Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
719
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 420
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
383
ER
Общий
17.96%
Суточный
9.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 719 постов
Смотреть все посты
Пост от 15.02.2026 06:58
139
0
1
#እያደገ የመጣ መገለጥ
(progressive revelation)


የመፀሃፍ ቅዱሳችን ባህሪ ለይቶ መረዳት መፀሃፍ ቅዱሳችን በትክክለኛ መንገድ እንድናውቅ ያግዘናል ። የመፀሃፍ ቅዱስ ፍሰት እያደገ የመጣ መገለጥ ነው ። መፀሃፍ ቅዱሱ እያደገ የመጣ ነው ሲባል ከታሪኮች ወደ ታሪኮች ስንሄድ በፊት ያልነበረ ነገር መጣ እያልን ሳይሆን የእግዚአብሔር ማንነት ፣ስራ መገለጡ የበለጠ እየጨመረ ግልፅ እየሆነልን መጣ ለማለት ነው ።  እያደገ መጣ የተባለው መገለጥ በፊት ከነበረው የበለጠ እየተብራራ መጣ እንጂ የበፊቱ ስህተት ወይም ከበፊቱ አዲስ ነገር መጣ ለማለት አይደለም ።

ለምሳሌ ያክል የስላሴን መገለጥ መመልከት እንችላለን ። ስላሴ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ነበር ። መገለጡ ብዙ ግልፅ አልነበረም ፣ወይም የስላሴ ሶስትነት ይልቅ ግልፅ የሆነልን አንድነቱ ነበር ። በአዲስ ኪዳን በይበልጥ ተብራርቶልን በይበልጥ የስላሴን አንድነትና ሶስትነት ተገነዘብን ። ይሔ እያደገ የመጣ መገለጥ ይባላል ። ስላሴ አልነበረም በብሉይ ኪዳን ሳይሆን ወይም በብሉይ ኪዳን ያለው ስላሴ ስህተት ነው ለማለት አይደለም እያደገ የመጣ መገለጥ ነው (ለእኛ ያደገው እውነቱ ሳይሆን መገለጡ ነው) ። ይልቁንም የበለጠ እንድንገነዘብ እንድናወቅው ለመግለጥ ለማብራራት የሚረዳ ነው እያደገ የመጣ መገለጥ ።

ለምን መፀሃፍ ቅዱሳችን እያደገ የመጣ መገለጥ አፃፃፍ ተከተለ ? መፀሃፍ ቅዱስ የሚያትትተው ስለ ታላቁ አምላክ እግዚአብሔር ነው ። እግዚአብሔር ተገልጦ የሚያልቅ አምላክ ባለመሆኑ በሂደት ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ባለው ጉዞ የበለጠ ራሱን ሀሳቡን በግልፅ እየገለጠልን መጣ ። ሌላው ሰው መሆናችን ሁሉን ባንዴ አውቀን የማንጨርስ መሆናችን እያደገ የመጣ መገለጥ ለእኛ አስፈላጊ ነው ። መፀሃፍ ቅዱስ እያደገ የመጣ መገለጥ መሆኑ ማወቃችን ከመፀሃፍ ቅዱስ ጋር ካለን ግንኙነት ለምን ይጠቅመናል? መፀሃፍ ቅዱስ ስናጠና የሆነ ቦታ ላይ ብቻ እንዳከማች ሙሉ መፀሃፍ ቅዱስ በስፋት እንድንመለከት ፣ አንድ ሀሳብ ከአንድ ቦታ ስናየው ያ ቦታ ሊሰጠን የሚችለው ክፍሉ ሊለን የፈለገው ሀሳብ ብቻ እንጂ ሰፊውን መልዕክት  አስፍተን እድናይ ላያደርግ ይችላል ፤ ምሳሌ ስለ ፀጋ ከሆነ ከአንድ ክፍል ያየነው ክፍሉ ከአውዱ የተነሳ ይነግረናል ፤ ከሙሉ የመፀሃፍ ቅዱስ አንፃር ሲሆን ፀጋ በብዙ አቅጣጫ መረዳት እንችላለን ። ስለዚህ እያደገ የመጣ መገለጭ(progressive revelation ) የመፀሃፍ ቅዱሳች አፃፃፍ ባህሪ በመሆኑ መገንዘብ ያስፈልገናል ።


@cgfsd
🔥 3
Пост от 11.02.2026 08:22
307
0
1
ክርስቶስ ኢየሱስ ሁለት ምፅአቶች(መምጣቶች) አሉት። የመጀመሪያው መምጣሉ ወይም ምፅአቱ ሰውን ለማዳን ሰው ሁኖ ወደዚህ ምድር የመጣው መምጣት ሲሆን፤ ሁለተኛው ምፅአቱ ደግሞ ዳግመኛ በክብር የሚመጣው  መምጣቱ ነው።  የመጀመሪያው መምጣቱ የሁለተኛው መምጣት እንደማይቀር ማረጋገጫ ነው። በመጀመሪያ መምጣቱ ስለ ሰው እንደሚሞትና ከሙታን እንደሚነሳ ተናግሮ ነበር፤ የተናገረው እውነት በመሆኑን በመሞትና ከሙታን በመናሳት አረጋገጠ። ሁለተኛ እመጣለሁ ብሎ በመሄዱ እንደሚመጣ የመጀመሪያው መምጣቱ እውነተኛ መሆኑና ለሁለተኛ መምጣቱ የተስፋ መታመኛ ነው። በመጀመሪያ መምጣቱ(በመወለዱ፣ በቅድስና በመመላለሱ፣ በሞቱና በመነሳቱ) የፈፀመው ታማኝነት የሁለተኛ መምጣቱ ላይ ታማኝ እንደሆነና በእሱም እርግጠኛ እንድንሆን ያደርገናል።

@cgfsd
13
Пост от 09.02.2026 22:00
361
0
1
#በመሰብሰባችን
¶ፕሮግራም መሪዎች አስጨፍነውን ባይሰብኩን በጸሎት ከአምላካችን ጋር እንድንፈስ ቢመሩን፤
¶ዘማሪዎች አንዱን መዝሙር ሳናጣጥም ከመዝሙር መዝሙር እንደ ጦጣ ባይዘሉ፤
¶ማስታወቂያ 1ሰዐት ያህል ወደ ኋላ ቅሩ የሚባሉ ሰዎች ስም እየተጠራ ባይንዛዛ፤
¶የቃሉ አገልጋዮች(ሰበረኪያን) ጭራና ቀንዱ የማይታወቅ፣ማለቂያና ነጥብ የሌለው ንግግር ባያደርጉ፤
#ይልቁኑ መግቢያ 👉ሐቲት 👉መደምደሚያ ያለው፤
👉ውቅር ያለው መልእክት በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በመታገዝ ለማገልገል ቢዘጋጁ፤
#ምዕመናን :-በቤተክርስቲያን የፕሮግራም መርሐግብር ጊዜአቸውን ጠብቀው በታማኝነት ቢገኙ፤
@መጽሐፍ ቅዱስና ማስታወሻ ይዘው ቢገኙ፤
@የከንፈሮቻቸውን ፍሬ ምሥጋናን እና የገንዘባቸውን ስጦታ በደስታና በፈቃደኝነት ቢያደርጉ፤
@ቃለ እግዚአብሔር ሲሰበክ ስልካቸውን በመነካካት ከአምልኮ መንፈስ እንዳይወጡ ስልካቸውን ✈️ ላይ ቢያደርጉ፤
@ቃለ እግዚአብሔር ተሰብኮ እንዳለቀ እንጸልይ ሲባል እንሂድ እንደተባለ ውልቅ እልም ባይሉ😁
@የመጨረሻውን ጸሎትና ቡራኬ ተቀብለው በቅዱሳን ሰላምታ ሰላምታ ተለዋውጠው፤ የሚያቁትን ብቻ ሳይሆን አዳዲስ ሰዎችንም ጭምር ሰላም ብለው በፍቅር ቢሰነባበቱ እላለሁ።


✍ ወንጌላዊ ሔኖክ ጌታቸው
@cgfsd
12
🔥 9
Пост от 05.02.2026 12:19
406
0
3
(የድነት መልኩ )



ድነት የመፀሃፍ ቅዱሳች የታሪኩ ልብ ነው ። መፀሃፍ ቅዱሳችን የድነት መፀሃፍ ነው (salvic book) ፣ አምላካችን አዳኝ የሆነ አምላክ ነው ፣ ቤተክርስቲያን የዳነች ማህበር ህብረት ናት። በዚህ ሁሉ መፀሃፍ ቅዱሳችን በድነት ሀሳብና እውነት የታጨቀ እንደሆነ መገንዘብ እንችላለን። ድነትን በመፀሃፍ ቅዱሳዊ ልኩና መልኩ መረዳት መፀሃፍ ቅዱሳችን በአግባቡ ለመተርጎም በር ይከፍትልናል። ሐዋሪያት በመፀሃፍ ቅዱሳችን የድነት መልክና ባህሪ በሚገባን መንገድ ገልፀውልናል ።

ሐዋሪያው ጳውሎስ ድነትን ወደ እግዚአብሔር ፊት መዞር ነው ወይንም ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው ይለናል ። በዛው የድነትን አላማ ሲያብራራ ደግሞ እውነተኛውን አምላክ  እግዚአብሔር ክብር እየተገዙ ማምለክ መሆኑን ጳውሎስ ፍንጭ ይሰጠናል።
      " በእንዴት ያለ አቀባበል እንደ ተቀበላችሁንና ሕያውና እውነተኛ የሆነውን አምላክ ለማገልገል ከጣዖታት ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንደ ተመለሳችሁ እነርሱ ራሳቸው ይናገራሉ፤ "
1 ተሰሎንቄ 1:9

ሐዋሪያው ጴጥሮስ ድነት የእግዚአብሔር በጎነት ወይም ታላቅ ስራ እንደሆነ ያበስረናል ። እግዚአብሔር ባህሪውን የገለጠበት ፣ ራሱን የገለጠበት መንገድ ነው ። ድነት እግዚአብሔር የማወቂም ጭምር ነው ።
     "እናንተ ግን ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃኑ የጠራችሁን የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ እንድታውጁ፣ የተመረጠ ትውልድ፣ የንጉሥ ካህናት፣ ቅዱስ ሕዝብ፣ እግዚአብሔር ለራሱ የለያችሁ ሕዝብ ናችሁ።"
1 ጴጥሮስ 2:9

ሐዋሪያው ዩሀንስ ድነት ከእግዚአብሔር የሚደረግ ህያው ህብረት እንደሆነ ይጠቁመናል ። መዳን ግቡ ከእግዚአብሔር የሚኖር ህብረት ሰለመሆኑ በዩሀንስ ፅሁፍ ውስጥ ተንፀባርቋል ።
      "እናንተም ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ፣ ያየነውንና የሰማነውን እንነግራችኋለን፤ ኅብረታችንም ከአብ፣ ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው። "
1 ዮሐንስ 1:3


@cgfsd
8
🔥 2
Пост от 03.02.2026 22:48
407
0
3
ወንጌሉን መወደድ ከሁሉ የሚቀድም የክርስትና ተግባር ነው ። ወንጌሉ ማለት እግዚአብሔር የገለጠውን እውነት የማዳን መንገድ ፣ የክርስቶስ የቤዛነት ስራ ወይንም የክርስትና አስተምሮዎች አጠቃሎ የሚይዝ ሀሳብ ነው። ወንጌሉን ስንል ወተን የምንሰራውን የወንጌል ስርጭት ብቻ እያልን አይደለም የክርስትና ትምህርቶቻችንም የወንጌሉ አካል ናቸው ። 

እውነተኛ ክርስቲያን የዳነበትን ወንጌል ይወዳል፣ እውነተኛ አገልጋይ በደስታ እየወደደው የሚያገለግለው የተገለጠውን የወንጌል እውነት ነው ። ወንጌሉን መወደድ ሲባል ጥቅቅ አርገን ወንጌሉን አውቀን እንጨርሰዋለን ለማለት ሳይሆን ሁሌ እያወቅነው እየተደመምንበት ፣ እየተገረምንበት እንኖርበታለን ። ግሪኮች ለአፈ -ታሪኮቻቸው ፍቅር አላቸው፣ ንጉሶች ለዙፋኖቻቸው መወደድ አላቸው ፣ መርከበኞች ለመልህቆቻቸው ፍቅር አላቸው፣ ክርስቲያኖች ለወንጌሉ ፍቅር አላቸው ምክኒያቱ አምላካቸው ራሱን የገለጠላቸውና ህብረቱን ያደረገው በወንጌሉ ስለሆነ ነው። በተቀበልነው ወንጌል ረክተናል? ደስተኛ ነን ወይ?
20
👍 1
Пост от 01.02.2026 05:40
366
0
0
ከቤተክርስቲያን ታሪክ ምን እንማር ?

@cgfsd
Звукозапись
🔥 4
Пост от 30.01.2026 17:57
415
1
4
ደረተ ወርቅ ራሰ በረዶ
ይደገፍሃል ዘላለም ወዶ
እንኳን አውርተህ ዝም ብለህ
ፍጥረት ይርዳል ከግርማህ ፊት
ኩሩ ማዕበል እጅ ይነሳሃል
ተራራ ጭሶ  አለው ይልሃል

🎶
10
🔥 9
Смотреть все посты