(ሁላችንም ይመለከታል!)
ዶክተር ኖርማል ኤል ጋይዝለር አጠር ባለው (Essential doctrine Made easy ) በተሰኘው ስራው ለድነት አስፈላጊ የሆኑ ቀዳሚ አስተምሮዎችን ይዘረዝራል ። የክርስትና አስተምሮ ቀዳሚ(primary doctrine) ሊሆኑ የሚገቡ አስተምሮዎች አሉ ። እነዚህ አስተምሮዎች ማስቀደም ትኩረት መስጠት አስፈላጊ ነው ለድነት ጠቃሚ ናቸውና ። ዶክተር ጋይዝለር መሰረታዊ ያላቸውን 14 (essential doctrine) ዘርዝር አስቀምጧል ። እነዚህ 14 መሰረታዊ አስተምሮ ለድነት አስፈላጊ ጠቃሚ መሆናቸውን ያትታል ። አስተምሮዎቹን ያወጣው ከሐዋሪያት የእምነት መግለጫ ነው ። የሐዋሪያት የእምነት መግለጫ (creed) እንደ ዶክተር ጋይዝለር አገላለፅ እንደሚለው መፀሃፍ ቅዱስን በአጭሩ ( creed are short summaries of what the bible teaches) በዚህ መንገድ ያስረዳናል ። የሐዋሪያት የእምነት መግለጫ መፀሃፍ ቅዱስን በአጭሩ ያሳዩናል ። ይሔ ማለት የእምነት መግለጫው (creed) በመፀሃፍ ቅዱስ መሰረት ላይ የቆመ ፣ የተመዘነ በመፀሃፍ ቅዱስ ስልጣን ስር ያለ ነው ። creed ላይ የመጣ አዲስ ትምህርት የለም የመፀሃፍ ቅዱስ ትምህርት እውቅና ሰጡ አስተጋቡ እንጂ ። ስለዚህ ዶክተር ኖርማል መሰረታዊ ቀዳሚ ሁሉም አማኝ በቀላሉና ግልፅ በሆነ መንገድ ለድነት ወሳኝ የሆነው አስተምሮ የሃዋሪያት እምነት መግለጫ ከጉባኤያት የወጡትን ትምህርቶች ይጠቁማል ። እነዚህም አስራ አራቱም :-
1, የእግዚአብሔር አንድነት
2, የእግዚአብሔር ሶስነትና አንድነት
3, የሰው ውድቀት
4, የክርስቶስ በድንግል መወለድ
5, የክርስቶስ ሀጢያት አልባነት
6, የክርስቶስ አምላክነት
7, የክርስቶስ ሰውነት
8, የእግዚአብሔር ፀጋ አስፈላጊነት
9, የእምነት አስፈላጊነት
10, የክርስቶስ ሞት
11, የክርስቶስ የስጋ ትንሳኤ
12, የክርስቶስ በስጋ ማረግ
13, የክርስቶስ ምልጃ
14, የክርስቶስ ዳግም መምጣት
መሰረታዊ አስተምሮዎችን የማወቅና የማሳወቅ ክርስቲያዊ ሃላፊነት አለብን ። ዶክተር ጋይዝለር ለሁሉም ግልፅ ተደራሽ እንዲሆን አስፈላጊና ለድነት ጠቃሚን አስተምሮ ከሐዋሪያት የእምነት መግለጫ አውጥቷል ። በቤተክርስቲያን ውስጥ ለሁሉም ተደራሽ በሆነ መልኩ ባልተወሳሰበ ለሁሉም ልክ በሚሆን መሰረታዊ አስተምሮን መማር አለብን ። ከመሰረታዊ አስተምሮ(basic doctrines) የተፋታ ተግባራዊ ህይወት (devotional life) ምንጩና መነሻው አያስታውቅም ። ከተግባራዊ ህይወት የተፋታ መሰረታዊ አስተምሮ አላማውን የተሳተ ነው ። ይሔ ጉዳይ ሁላችንም ይመለከተናል ። በቤተክርስቲያን ልንማር ፣ በህብረት የጥናት ወቅቶቻችን ልናጠናው ፣ በኑሮም ስርአታችን የህይወት መርህ አርገናቸው ልንኖር ያስፈልጋል ።
@cgfsd