መንገድ የታየበት ግሩም ጉዞ ነው ። በሰማይ ጠበቃ ጵራቅሊጦስ ኢየሱስ ስለ እኛ እየታየ በሊቀካህናዊ አገልግሎቱ እየደገፈን ያግዘናል (ዕብ 4:16) ። በዚህ ምድር ደግሞ አፅናኙ ጵራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ጥንካሬን ፣ ማፅናናት እያበዛ ፣ ድካማችን እያገዘ ይደግፈናል (ሮሜ8:26) ። እግዚአብሔር ደጋግፎናል ! ይደግፈናልም!

ጵራቅሊጦስ👉 ( አፅናኙ መንፈስ ቅዱስ) በምድር ላይ ለቅዱሳን አለኝታ ነው ።

ጵራቅሊጦስ 👉(ጠበቃው ኢየሱስ) በሰማይ ለቅዱሳኑ አለኝታ ነው።

@cgfsd
13
🔥 4
Пост от 25.03.2026 07:29
301
0
2
(ሸክም)



ሸክም ያጎብጣል፤ ሸክም ቀና ያረጋል ። የተሸከመ ሰው ያቀረቀረው ለተሸከመው ጉዳይ ነው ። ቀናም የሚለው ሸክሙን ለማረገፍ ነው ። ክርስትና የሸክም ህይወት ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም ። የተቀበልነው ህይወት በራሱ መቃተት አለው ፣ የተቀበልነው መንፈስ በራሱ መቃተት አለው(ሮሜ8:26-27) ፣ የቅዱሳን ህብረት የሸክም መከፋፈሪያ ስፍራም ነው ።

የዘጠኛ ክፍል ተማሪ እያለን አምስት የምንሆን ልጆች ሰኞ ማታ ማታ የኤፌሶን መፀሃፍ ለአንድ አመት የሚጠጋ ጊዜ እናጠና ነበር ። ሰፈራችን የተራራቀና ከትምህርት በኋላ ማታ ስለነበር የሚደረገው ፤ በቤተክርስቲያናችን ያለች የተወደደች እናት ቤት አስፈቅደን እሷ ቤት ነበር የምናደርገው። ከጥናት በኋላ በተደጋጋሚ በምናጠናው መካከል እጅግ በጣም ለሚሰማቸው ግልፅ የሆኑ ሁለት ወንድሞች ነበሩ ። በተደጋጋሚ የፀሎት ርዕስ ሸክም ያጋሩናል ። በዚህ ሀሳብ እንፀልይ ፣ ለጎረቤታችን እንደዚህ እንፀልይ ይሉንና ሸክም ያካፍሉናል ። ድካም ውስጥ ሲሆኑ ፣ ፀሎት ፣ ቃል ማጥናት ሲከብዳቸው እንድንበረታ ፀልዩልን እያሉ ሸክምን ያሸክሙናል ። ሁልጊዜ ከሚያፀልዩን ፀሎት መካከል የሁለቱም እህቶች ወንጌል ሰምተው መዳን እንዲሆንላቸው ብዙ ቀናት በዚህ ሸክም አብረን ፀልየናል ። ከተወሰኑ ወራቶች በኋላ የሁለቱም እህቶች ወንጌልን ተቀበሉ ። ፀሎታችን ስለተመለስ አብረን ጌታን አመሰገን። ፀሎት ተመለሰ ብለው  በሌላ ጊዜ ሲመጡ አላቆሙም ሌላ ሸክም ይዘው ይመጡ ነበር ። እውነተኛ(Genuine) ህብረት ሸክም መከፋፈል አለው ።

ሸክም መንፈሳዊ ሀላፊነት ነው ። የጓዳ ምጥ ፣ የአደባባይ ፍሬ ነው ። ሐዋሪያው ጳውሎስ ቅዱሳን ሸክሞቹ ነበሩ ዘወትር ስለናንተ ስፀልይ ማለት ከደብዳቤው አይጠፋም (ፊል1:3-5) ። ብዙውን ጊዜ ሸክሞች ስላልተሸከምን ይሁን? ፀሎት ስራ የሆነብን ወይም የፀሎት ህይወታችን የቀዘቀዘው ?  ለክርስትያን መንፈሳዊ ሸክም ጌጡ ነው ።

@cgfsd
🔥 10
8
Пост от 21.03.2026 10:16
398
0
4
#ነፍስም_እኮ_ይርባታል
ስለበላን ብቻ አንጠግብም፤ ስላነበብን ብቻ አንጽፍም ፤ ስለተዘጋጀን ብቻ አንሰብክም።  መድረክ ባገኘበት ያገኘውን ነገር እያላዘነ እንደሚደሰኩር ፓለቲከኛ አናስተምርም።  የእግዚአብሔር ክብር ባልተገኘበት ቦታ ምንም አላገኘንም።  ክብሩ ርቦናል ፤ መገኘቱ ናፍቆናል።  መታደሳችን ያጓጓናል ፤ #ነፍስም_እኮ_ይርባታል። 

ሰለሞን አበበ [ የተቆረሱ ነፍሶች ፤ ተቀብለን ለማቀበል ]
19
🔥 8
😢 2
Пост от 20.03.2026 12:59
413
0
0
(ችግረኛ የለም !)


ከመካከላቸውም አንድ ችግረኛ አልነበረም፤ ምክንያቱም መሬትም ሆነ ቤት የነበራቸውን ሁሉ እየሸጡ ዋጋውን አምጥተው፣  በሐዋርያት እግር ሥር በማስቀመጥ ለእያንዳንዱ በሚያስፈልገው መጠን ያካፍሉት ነበር።
ሐዋርያት ሥራ 4:34-35


የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ናት ። መንፈስ ቅዱስ በባለሃምሳ ቀን ከወረደ በኋላ የመጀመሪያ የምናገኘው የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ነው ። በኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን በ12 ሐዋሪያት የምትመራ ከፍተኛ በሚድኑ ሰዎች የሚጨመርባት ፣ በተአምራት ፣ በትጋት በመማር የደመቀ ህብረት ነበረች ። የሚድኑ ሰዎች በእየ ጊዜው እየጨመረ ሲመጣ ከተስተዋነው ነገር መካከል አንዱ የሚጨመሩት አማኞች ንብረታቸው እየሸጡ በሐዋሪያት እግር ስር እያስቀመጡ በአንድነት ይኖራሉ ።

የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ውስጥ መፀሃፍ ቅዱስ እንደሚነግረን አንድ ችግረኛ የለም ይለናል ። የተቸገረ ችግር የማይታይባት ህብረት ናት ። በዚች ቤተክርስቲያን ውስጥ ችግረኛ የሌለው ችግር ስሌለ ሳይሆን ወይንም ችግረኛ ገፍተው አስወጥተው ሳይሆን አሊያም የሀብታሞች ብቻ ስብስብ ስለሆነም አይደለም ። በዚህ ምድር የተቸገረ በኢኮኖሚ(ደሀ) ሊኖር እንደሚችል ከመፀሃፍ ቅዱሳችን እንረዳለን ። ኢየሱስን ይሁዳ ሽቶውን 300 ዲናር ተሽጦ ለድሆች ይሰጥ ሲለው  የኢየሱስ መልስ " ድሆች ሁልጊዜ በመካከላችሁ ይኖራሉ " ነበር (ዩሀ12) ። ድሃ በዚህ ምድር በእኛ መካከል መኖሩ የዚህ አለም እውነት ነው ።

ታዲያ ለምን በኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ችግረኛ ላይኖር ቻለ ?  መልሱ ግልፅ ነው ተካፍለው ስለሚኖሩ ነው ። ድሆችን በመካከላችሁ ይኖራሉ ያለው ጌታ በኢየሩሳሌም በመካከላቸው ችግረኛ እንዳይኖር ያደረጋቸው ተካፍሎ የመኖር ባህላቸው ነው ። በሐዋሪያት እግር ስር ያላቸውን ሽጠው ያስቀምጡ ነበር ፤ እያንዳንዱ እንደሚያስፈልጋቸው ይጠቀሙ ነበር ። ሚስጥሩ ተካፍሎ መኖር ነው ። አሁን በመካከላችን ስንት ሰው ተቸግሮ ይሁን ? በመካከላችን የተቸገረ እንዳይኖር ተካፍለን መኖር ነው ። ያለን ሽጠን ቤተክርስቲያን ማምጣት በዚህ ዘመን አይጠበቅብንም ፤ ካለን ትንሿን አጠገባችን ካለው ጋር መጋራት መፍትሔ ይሆናል ።

@cgfsd
9
🥰 2
Смотреть все посты