Телеграм канал ''




457 подписчиков
73 просмотров на пост


Детальная рекламная статистика будет доступна после прохождения простой процедуры регистрации


Что это дает?
  • Детальная аналитика 3'274'253 каналов
  • Доступ к 1'077'562'008 рекламных постов
  • Поиск по 2'562'447'751 постам
  • Отдача с каждой купленной рекламы
  • Графики динамики изменения показателей канала
  • Где и как размещался канал
  • Детальная статистика по подпискам и отпискам
Telemetr.me

Telemetr.me Подписаться

Аналитика телеграм-каналов - обновления инструмента, новости рынка.

Просмотр поста #1220 от 2023-03-14 07:23:35

የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመኖር የግድ ኢየሱስን ማየት አስፈላጊ ነው ምክኒያቱም የእግዚአብሔር ፈቃድ በሙላት የኖረው ኢየሱስ ብቻ ነው ።

(ኢየሱስን በማየት በእግዚአብሔር ፈቃድ መመላለስ)

@cgfsd
@ownkin
👍 16


Последние посты канала:

ውዳችን ኢየሱስ ወከባ አያስቆመውም .... ለአየር መተንፈስ በሚከብደው  በግፊያ መሀል ግን ለነካው ይቆማል ።
             
      ምስክር : የደሟ ምንጭ የቆመላት


@ownkin
  @cgfsd
👍 10
👍 10
Видео/гифка
(የነካኝ ምስክርነት)


በክርስቲያን ቤተሰብ በማደጌ ኢየሱስን የማውቀው ልክ  በመስቀል ላይ የተሰቀለ  የሚል ብቻ እውቀት ነበር ። በኋላ ግን ከዛ ያለፈ እንደሆነ አስገራሚ ማንነት እንዳለው ስረዳ አብዝቼ አብዝቼ ኢየሱስ የሚለው ስም አንስቼ ማንነቱ አስቤ አልጠግብ አልኩ ።ስለ ኢየሱስ ሳይሆን ራሱን ኢየሱስ ማወቅ ጀመርኩ ።

ኢየሱስ አስገራሚ ማንነት አለው 😍



@ownkin
@cgfsd
👍 14
#የዘላለም ርዕስ #የማያልቅ ምዕራፍ #የማይፈፀም ታሪክ #የማይጨረስ መፀሀፍ #የእሱ መች አልቆብን ሌላ እንጀምራለን #የተሰቀለውን ስንሰብክ እንኖራለን #ዋናው ኢየሱስ ነው  #ዋናው ክርስቶስ ነው #ከሞት ለተቤዥን #በደሙ መፍሰስ #በደሙ መፍሰስ #መቼ አወጅነው እና #የእርሱን ድንቅ ስራ


🎼
@ownkin
@cgfsd
👍 12
የሰማይ ድባብ የቤዛነቱ ድባብ ነው ። ለዚህም ነው በሰማይ ታርደሃል እና እየተባለ ቅኔ የሚቀኙለት እዛም ሰማይ የቤዛነቱ ጠረን ይሸታል ፣ የቤዛነቱ መአዛ ያውዳል። ቤተክርስቲያንም የክርስቶስ የቤዛነት ድባብ ጉባኤዋን ያጥናል ፣ በመካከሏ የቤዛነቱ ደስታ ያስተጋባል፣ ቤዛነቱ ያንሰፈስፋታል፣ ቤዛነቱ ቀልቧን ይሰርቃል።


@ownkin
@cgfsd
👍 3
በመዳፍህ መሃል ያሳለፍከኝ #ጌታ ተቸንክረህ ደምተህ ሰው ያረከኝ #ጌታ የቱ ትከሻዬ ፍቅርህን ይችላል ከምገልፀው በላይ #ውለታህ ከብዶኛል ።


🎼
@ownkin
@cgfsd
👍 9
የመስቀሉን ሊሻን አርገን #የደሙን ሀብል አጥልቀን #በቀዩ ምንጣፍ ላይ በእምነት #ተራምደን ገብተናል ገነት #ድል ነስቶ ድል አልብሶናል #ኢየሱስ ማዕረግ ሁኖናል ።



🎼
@cgfsd
@ownkin
👍 11
አብዝቶ በመስቀሉ ስራ የተመሰጠ(የተደነቀ) በመዳኑ ውስጥ ያለውን ደስታ ያጣጥማል ።

@ownkin
@cgfsd
👍 13
( ይርባል እንዴ ??)

ሁለት ወዳጆች ጨዋታቸው ይጫወታሉ ። አንድኛዋ ለተወሰነ አመታት እስራኤል ኑሯለች ። ስለ እስራኤል የምታወቀውን ለሌላኛዋ ጓደኛዋ ትነግራታለች ።
   " እስቲ ተይኝ አሁን አሜሪካ ፣ አውስትራሊያ ሀገር ነው ምናምንቴዎች ፤ ሀገር ማለት እስራኤል ነው ። መሬቱን እንደው ብታይ አሸዋ ነው ግን በልምላሜ አረጓዴ ነው። ለካ እውነት  ነው ... በመፀሀፍ ቅዱስ ማር እና ወተት የምታፈሰው የተባለላት ያለ አንዳች አይደለም ። አይምሮአቸውስ ብትይ የተባረከ በእውቀት የተሞሉ ናቸው ።

እንደው በየቤተክርስቲያኑ ምስባክ እንደው ስለጌታችን ታሪክ  ሲወራ በአይምሮዬ ኮለለል እያለ ይታየኛል  የጎበኘሁት ሁሉ  ።
  ጌታችን የተቀበረበት መቃብር ብትይ ፣ ክብሩ ከደቀመዛሙርቱ ጋር የተገለጠበት ደብረ ታቦር ፣ ሊሰቀል ሲል ቀድሞ የፀለየበት ጌተሰማኒ፣ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ከፀለየ በኋላ ድንጋዩን ዳቦ አርግ ተብሎ የተፈተነበት ፣የተሰቀለበት ቀራኒዬ ጎልጎታ፣ ደግሞ በምፅአቱ ይመጣበታል የሚባለውንን ተራራ፣ ይሔ ይገርምሻ ስሙ ማን ነበር ??? ይሔ አራጣ ያበድር የነበረው አዎ አዎ አጭሩ ዘኪዬስ እሱ የወጣበት ዛፍ ሁላ ሳትቀር ነው ያየሁት ።
     ሌላኛዋ ጓደኛው በተራዋ ወይ ያንን ማየት የሚችል እንደው የተባረከ ነው!! አለች ፤ በረጅም እየተነፈሰች  እንባ ከአቀረሩ አይኖቿ ጋር ።
  ግን አንድ ጥያቄ ልጠቅሽ ....ግን እዛ ይርብሻል እንዴ?? (ይርባል እንዴ) ??   ማለት በቃ ይሔን እያየሽ አይርብሽም አይደል  ነፍስማ መቼም ይሔ አይታ ትጠግባለች እንጂ አትራብም ።
   የእስራኤሏ ሴትዬ አንገቷን ዝቅ አድርጋ ትዝታ እንደገረፈው ተክዛ አዎ ያጠግባል ብላ ቋጨችው።
.............................

.... ታዲያ እንዴት እንጥገብ??መቼም መንፈሳዊ ነገር ለመጥገብ የግድ ኢየሱሰስ የተወለደበት፣ እና የሞተበትን ብቻ ማየት አይጠበቅብንም ። እርሱ ራሱ የህይወት እንጀራ ነኝ ብሎናል እሱን ከበላን አይርበንም ማንነቱ ጥጋብ ሆኖናል።   

  ጋሽ ሰለሞን አበበ ገብረመድህን በአንድ የፅሀፉ ልጠፋቸው ላይ እንዲህ አሉ
  " መስቀል ላይ የተጋገረ እንጀራ "።
ግሩም አባባል እንደሆነ ተረድቻለሁ ። እግዚአብሔር መቼ የነፍስ ጠኔያችን እና ጉስቁላችን ለማከም፣ለማስታገስ፣ ለማጥገብ ብሎም ለማርካት አንድያውን በዘላለማዊ ፍቅሩ ህይወት እንዲሆንል ጋገረልን ። ከዛም የተጋገረውን በፍቅር ድምፅ ብሉልኝ አለ ። ከዚህ በላይ ምን የሚያጠግብ ህይወት አለ??ምንም !!
   የተጋገረውን እንጀራ እያሰብኩ አጭር ስንኝ ቋጠርኩ
        መስቀል ባሉት ምጣድ
                 ርሃብ ታሰረ
          የህይወት እንጀራው
                  መናው ተጋገረ

ለማስታወስ ያክል እግዚአብሔር እስራኤላዊያን በግብፅ ሳሉ ስለ ፋሲካው በግ በተመለከተ ከአዘዛቸው ትዕዛዝ አንዱ የፋሲካው በግ እንዲበሉ በመጀመሪያ ጥጋብ እንዲሆናቸው ነበር ።ግልፅ ያለ የኢየሱስ ምሳሌ ነው  ፋሲካችን ክርስቶስ ከሆነ ዘንዳ ምን እንበላለን ??ምንም !! እስራኤላዊያን ከግብፅ ወጥቸው ወደ ከነአን ለሚያደርጉት ጉዞ የበሉት የፋሲካ በግ ስንቅ ሆኖቸው ነው ። እኛስ የጀመርነው እውነተኛው መንፈሳዊ ህይወት ኢየሱስን ተመግበን አይደል ። የጀመርነውን ህይወት በድል የሚያስጨርሰን ሚስጥሩ የበላነው እውነተኛው መብል ኢየሱስ ነው ። እግዚአብሔር እንደዚህ የሚል አይመስላችሁም ..ብሉልኝ ይሔው ቢበሉት የማያልቅ ይሔው የሚትረፍረፍ ማዕድ ከሰማይ የሆነ የህይወት እንጀራ ። አባቶች መና በልተው ተራቡ በዛው በምድረበዳ ቀሩ ..እውነተኛ የህይወት እንጀራው ኢየሱስ የበላ ግን የዘላለም ህይወት ይቀናጃል ። ቲሞቲ ከለር የተባሉ ሰው እንዲህ አሉ " ኢየሱስ የህይወት እንጀራ ነኝ ሲል እግዚአብሔር ጋግሮላችኋል እያለ ነው "።

ጌታችን ኢየሱስ እሱ ራሱ የህይወት እንጀራ እንደሆነ ለተከተሉት ሊያሳውቅ በማሰብ 2አሳ እና 5እንጀራን አበዛላቸው ደስም አላቸው በሉ ተነጋገሩ መብዛቱ በራሱ አስደሳችነው አለማለቁም ሌላ አጃይብ ነው ።ግን ከበዛው ምግብ በላይ እሱ ኢየሱስ በእነርሱ ህይወት ሊበዛላቸው የህይወት እንጀራ ሊሆንላቸው እንደመጣ አልተገነዘቡም ነበር ።  2አሳ እና 5 እንጀራው በአንድ ጊዜ ተበልቷል ያው እዛ ቦታ ለነበሩት የህይወት እንጀራ ሁኖ ከመስቀል ላይ የተበላለው ግን ዛሬም ፣ነገም
  የሚበላ ለሁሉም የሚደርስ የተትረፈረፈ ማዕድ ነው ።


    በቀራንዬ ላይ ለእኛ በጉ ታርዷል
    ፈርኦን አይደለም ዲያቢሎስ ተረቷል
    በትረ ሙሴያችንም የጌታ መስቀል ነው
     በእሱ ቀጥቅጠን ነው ሞትን የገደልነው
                  (ዘማሪ ቴዎድሮስ)


✍ ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
👍 11
Показать все остальные посты

Настройки







Режим "полный" означает, что на странице аналитики канала все разделы будут отображаться сразу, блок за блоком.

Режим "со вкладками" означает, что в аналитике каналов страница будет поделена на разделы со вкладками для ускорения загрузки и отрисовки страницы.