Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
1.0K
334
3
0
7.3K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 437
Сегодня
+2
Просмотров на пост
Всего
351
ER
Общий
21.14%
Суточный
13.1%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 1 040 постов
Смотреть все посты
Пост от 27.03.2026 11:31
130
0
2
(መገለጡን መከተል)


መፀሃፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ከሚያሳስበን ነገሮች መሃል እግዚአብሔርን መፈለግ ዋነኛ የመፈጠራችንና የመዳናችን አላማ እንደሆነ ነው ። እግዚአብሔር ለመፈለግ ስናስብ በአዲስም ሆነ ብሉይ ኪዳን የተሻለ መንገድ እግዚአብሔር በተገለጠበት መንገድ እሱን መፈለግ ነው ። እግዚአብሔር መፈለግ ውል እንደሌለው ወይም  ወዳገኝበት አቅጣጫ ሁሉ እግዚአብሔርን አንፈልግም ምክኒያቱም እግዚአብሔርን ለመፈለግ ትክክለኛው መንገድ ራሱ እግዚአብሔር ነው ። እግዚአብሔር ከእኛ ረቂቅ በመሆኑ ራሱን በገለጠልን መንገድ ብቻ ነው የምናውቀው።

እግዚአብሔር በህዝቡ መሃል እንዲመለክ ፣ እንዲፈለግ ያደረገው ራሱን በመግለጥ ነው ። አብርሃምን እግዚአብሔር" እኔ ኤልሻዳይ ነኝ"በማለት ራሱን ገለጠለት (ዘፍ 17:1) አብርሃም የእግዚአብሔር አልሻዳይነት ማዕከል(center) ያደረገ ኑሮን ኖረ ። እግዚአብሔር ለሙሴ እኔ " የአባቶችህ የአብርሃም የይስሃቅ አምላክ እኔ ነኝ"  በማለት ራሱን ገለጠለት (ዘፀ3:6)።ሙሴም በተገለጠ መንገድ እግዚአብሔርን ፈለገው ።

እግዚአብሔር በብዙ ጎዳና ተናግር የነበረ ቢሆንም በተሻለ መንገድ በላቀ መንገድ በልጁ ተናገረ(ዕብ1:3) ።  እግዚአብሔር በልጁ  የተናገረው የሚገኘውን መዳንና ራሱን ማን  እንደሆነ ማንነቱን ነው ። የኢየሱስ ሰው መሆን አላማ ውስጥ ዋነኛው እግዚአብሔር በትክክል መግለጥ ነው ። እግዚአብሔር ራሱን በልጁ በኩል ገለጠልን ። እግዚአብሔር በተገለጠን መንገድ መፈለግ ትክክለኛው መፈለግ ነው ። እግዚአብሔር መፈለግ ስንል እግዚአብሔር ለማምለክ፣ ከእግዚአብሔር ህብረት ለማረግ ፣ እግዚአብሔር ለመምሰል ነው ። ለዚህ መፍትሔው ራሱን በተገለጠልን ደጋግሞ መፈለግ ነው ። መገለጡን መከተል መፈለጉን ትክክል ያረገዋል ።


@cgfsd
8
Пост от 26.03.2026 10:41
0
0
0
Пост от 26.03.2026 10:26
351
0
3
(ጵራቅሊጦስ በሰማይ ጵራቅሊጦስ በምድር)



በመፀሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ ጵራቅሊጦስ በሚለው ቃል ኢየሱስና መንፈስ ቅዱስ ተጠርተዋል ። መንፈስ ቅዱስ ከተጠራባቸው ስሞች መካከል አንዱ አፅናናኝ ወይም ጵራቅሊጦስ የሚል ነው (ዩሀ14:15-16) ። ጵራቅሊጦስ ማለት አፅናኝ የሚልም ትርጉም አለው ። መንፈስ ቅዱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ እንደተጠራ ሁሉ ጌታ ኢየሱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ ተጠርቷል (1ዩሀ 2:1) ። ኢየሱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ የተጠራው ጠበቃ በሚል ቃል ነው ። ጵራቅሊጦስ ትርጉሙ ውስጥ አፅናናኝ እንዳለ ሁሉም ሌላኛው ትርጉሙ ጠበቃ የሚል ፍቺ አለው ። ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ አፅናኝ ጵራቅሊጦስ ፤ ኢየሱስ ደግሞ ጠበቃ ጵራቅሊጦስ ተብለው ተጠርተዋል ።

ኢየሱስ በሰማይ ስለእኛ ያለ አጋዥ ጠበቃ ወገን ጵራቅሊጦስ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በእኛ ውስጥ ያለ የሚረዳን ረዳት አፅናኝ ጵራቅሊጦስ ፤ ይሔም በመሆኑ እጅግ አስደናቂ እርዳታ አለን ። የክርስትና ጉዞአችን በእግዚአብሔር ያለልክ የሚደገፍ በፀጋው የተትረፈረፈ እግዚአብሔር እኛ ጋር መሆኑን በብዙ መንገድ የታየበት ግሩም ጉዞ ነው ። በሰማይ ጠበቃ ጵራቅሊጦስ ኢየሱስ ስለ እኛ እየታየ በሊቀካህናዊ አገልግሎቱ እየደገፈን ያግዘናል (ዕብ 4:16) ። በዚህ ምድር ደግሞ አፅናኙ ጵራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ጥንካሬን ፣ ማፅናናት እያበዛ ፣ ድካማችን እያገዘ ይደግፈናል (ሮሜ8:26) ። እግዚአብሔር ደጋግፎናል ! ይደግፈናልም!

ጵራቅሊጦስ👉 ( አፅናኙ መንፈስ ቅዱስ) በምድር ላይ ለቅዱሳን አለኝታ ነው ።

ጵራቅሊጦስ 👉(ጠበቃው ኢየሱስ) በሰማይ ለቅዱሳኑ አለኝታ ነው።

@cgfsd
13
🔥 4
Пост от 25.03.2026 07:29
261
0
2
(ሸክም)



ሸክም ያጎብጣል፤ ሸክም ቀና ያረጋል ። የተሸከመ ሰው ያቀረቀረው ለተሸከመው ጉዳይ ነው ። ቀናም የሚለው ሸክሙን ለማረገፍ ነው ። ክርስትና የሸክም ህይወት ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም ። የተቀበልነው ህይወት በራሱ መቃተት አለው ፣ የተቀበልነው መንፈስ በራሱ መቃተት አለው(ሮሜ8:26-27) ፣ የቅዱሳን ህብረት የሸክም መከፋፈሪያ ስፍራም ነው ።

የዘጠኛ ክፍል ተማሪ እያለን አምስት የምንሆን ልጆች ሰኞ ማታ ማታ የኤፌሶን መፀሃፍ ለአንድ አመት የሚጠጋ ጊዜ እናጠና ነበር ። ሰፈራችን የተራራቀና ከትምህርት በኋላ ማታ ስለነበር የሚደረገው ፤ በቤተክርስቲያናችን ያለች የተወደደች እናት ቤት አስፈቅደን እሷ ቤት ነበር የምናደርገው። ከጥናት በኋላ በተደጋጋሚ በምናጠናው መካከል እጅግ በጣም ለሚሰማቸው ግልፅ የሆኑ ሁለት ወንድሞች ነበሩ ። በተደጋጋሚ የፀሎት ርዕስ ሸክም ያጋሩናል ። በዚህ ሀሳብ እንፀልይ ፣ ለጎረቤታችን እንደዚህ እንፀልይ ይሉንና ሸክም ያካፍሉናል ። ድካም ውስጥ ሲሆኑ ፣ ፀሎት ፣ ቃል ማጥናት ሲከብዳቸው እንድንበረታ ፀልዩልን እያሉ ሸክምን ያሸክሙናል ። ሁልጊዜ ከሚያፀልዩን ፀሎት መካከል የሁለቱም እህቶች ወንጌል ሰምተው መዳን እንዲሆንላቸው ብዙ ቀናት በዚህ ሸክም አብረን ፀልየናል ። ከተወሰኑ ወራቶች በኋላ የሁለቱም እህቶች ወንጌልን ተቀበሉ ። ፀሎታችን ስለተመለስ አብረን ጌታን አመሰገን። ፀሎት ተመለሰ ብለው  በሌላ ጊዜ ሲመጡ አላቆሙም ሌላ ሸክም ይዘው ይመጡ ነበር ። እውነተኛ(Genuine) ህብረት ሸክም መከፋፈል አለው ።

ሸክም መንፈሳዊ ሀላፊነት ነው ። የጓዳ ምጥ ፣ የአደባባይ ፍሬ ነው ። ሐዋሪያው ጳውሎስ ቅዱሳን ሸክሞቹ ነበሩ ዘወትር ስለናንተ ስፀልይ ማለት ከደብዳቤው አይጠፋም (ፊል1:3-5) ። ብዙውን ጊዜ ሸክሞች ስላልተሸከምን ይሁን? ፀሎት ስራ የሆነብን ወይም የፀሎት ህይወታችን የቀዘቀዘው ?  ለክርስትያን መንፈሳዊ ሸክም ጌጡ ነው ።

@cgfsd
🔥 10
8
Пост от 21.03.2026 10:16
398
0
4
#ነፍስም_እኮ_ይርባታል
ስለበላን ብቻ አንጠግብም፤ ስላነበብን ብቻ አንጽፍም ፤ ስለተዘጋጀን ብቻ አንሰብክም።  መድረክ ባገኘበት ያገኘውን ነገር እያላዘነ እንደሚደሰኩር ፓለቲከኛ አናስተምርም።  የእግዚአብሔር ክብር ባልተገኘበት ቦታ ምንም አላገኘንም።  ክብሩ ርቦናል ፤ መገኘቱ ናፍቆናል።  መታደሳችን ያጓጓናል ፤ #ነፍስም_እኮ_ይርባታል። 

ሰለሞን አበበ [ የተቆረሱ ነፍሶች ፤ ተቀብለን ለማቀበል ]
19
🔥 8
😢 2
Пост от 20.03.2026 12:59
413
0
0
(ችግረኛ የለም !)


ከመካከላቸውም አንድ ችግረኛ አልነበረም፤ ምክንያቱም መሬትም ሆነ ቤት የነበራቸውን ሁሉ እየሸጡ ዋጋውን አምጥተው፣  በሐዋርያት እግር ሥር በማስቀመጥ ለእያንዳንዱ በሚያስፈልገው መጠን ያካፍሉት ነበር።
ሐዋርያት ሥራ 4:34-35


የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ናት ። መንፈስ ቅዱስ በባለሃምሳ ቀን ከወረደ በኋላ የመጀመሪያ የምናገኘው የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ነው ። በኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን በ12 ሐዋሪያት የምትመራ ከፍተኛ በሚድኑ ሰዎች የሚጨመርባት ፣ በተአምራት ፣ በትጋት በመማር የደመቀ ህብረት ነበረች ። የሚድኑ ሰዎች በእየ ጊዜው እየጨመረ ሲመጣ ከተስተዋነው ነገር መካከል አንዱ የሚጨመሩት አማኞች ንብረታቸው እየሸጡ በሐዋሪያት እግር ስር እያስቀመጡ በአንድነት ይኖራሉ ።

የኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ውስጥ መፀሃፍ ቅዱስ እንደሚነግረን አንድ ችግረኛ የለም ይለናል ። የተቸገረ ችግር የማይታይባት ህብረት ናት ። በዚች ቤተክርስቲያን ውስጥ ችግረኛ የሌለው ችግር ስሌለ ሳይሆን ወይንም ችግረኛ ገፍተው አስወጥተው ሳይሆን አሊያም የሀብታሞች ብቻ ስብስብ ስለሆነም አይደለም ። በዚህ ምድር የተቸገረ በኢኮኖሚ(ደሀ) ሊኖር እንደሚችል ከመፀሃፍ ቅዱሳችን እንረዳለን ። ኢየሱስን ይሁዳ ሽቶውን 300 ዲናር ተሽጦ ለድሆች ይሰጥ ሲለው  የኢየሱስ መልስ " ድሆች ሁልጊዜ በመካከላችሁ ይኖራሉ " ነበር (ዩሀ12) ። ድሃ በዚህ ምድር በእኛ መካከል መኖሩ የዚህ አለም እውነት ነው ።

ታዲያ ለምን በኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ችግረኛ ላይኖር ቻለ ?  መልሱ ግልፅ ነው ተካፍለው ስለሚኖሩ ነው ። ድሆችን በመካከላችሁ ይኖራሉ ያለው ጌታ በኢየሩሳሌም በመካከላቸው ችግረኛ እንዳይኖር ያደረጋቸው ተካፍሎ የመኖር ባህላቸው ነው ። በሐዋሪያት እግር ስር ያላቸውን ሽጠው ያስቀምጡ ነበር ፤ እያንዳንዱ እንደሚያስፈልጋቸው ይጠቀሙ ነበር ። ሚስጥሩ ተካፍሎ መኖር ነው ። አሁን በመካከላችን ስንት ሰው ተቸግሮ ይሁን ? በመካከላችን የተቸገረ እንዳይኖር ተካፍለን መኖር ነው ። ያለን ሽጠን ቤተክርስቲያን ማምጣት በዚህ ዘመን አይጠበቅብንም ፤ ካለን ትንሿን አጠገባችን ካለው ጋር መጋራት መፍትሔ ይሆናል ።

@cgfsd
9
🥰 2
Пост от 18.03.2026 11:09
334
0
1
(የክርስቶስ እርገት)


በክርስትና ውስጥ ክርስቶስን በተመለከተ የክርስቶስ ውልደት ፣ ሞት ፣ ትንሳኤና ዳግም መምጣት አስፈለጊ እንደሆነ ዋና የትኩረት አቅጣጫ እንደሆነበት መጠን የክርስቶስ እርገት እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ ነው ።

               እንዲህም አሏቸው፤ “እናንት የገሊላ ሰዎች ሆይ፤ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ እዚህ የቆማችሁት ለምንድን ነው? ይህ ከእናንተ ዘንድ ወደ ሰማይ ሲያርግ ያያችሁት ኢየሱስ፣ ልክ ወደ ሰማይ ሲወጣ እንዳያችሁት በዚሁ ሁኔታ ይመለሳል።”
ሐዋርያት ሥራ 1:11

   የክርስቶስ ማረግ በረከቶች

1, በክርስቶስ የተሰራው ስራ (ሞቱና ትንሳኤው) እውነት መሆኑን ያረጋግጥልናል።

2, የክርስቶስ ምልጃ ሊቀ ካህናዊ አገልግሎት እንደሚቀጥል ዋስትና ይሆነናል ።

3, ዳግም ተመልሶ እንደሚመጣ የማይነቃነቅ ፅኑ ተስፋ ይሆንልናል ።

4, በስጋ በማረጉ አሁንም የሰው ዘመድ ወገን ለሰው ተቆርቆሪ እንደሆነ ገብቶን እምነትና መደገፍን ይጨምርናል ።

5, በአዲሱ የትንሳኤ አካል በመነሳቱና በማረጉ በአዲሱ የትንሳኤ አካል በትንሳኤ ቀን እንደምንነሳ ማረጋገጫችን ይሆንልናል ።

6, እኔ ብሄድ ይሻላችኋል ያለው እሱ በመሆኑ ፤ በክርስቶስ እርገት ምክኒያት መንፈስ ቅዱስ እኛ መካከል እያፅናናን እንዲሰራ አድርጎልናል ።

7, ክርስቶስ በማረጉና በመክበሩ ወደ ፀጋው ዙፋን በድፍረት የመግባት ነፃነት ተቀናጅተናል ።

የክርስቶስ እርገት የክርስትና ውበታችን እጅግ ወሳኝ ምዕራፍ ነው ። እንደ ሞቱና ትንሳኤው እርገቱም ዋና ነው ።
🔥 5
2
Смотреть все посты