Каталог каналов Каналы в закладках Новинка Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
1.0K
334
3
0
7.3K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 442
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
376
ER
Общий
18.34%
Суточный
10.3%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 1 044 постов
Смотреть все посты
Пост от 03.04.2026 09:27
120
0
2
(ቤተመቅደስ እና ቤተመንግሥት )


እግዚአብሔር አምላክ (ያህዌ ኤሎሂም) ሰውን ወስዶ እንዲያለማትና እየተንከባከበ እንዲጠብቃት በዔድን የአትክልት ስፍራ አስቀመጠው።
ዘፍጥረት 2:15

በእግዚአብሔር መልክና አምሳል ሰው ተፈጠረ ። ሰው ከተፈጠረ በኋላ እግዚአብሔር ሰውን ምድርን ፣ ይጠብቃት ፣ ይንከባከባትና እንዲያለማት በኤደን ገነት ጌታ  አስቀመጠው ። አዳም በእግዚአብሔር መልክ መፈጠሩ ትልቅ አስደናቂ ጉዳይ ሲሆን ከተፈጠረ በኋላም በኤደን ገነት ትልቅ ሃላፊነት ተሰጠው ። የመንከባከብ ፣ የመጠበቅ ሃላፊነት ተሰጥቶት በአትክልት ቦታው ተቀመጠ ። ኤደን ገነትን መንከባከብና መጠበቅ ለአዳም ከእግዚአብሔር የተሰጠው አደራ ነው ። መጠበቅና መንከባከብ የሚለው ቃልና ሃሳብ ከብሉይ ኪዳኑ የቤተ መቅደ ስርአት እንቅስቃሴ በማሰብ ከሚውል ቃል ጋር ተመሳሳይነት አለው ። ካህኑ በቤተመቅደስ የሚያደርገውን ተግባር ይመስላል አዳም በኤደን ገነት እንዲንከባከብ የተሰጠው ። ስለዚህ ኤዴን ገነት ለአዳም ከተሰጠው ካህናዊ አገልግሎትና በስፍራው ካለው የእግዚአብሔር መገኘት የተነሳ ኤደን ገነት ቤተመቅደስ ነው ማለት ይቻላል ። መቅደስ ነው ስንል እግዚአብሔር መገኘቱ አለ ፤  አዳም ደግሞ ካህን ሁኖ ይንከባከባል ።

    እግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ “ብዙ ተባዙ፤ ምድርን ሙሏት፤ ግዟትም፤ የባሕርን ዓሦች፣ የሰማይን ወፎች፣ እንዲሁም በምድር ላይ
የሚንቀሳቀሱትን ሕያዋን ፍጡራንን ሁሉ ግዟቸው” ብሎ ባረካቸው።
ዘፍጥረት 1:28

ኤደን ገነት በሌላ ጎኑ ቤተመንግስትን ይወክላል ። ቤተመንግስት የንጉስ መኖሪያ ነው ። አዳም የንግስና ድርሻ በፍጥረት መሃል  ሲሰጠው ማየት ይቻላል ። " በምድር
ላይ የሚንቀሳቀሱትን ፣ ሕያዋን ፍጡራንን ሁሉ ግዟቸው የሚል ሃላፊነት ለሰው ተሰጥቷል ። መግዛት የንጉስ መገለጫ ነው ። እዚህ ጋር ልብ ማለት ያለብን የአዳም ንግስና ወይም ገዢነት የባህሪ ወይም የእግዚአብሔር አይነት የመለኮት ገዢነት አይደለም ። የፀጋ ገዢነት ነው ። ይሔ ደግሞ የሚያሳየው የአደራ ገዢነት በአደራ የማስተዳደር የእግዚአብሔር ገዢነት ለማሳየት በፀጋው የሆነ የመንከባከብ ፣ የአደራ ገዢነት የተሰጠው በሌላ አገላለፅ የእግዚአብሔር ወኪል የሆነበት እንደማለት ነው። ይሔም የፀጋ ገዢነት ይባላል ። ምሳሌ የእኛ ልጅነት ኢየሱስ ልጅ እንደተባለው አይነት የመለኮት ወይንም የባህሪ ልጅነት ሳይሆን የፀጋ ነው ። ልጅ ያልነበረውን በምህረቱ ፣ በፍቅሩ የተገኘ እድል ነው ።  አዳም ገዢ ነህ ሲባል ብዙ ተአምር የለውም የፀጋ ገዚነት ባላደራነት ነው ። በዚህ መልኩ አዳም ንጉስ ይመስላል ። ኤደን ገነት እንደ ቤተመቅደስም እንደ ቤተመንግስት መመልከት ይቻላል ።

ይህም የሚያስረዳን እግዚአብሔር ሰው በቤተመቅደሱ  በመገኘቱ እንዲኖር ካህን እንዳደረገው ፣ የእግዚአብሔር ወኪል በመሆን እግዚአብሔርን እንዲያስተዋውቅ ፍጥረት እየመራ የእግዚአብሔርን መልክ የሚያሳይ መሪ እንዲሆን ኤደን ገነትን ቤተመንግስት አርጎለት ነበር። አዳም ንጉስም ካህን ነበር ።  ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው (መዝ8)  አቤት እግዚአብሔር ግን እንዴት ነው? ሰውን የወደደው ፤ ሰውን ያሰበው ።  የእግዚአብሔር ፍጥረት ግሩም ነበር ! የሰው ውድቀት አስከፊ የሚሆነው ለዚህም ምክኒያት ነው ። እግዚአብሔር ግን ዕቅዱና ስራው ዕፁብ ድንቅ ነው ።


@cgfsd
8
🔥 2
🥰 2
Пост от 02.04.2026 08:35
201
0
3
በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ የቤተክርስቲያን አባት(church fathers) ተብለው ከሚጠሩት መካከል ፖሊካርፕ ይጠቀሳል ። ፖሊካርፕ በቤተክርስቲያን ታሪክ ከሐዋሪያው ዩሀንስ ስር ቁጭ ብሎ የተማረ ደቀመዝሙር እንደሆነ ይታመናል ። ፖሊካርፕ የእድሜው መጨረሻ ላይ ወታደሮች ሊይዙት ወደ እርሱ ሲመጡ ወታደሮች በደስታ ተቀብሎ የሚበሉት ምግብ አቅርቦ አበላቸው ። የተወሰነ ጊዜ ብቻ እንዲሰጡት በትህትና ጠይቆ ለ2 ሰአታት ያክል ስለሚያቃቸው ሰዎች ሁሉ ፣ አለም ላይ ስላለችው ቤተክርስቲያን ሲፀልይ ቆየ ፤ ከዛም በ86 አመቱ ለመሰዋት ተዘጋጅቶ ከወታደሮቹ ጋር ሄደ ።

በግል የፀሎት ጊዜያችን ሌሎች ሰዎች የፀሎት ርዕስ ሊሆኑን እንደሚገባ ከፖሊካርፕ መማር እንችላለን ፤ ፖሊካርፕ የህይወቱ የመጨረሻ ሰአታትን ለሌሎች በመቃተት ያሳለፈው ። ለሌሎች መንበርከክ ሌሎች የመውደድ ምልክት ነው ።  እዮብ  ያሳለፈው መከራ ያሳዝናል ስላጣው ነገር ከመፀለይ ይልቅ በምጡ ጊዜ ከልቡ ለወዳጆቹ ፀለየላቸው ።

    ኢዮብ ለወዳጆቹ ከጸለየ በኋላ፣ እግዚአብሔር እንደ ገና አበለጸገው፤ ቀድሞ በነበረው ፈንታ ዕጥፍ አድርጎ ሰጠው።
ኢዮብ 42:10

@cgfsd
👍 5
3
🔥 2
Пост от 01.04.2026 08:04
225
0
3
(ሙታን ትንሳኤ)


ሙታን ትንሳኤ ከሞት በኋላ ያለውን ትንሳኤ የሚያመለክት መንፈሳዊ ሀሳብ ነው ። ሞት እዚህ ምድር እንዳለ እውን ነው ። እንደዚሁ ደግሞ ትንሳኤ እንዳለ መፀሃፍ ቅዱሳችን በተደጋጋሚ ያረጋግጥልናል ። ሐዋሪያው ጳውሎስ ሙታን ትንሳኤ የለም ከሞት በኋላ ትንሳኤ አይኖርም ብለው የሚያስቡትን ሰዎች ምነኛ ምስኪኖች ናቸው ይላል(1ቆሮ15) ። ኢየሱስ በነበረበት ዘመን ሰዱቃዊያን የተባሉት ቡድኖች ከሞት በኋላ ትንሳኤ የለም በማለት ያምናሉ ። ሰዱቃዊያን ኢየሱስን ስለዚህ ጉዳይ ጠይቀውት ጌታ ሙታን ትንሳኤ ስለመኖሩ በአጭሩ እንደዚህ አስረዳቸው ።

" ስለ ሙታን ትንሣኤ ግን እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ የተናገራችሁን አላነበባችሁምን? ‘እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ።’ እግዚአብሔር የሕያዋን እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም።"
ማቴዎስ 22:31-32

በኢየሱስ አገላለፅ ሙታን ትንሳኤ አለ ። ለዚህ ማሳያ እግዚአብሔር ራሱን በብሉይ ኪዳን ሲያስተዋውቅ እኔ የአብርሃም ፣ የይስሃቅ ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ በማለት ነው ። እነ አብርሃም ሙተዋል ግን ተስፋ የሰጣቸውና የሚፈፅመው እሱ ስለሆነ የእነሱ አምላክ ነኝ ሲል እነርሱን እንደሚያስነሳ የሰጠውን ተስፋ እንደሚፈፅም ሙተው እንደማይቀሩም እየተናገረ ነው ፤ ምክኒያቱ ደግሞ እግዚአብሔር የህያዋን አምላክ ስለሆነ ነው ። የእነ አብርሃም አምላክ ነኝ የሚለው የእግዚአብሔር ራሱን የገለጠበት መገለጫ ለሙታን ትንሳኤ የሚሰጥ አምላክ ነኝ እንደማለት ነው ። ሙታን ትንሳኤ የተስፋችን ማዕከልም ነው ። በክርስቶስ ዳግም መምጣት ውብ የሚያረገው ሙታን ትንሳኤ ነው ። የጥንት ቤተክርስቲያን የጉባኤያት የእምነት መግለጫ ላይ " በሙታን ትንሳኤ እናምናለን " የሚል የእምነት ማፅኛ አለ ። ሙታን ትንሳኤ ስለመኖሩ እግዚአብሔር ራሱ የአብርሃም ፣ የይስሃቅ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ ብሎ አረጋግጦልናል ።

@cgfsd
8
🥰 3
Пост от 28.03.2026 19:11
372
0
3
...ሰው አምላክ ለመሆን በሚጣጣርበት አለም አምላክ ሰው ሆነ !
19
🥰 17
Пост от 27.03.2026 11:31
411
0
4
(መገለጡን መከተል)


መፀሃፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ከሚያሳስበን ነገሮች መሃል እግዚአብሔርን መፈለግ ዋነኛ የመፈጠራችንና የመዳናችን አላማ እንደሆነ ነው ። እግዚአብሔር ለመፈለግ ስናስብ በአዲስም ሆነ ብሉይ ኪዳን የተሻለ መንገድ እግዚአብሔር በተገለጠበት መንገድ እሱን መፈለግ ነው ። እግዚአብሔር መፈለግ ውል እንደሌለው ወይም  ወዳገኝበት አቅጣጫ ሁሉ እግዚአብሔርን አንፈልግም ምክኒያቱም እግዚአብሔርን ለመፈለግ ትክክለኛው መንገድ ራሱ እግዚአብሔር ነው ። እግዚአብሔር ከእኛ ረቂቅ በመሆኑ ራሱን በገለጠልን መንገድ ብቻ ነው የምናውቀው።

እግዚአብሔር በህዝቡ መሃል እንዲመለክ ፣ እንዲፈለግ ያደረገው ራሱን በመግለጥ ነው ። አብርሃምን እግዚአብሔር" እኔ ኤልሻዳይ ነኝ"በማለት ራሱን ገለጠለት (ዘፍ 17:1) አብርሃም የእግዚአብሔር አልሻዳይነት ማዕከል(center) ያደረገ ኑሮን ኖረ ። እግዚአብሔር ለሙሴ እኔ " የአባቶችህ የአብርሃም የይስሃቅ አምላክ እኔ ነኝ"  በማለት ራሱን ገለጠለት (ዘፀ3:6)።ሙሴም በተገለጠ መንገድ እግዚአብሔርን ፈለገው ።

እግዚአብሔር በብዙ ጎዳና ተናግር የነበረ ቢሆንም በተሻለ መንገድ በላቀ መንገድ በልጁ ተናገረ(ዕብ1:3) ።  እግዚአብሔር በልጁ  የተናገረው የሚገኘውን መዳንና ራሱን ማን  እንደሆነ ማንነቱን ነው ። የኢየሱስ ሰው መሆን አላማ ውስጥ ዋነኛው እግዚአብሔር በትክክል መግለጥ ነው ። እግዚአብሔር ራሱን በልጁ በኩል ገለጠልን ። እግዚአብሔር በተገለጠን መንገድ መፈለግ ትክክለኛው መፈለግ ነው ። እግዚአብሔር መፈለግ ስንል እግዚአብሔር ለማምለክ፣ ከእግዚአብሔር ህብረት ለማረግ ፣ እግዚአብሔር ለመምሰል ነው ። ለዚህ መፍትሔው ራሱን በተገለጠልን ደጋግሞ መፈለግ ነው ። መገለጡን መከተል መፈለጉን ትክክል ያረገዋል ።


@cgfsd
13
Пост от 26.03.2026 10:41
0
0
0
Пост от 26.03.2026 10:26
696
0
3
(ጵራቅሊጦስ በሰማይ ጵራቅሊጦስ በምድር)



በመፀሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ ጵራቅሊጦስ በሚለው ቃል ኢየሱስና መንፈስ ቅዱስ ተጠርተዋል ። መንፈስ ቅዱስ ከተጠራባቸው ስሞች መካከል አንዱ አፅናናኝ ወይም ጵራቅሊጦስ የሚል ነው (ዩሀ14:15-16) ። ጵራቅሊጦስ ማለት አፅናኝ የሚልም ትርጉም አለው ። መንፈስ ቅዱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ እንደተጠራ ሁሉ ጌታ ኢየሱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ ተጠርቷል (1ዩሀ 2:1) ። ኢየሱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ የተጠራው ጠበቃ በሚል ቃል ነው ። ጵራቅሊጦስ ትርጉሙ ውስጥ አፅናናኝ እንዳለ ሁሉም ሌላኛው ትርጉሙ ጠበቃ የሚል ፍቺ አለው ። ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ አፅናኝ ጵራቅሊጦስ ፤ ኢየሱስ ደግሞ ጠበቃ ጵራቅሊጦስ ተብለው ተጠርተዋል ።

ኢየሱስ በሰማይ ስለእኛ ያለ አጋዥ ጠበቃ ወገን ጵራቅሊጦስ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በእኛ ውስጥ ያለ የሚረዳን ረዳት አፅናኝ ጵራቅሊጦስ ፤ ይሔም በመሆኑ እጅግ አስደናቂ እርዳታ አለን ። የክርስትና ጉዞአችን በእግዚአብሔር ያለልክ የሚደገፍ በፀጋው የተትረፈረፈ እግዚአብሔር እኛ ጋር መሆኑን በብዙ መንገድ የታየበት ግሩም ጉዞ ነው ። በሰማይ ጠበቃ ጵራቅሊጦስ ኢየሱስ ስለ እኛ እየታየ በሊቀካህናዊ አገልግሎቱ እየደገፈን ያግዘናል (ዕብ 4:16) ። በዚህ ምድር ደግሞ አፅናኙ ጵራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ጥንካሬን ፣ ማፅናናት እያበዛ ፣ ድካማችን እያገዘ ይደግፈናል (ሮሜ8:26) ። እግዚአብሔር ደጋግፎናል ! ይደግፈናልም!

ጵራቅሊጦስ👉 ( አፅናኙ መንፈስ ቅዱስ) በምድር ላይ ለቅዱሳን አለኝታ ነው ።

ጵራቅሊጦስ 👉(ጠበቃው ኢየሱስ) በሰማይ ለቅዱሳኑ አለኝታ ነው።

@cgfsd
15
🔥 4
Смотреть все посты