Каталог каналов Новое Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Мониторинг Новое Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
736
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 315
Сегодня
+1
Просмотров на пост
Всего
331
ER
Общий
24.56%
Суточный
13.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 736 постов
Смотреть все посты
Пост от 10.11.2025 09:28
206
0
0
በአንድ ሰው መተላለፍ ምክንያት ሞት በዚህ ሰው በኩል የነገሠ ከሆነ የእግዚአብሔርን የተትረፈረፈ ጸጋና የጽድቅ ስጦታ የተቀበሉት በአንዱ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እንዴት አብልጠው በሕይወት አይነግሡ! ሮሜ 5 :17 ሞት ብቻውን ነገሰ ኢየሱስ አብሮ ነጋሽ አደረገን የመዳን ውበቱ ኢየሱስ ጋር አብሮ መክበሩ ነው። ኢየሱስ ጋር አብሮ መክበር ለአክባሪው ማንነት በፍፁም መገዛት እየተገዙ መክበር ነው ። @cgfsd
18
🥰 2
Пост от 09.11.2025 14:54
265
0
3
የማይተረጎም መውደድ በርከት ያሉ የእብራይስጥ ቃላት ወደ ተለያዮ ቋንቋዎች ሲተረጓሙ አንዳንድ ቃላት ግን በቀጥታ ከእብራይስጥ የተወሰዱ ቃላቶች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይገኛሉ፤ ሃሌሉያ፣ ኪሩብ እና ሆሳእናን እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል። የቅዱሳት መጽሐፍት ተርጓሚዎች "ሄሴድ"(חֶסֶד chesed) ለሚለው ቃልም ተመሳሳይ መንገድን ቢጠቀሙ መልካም ነበር ይባላል። በቀጥታ ቃሉን ቢጠቀሙ የቃሉን የትርጓሜ ሃብት የሚያሳይ ከመሆኑ የተነሳ እንደወረደ ቢቀመጥ ብለው የሚመኙ ብዙዎች ናቸው። ለዚህ ቃል አቻ የሚሆን ትርጓሜ የለውም ተብሎም ይሞገታል። ሲተረጓም "ምኅረት፣ ቸርነት፣ መልካምነት፣ ርኅራኄ፣ ዘላለማዊ ፍቅርና ወዘተ" ተብሎ ነው በአማርኛችን የተተረጓመው። ነገር ግን ሄሴድ የሚልን ቃል በተወሰኑ የአማርኛ ቃላቶች መወሰን ቃሉ የተሸከመውን ትልቅ ነገረ መለኮታዊ ሃሳብና እግዚአብሔራዊ ማንነት መጨቆን ይመስላል ይላሉ ከሃሳቡ ተነስተው። ትርጓሜው ውቅያኖስን በኩባያ የመጨለፍ ያህል ነው። የብሉይ ኪዳን ተንታኙ ቻድ በርድ እንደምሣሌ መዝሙር 36 ላይ ሄሴድ ሶስቴ የሚመጣበትን መንገድ ያስረዳል። (ቁ5) እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ [ሄሴድህ] እስከ ሰማያት ይደርሳል፤ ታማኝነትህም እስከ ጠፈር ይመጥቃል። (ቁ7)አምላክ ሆይ፤ ምሕረትህ [ሄሴድህ] እንዴት ክቡር ነው! የሰዎች ልጆች ሁሉ፣ በክንፎችህ ጥላ ሥር መጠጊያ ያገኛሉ። (ቁ10) ለሚያውቁህ ምሕረትህ [ሄሴድህ]፣ ልባቸውም ለቀና ጽድቅህ ዘወትር አይቋረጥባቸው። መዝሙር 36፥5፣ 7ና 10 (አጽንዖት የተጨመረ) . ሄሴድ ለትርጓሜ አዳጋች የሆነ የያሕዌን ፍቅርን የሚገልጽ ነው። ምሕረት የሚለው ቃል ሊሸከመው አይችልም። ሄሴድ የእግዚአብሔርን ቃልኪዳናዊ ታማኝነት አንድያ ልጁን በመስቀል እስከማንጠልጠል ያደረሰ ነው። በመስቀሉ የተገለጠ የእግዚአብሔር ልብ ነው። እስከ ምድረ ጥግ የሚከታተለን ፍቅር፣ የሚያነሳንና እንደ መልካም እረኛ በትከሻው የሚሸከመን ብሎም ወደ ቤት የሚወስደን አይነት ፍቅር ነው። ሄሴድ የሚለውን ቃል በተሟላ መልኩ ሊገልጸውና ሊያብራራው የሚችል አንድ ስም ብቻ አለ፤ ክርስቶስ ይባላል። እርሱ አብ ስጋ ይሆን ዘንድ የላከው እውነተኛ ሄሴድ ነው። የእግዚአብሔርን ሃሳብ በስጋ የገለጠ የፍቅርና ርህርሄ፣ የእንክብካቤና ቸርነት ሁሉ ቁንጮ ነው። የያሕዌ ሄሴድ በክርስቶስ ተገለጠ! እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህንና ፍቅርህን ዐስብ [ሄሴድህን] ዐስብ፤ እነዚህ ከጥንት የነበሩ ናቸውና። መዝሙር 25፥6 (አጽንኦት የተጨመረ) መልካም ሰንበት! (ከቻድ በርድ Unveiling Mercy: 365 Daily Devotions Based on Insights from Old Testament Hebrew የተወሰደ) ✍️ አማኑኤል አሰግድ
14
🔥 1
Пост от 06.11.2025 10:23
409
0
0
ሞት ለእኛ  በዲያብሎስ የተረገጥንበት ነው ። ሞት ለክርስቶስ ዲያብሎስን ድል የነሳበት፣ የሞት ኋይሉን የሻረበት ነው ። በዚህ አኳኋን ሞቱ ንግስናውን (ንጉስነቱን) የገለጠበት ነው ።      ማስያስ (ዲያቆን ሚክያስ አስረስ) @cgfsd
14
🔥 4
Пост от 05.11.2025 14:45
451
0
3
እግዚአብሔር አብ ልጁን ሰጠ እግዚአብሔር ወልድ ራሱን ሰጠ መንፈስ ቅዱስ ቃሉን ሰጠ    ቃሉም እኛን ወለደ 🎶
36
🔥 8
👍 1
Пост от 01.11.2025 06:38
454
0
2
ቲኪቆስ ቲኪቆስ የስሙ ትርጓሜ "ዕድል" ወይም "እድለኛ" ማለት ነው:: ቲኪቆስ "ከእስያ" አካባቢ [ሃዋሪያው ጳውሎስ እንደተናገረው ሐዋ. 20:4] ከኤፌሶን ወይም ባቅራቢያው ካሉት ከተሞች እንደመጣ ይታመናል:: በእርግጥ ቲኪቆስ ከጳውሎስ ጋር በሦስተኛው የጳውሎስ የወንጌል ሥርጭት ጉዞ [ጳውሎስ ከግሪክ ወደ ኢየሩሳሌም በሔደ ጊዜ] አብሮ እንደነበር ራሱ ሃዋርያው ተናግሯል (ሐዋ. 20:4):: ቲኪቆስ ግንባር ቀደም በመሆን በወንጌል ሥራ ውስጥ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ስማቸው እንደተጠቀሱት እንደነ ጴጥሮስ፣ ጳውሎስ፣ ዮሐንስ፣ ወዘተ አይሁን እንጂ፤ ከግንባር ቀደሞቹ ጀርባ ከነበሩት ድንቅ የወንጌል አገልጋዮች ተርታ የሚሰለፍ ወንድም ነው:: ስለ ቲኪቆስ የጳውሎስ ምስክርነቶች በጥቂቱ:- 1. ቲኪቆስ "የተወደደው ወንድም" ነው (ኤፌ.6:21፣ ቆላ. 4:7) 2. ቲኪቆስ "የታመነ አገልጋይ" ነው (ቆላ.4:7) 3. ቲኪቆስ "በጌታ ኢየሱስ ሥራ ታማኝ አገልጋይ" ነው (ኤፌ.6:21) 4. ጳውሎስ "በጌታም አብሮኝ ባሪያ የሆነ" በማለት ስለ ቲኪቆስ መስክሯል (ቆላ.4:7) 5. ጳውሎስ በቆላስይስ 4:11 ላይ "በእግዚአብሔር መንግሥት ከእኔ ጋር አብረው የሚሠሩት እነዚህ ብቻ ናቸው፥ እኔንም አጽናንተውኛል" ብሎ በስም ከጠቀሳቸው ወንድሞች መካከል አንዱ ቲኪቆስ ነው 6.  ጳውሎስ ከአናሲሞስ ጋር የቆላስይስን ደብዳቤ አስይዞ የላከው ሰው ቲኪቆስ ነው (ቆላ. 4:6-7) 7. ቲኪቆስ ምንአልባትም ጳውሎስ ቲቶን "ለተወሰነ ጊዜ" እንዲተካው ወደ ቀርጤስ ልኮት ሳይሆን አይቀርም (ቲቶ. 3:12) እንዲሁም ወደ ኤፌሶን ጢሞቴዎስን ለተወሰነ ጊዜ እንዲተካ ስለ መላኩ ፍንጮች አሉ (2ጢሞ. 4:12) 8. ቲኪቆስ የጳውሎስ የቅርብ ሰው፣ የወንጌል አገልጋይ፣ በወንድሞች መካከል በጤናማ የወንጌል አገልግሎት የተጋ በህይወት ምስክርነቱም የታወቀ ሰው ነበር:: ከላይ በጥቂቱ ከዘርዘርኳቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እንደምንረዳው፣ ቲኪቆስ:- - በምንም ማዕርግ ወይም የአገልግሎት መለያ አይታወቅ እንጂ የአገልግሎትና የሕይወት ምስክርነቱ ግን በቅዱሳን ዘንድ የታወቀ ሰው ነበር:: - ለጳውሎስ የወንጌል አጋር ብቻ ሳይሆን የኑሮም አጋር ነበር:: "ኑሮዬን ያስታውቃቹሃል" ያለውን ልብ በሉ (ቆላ. 4:7) - በወንጌል ምክንያት ታስሮ በብቸኝነት ለነበረው ጳውሎስ መጽናናት የሆነ ሰው ነው - እውነተኛው አስተምህሮ (orthodoxy) ከህይወት ምስክርነቱ (Orthopraxy) የማይጣላበት ሰው ነበር:: - ታማኝ ነው፣ የተወደደ ነው፣ አገልጋይ ነው፣ መልዕክተኛ ነው፣ ወዘተ ቲኪቆስ በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ሆነ በአሁኗ ቤተክርስቲያን ከ"መጋረጃ ጀርባ" ወይም "behind the scene"ወይም "ያልተዘመረላቸው ጀግኖች" ወይም "unsung heros" ለሆኑ ብዙ አገልጋዮች እንደ ምሳሌ የሚቀርብ አገልጋይ ነው:: ለአንድ የወንጌል አገልጋይ ስም ሳይሆን የህይወት ምስክርነት፣ ማዕረግ (title) ሳይሆን ለወንጌል ታማኝነት መሠረታዊ ጉዳይ እንደሆነ ያስተማረም ሰው ነው ቲኪቆስ:: ✍️ Eyob B kassa @cgfsd
🔥 11
4
Пост от 29.10.2025 12:01
420
0
1
( የእግዚአብሔር ውበት) ፍጥረት በዝምታ የእግዚአብሔርን እፁብ ድንቅነት ይመሰክራሉ ። ታሪክም ከእግዚአብሔር በቀር ሃያል እንደሌለ ያሳብቃል  ። በቅዱሱ መፀሃፍ የተገለጠው የእግዚአብሔር የማንነትና የስራው ውበት ይለያል ! አስደናቂው ባህሪው ውስጥ እንከን የለሽ ፍፁም ትክክል ስራው ይታያል ። በተቀያየሩ ሰዎች ውስጥ ያልተለወጠ እቅዱ ፣ ደጋግሞ ሰውን መቅረብ ፣ በሰው መካከል ለመኖር አጎንብሶ መምጣቱ ፣ በሰው ቋንቋ እኔ ማለት ብሎ በሀ ሁ ራሱን መግለፁ ግሩም ነው ። ከመፀሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ድረስ የሚታየው ይሔ አስደናቂው አምላክ ያለው የማንነት ውበት ነው ። መፀሃፍ ቅዱሱን በትክክል ያነሳ በእግዚአብሔር ማንነት መገረም ውስጥ ደጋግሞ ይወድቃል ! @cgfsd
18
🔥 6
Пост от 24.10.2025 12:49
445
0
6
....ስለዚህ እግዚአብሔር ለፍጥረቱ አዝኖ የፍጥረቱን መከራ የራሱ አድርጎ ወሰደ ። ጎልጎታ ከዚህ የእግዚአብሔር ሐዘኔታ ይመነጫል ። እናም በጎልጎታ ኮረብታ ላይ መስቀል ከመተከሉ በፊት በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ መስቀል ተተክሎ ነበር ። መስቀሉ ከጎልጎታ ኮረብታ ቢነቀልም ፣ በእግዚአብሔር ልብ ላይ ያለው መስቀል ግን እስካሁንም አለ ።            የተሰቀለው  (ጳውሎስ ፈቃዱ)
18
🔥 4
🥰 3
😢 2
Смотреть все посты