Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
1.1K
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 490
Сегодня
-2
Просмотров на пост
Всего
342
ER
Общий
20.25%
Суточный
10.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 1 078 постов
Смотреть все посты
Пост от 27.05.2026 10:17
46
0
1
(የመስቀሉ አሰላሳይ )


መስቀሉ በተደጋጋሚ አስበው ካሳሰቡን ሰዎች መካከል ዘማሪ አዲሱ ወርቁ አንዱ ናቸው ። ጋሽ አዲሱ መዝሙራቸው የመስቀሉን ፍቅር እንድናስብ የሚጋብዝ በጥልቀት የታሰበ መንፈሳዊ ስራዎች ናቸው ። በሁለቱ አልበም መዝሙሮች ውስጥ በርካታ የመስቀሉ ስራዎች ታጭቀው እናገኛለን ። የአልበም መዝሙር ስራዎች ርዕስ ራሱ የመስቀሉ ፍቅር ይሰኛል ።

አንድ ጊዜ ኮብልላ ነበረ ነፍሴ ከእግዜር መንገድ .... ደሙን ለእኔ አፍስሶ አዳነኝ ...የሚለውን መዝሙር በሬዲዮ አፄ-ሀይለስላሴ ይሰማሉ ። ዘማሪውን አዲሱ ወርቁ በዛ መከራ ዘመን አስጠርተው አበረታቱት(የተጠራ ህይወት መጋቢ መርዕድ ለማ) ። ምን ያህል ዘመን ተሻጋሪ ለሁሉም ሰው መሆን የሚችል መዝሙር እንደሆነ ከዚህ ታሪክ መረዳት እንችላለን ።

ጋሽ አዲሱ የመስቀል ፍቅሩን እንጨት ላይ የሆነ አንድ ክስተት አርገው አያዩትም ። የእግዚአብሔር መንግስት እቅድ ፣ የአማኝ ህይወት ላይ የዕለት ዕለት ጉልህ ተፅዕኖ ያለው የእግዚአብሔር የልብ ምክር አደርገው ያቀርቡናል ፤ በዚህ ብቻ ሳይሆን አማኝ ደጋግሞ የመስቀል ፍቅሩን ማሰብ ማሰላለሰል እንደሚገባው ይጠቁማሉ። ሌላኛው በመዝሙራቸው ውስጥ የመስቀሉ ስራ ወደ ምስጋና ሲያመራቸው እናያልን ። የተዋጀ ሰው ምስጋና ፣ የዳነ ሰው ምስጋና አላቸው  ።  ምስጋናው ውስጥ መገረም ፣ መደነቅ ይታይባቸዋል ።
"
የነፍሳት ሁሉ ምስጋና ዙፋንህን ይክበበው
በቸርነትህ ተገርሟል  በልጅህ የዋጀኸው"

ምስጋናቸው መገረም ብቻ አይደለም ። በተግባራዊ የሆነ ምድር ላይ የወረደ መሆን እንዳለበት ፍንጭ ይሰጡናል ።
      " ጌታዬን አከብራለሁ ጌታዬን አከብራለሁ
                   በኑሮዬ ..................."

የጋሽ አዲሱ ወርቁ መዝሙሮች የመስቀሉን ፍቅር በማሰላለሰል ፣ የእግዚአብሔር ፍቅር በመረዳት ተግባራዊ የሆነ ህይወት ለመኖር ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ጥልቅ ህብረት እንዲኖር ጥሪ ያቀርብናል ። መዝሙሮቹ እንድትሰሙት አበረታታለሁ🙌 ።


@cgfsd
4
Пост от 25.05.2026 18:03
228
1
1
(ሊቀ-ካህናቱ ይባርከናል --አሜን)



ክርስቶስ የብዙ ሰዎችን ኀጢአት ለመሸከም፣ እንዲሁ አንድ ጊዜ መሥዋዕት ሆኖአል፤ ሁለተኛ ጊዜም ይገለጣል፤ ይህም ለሚጠባበቁት ድነትን ለማምጣት እንጂ ኀጢአትን ለመሸከም አይደለም።
ዕብራውያን 9:28


በዕብራዊያን መፀሃፍ ወደ ሰማይ የገባ ሊቀካህናት አለ ። ወደ ሰማይ የገባበት አገባብ ከብሉይ ኪዳን የሊቀካህን የስርየት ቀን አገባብ ጋር እያነፃፀረ ያሳየናል ። የብሉይ ኪዳን የስርየት ቀን ሊቀካህኑ መስዋዕቱን ይዞ ወደ መቅደሱ ይገባል። በመቅደሱ ውስጥ መስዋዕቱን አቅርቦ ከጨረሰ በኋላ ከመቅደሱ ይወጣል ። ህዝቡ ከመቅደስ ውጭ ይጠባበቃሉ። ሊቀካህናቱ ከመቅደሱ ወጥቶ ህዝቡን ይባርካል ። በዕብራዊያን መፀሃፍ የክርስቶስ ሊቀካህናት ስራው ከብሉይ ኪዳኑ የሊቀካህናት ወደ መቅደስ አገባቡን በተመሳሳይ መንገድ አተራረክ ይተርካል ። ሊቀካህናት ክርስቶስ ደሙን ይዞ ወደ ሰማዩ መቅደስ ገባ ። ስለ ህዝቡ አንድ ጊዜ ፈፅሞ ታየ  ። ልክ እንደ ብሉይ ሊቀካህናት ክርስቶስ ከመቅደሱ ወጥቶ ይመጣል ። እየጠበቁት ላሉት ህዝቦች ይባርካቸዋል ።

የክርስቶስ ዳግም መምጣት ከሚያረጋግጥሉን ነገሮች አንዱ የክርስቶስ ወደ ሰማይ መቅደስ ካህን ሁኖ መግባቱ ከዛም ተመልሶ መጥቶ ህዝቡን እንደሚባርክ የሚስል ስዕል ነው ። ሊቀካህኑ ስለ መስዋዕቱ ከገባ ተመልሶ ወጥቶ ህዝቡን ይባርካል ። ሊቀካህናቱ ወጥቶ ይባርከናል ። ይመጣልናል የሚባርከን ከእርሱ ለዘላለም በመሆን ነው ። ሊቀካህናቱ ባለበት መኖር ይሆናል መጨረሻው ። በመማፀኛ ከተማ ከፍርድ ያመለጡ  ሀጢያተኞች ስለ ምህረት በአንድ ከተማ ከሊቀካህናቱ ጋር ይኖራሉ ። የክርስቶስ ክህነት ሀጢያት በተሸነፈበት እግዚአብሔር በምናይበት ዘላለም ውስጥ ለመኖር ሊቀካህናት አንድ ጊዜ በመቅደሱ እንደታየልን በመጨረሻውም ከፍርድ ይልቅ ስለእኛ በመምጣቱ ድጋሚ ይታይልናል ። ይሔ ዳግም መምጣቱ ነው ። ሊቀካህናቱ ይባርከናል ።


“እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ፥ የብዙዎችን ኃጢአት ሊሸከም አንድ ጊዜ ከተሰዋ በኋላ፥ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁት ሁለተኛ ጊዜ ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል።”
  — ዕብራውያን 9፥28

እንዲህ ይባርካቸው ነበር ካህኑ :-

“ ‘እግዚአብሔር(ያህዌ) ይባርክህ፤
ይጠብቅህም፤
እግዚአብሔር(ያህዌ) ፊቱን ያብራልህ፤
ይራራልህም፤
እግዚአብሔር(ያህዌ) ፊቱን ይመልስልህ፤
ሰላሙንም ይስጥህ።’ ”
“በዚህ ሁኔታ ስሜን በእስራኤላውያን ላይ ያደርጋሉ፤ እኔም እባርካቸዋለሁ።”
ዘኁልቍ 6:24-27


@cgfsd
13
👍 1
🔥 1
Пост от 23.05.2026 20:35
189
0
3
መስቀል እውነት ነው። እውነት ብቻ ሳይሆን ግን የእውነትነት ልኬት ነው። መስቀል ማለት የሰውነት እጣ ነው። መስቀል ሁሉም ለሚኖረው ህይወት ምሳሌ ነው። ግን ከንቱ የማይበቃ የሚልቀው ሚገኝለት የሚተካ አይደለም። ፍፁም የተኖረ ህይውት ምሳሌ ነው። የእውነት መጨረሻ ልኩ መስቀል ላይ ተገልጧል። የማይካደው እውነት ፣ የማይታፈን ጩኸት ፣ የሰው እጣፈንታ በእያንዳንዱ ቅፅፈት..መስቀል

ሰው ልኩ ከመስቀል አያልፍም፣ ከጎልጎታ የሚልቅ መስቀል አይገኝም። የመስቀል ልክ ቀራኒዮ የሰውም ልኩ መስቀል ነው ካልን የናዝሬቱ ኢየሱስ የሰው ድምዳሜ ነው እያልን ነው ማለት ነው።
19
Пост от 22.05.2026 17:47
314
0
0
(ኢየሱስ ተሸኘ)

በቤተክርስቲያን....
ጭብጨባው በረታ
ከበሮው ተመታ
መድረኩ ተናጠ
ቤቱ ተናወጠ
የምዕመናን ልብ ፥ በደስታ ቀለጠ
       እነሆ
ደማቁ ዝማሬ ፥ በአዳራሹ ናኘ
በሆታ በእልልታ ፥ ኢየሱስ ተሸኘ

(✍ገጣሚ ዳዊት ፀጋዬ)


  ይሔ ግጥም ሳነብ የዛሬ 4 አመት የተሰመኝ ስሜት 😭 ባነብቡኩት ቁጥር አሁንም ያስደነግጠኛል ።
10
😢 7
Пост от 22.05.2026 08:08
256
0
1
በ ትንሳኤህ ማግስት ...ፆም ፀሎቱም ቀረ ስግደቱም ተረሳ ... እኛ መሞት ጀመርን አንተ ስትነሳ🥺
9
😢 7
Пост от 21.05.2026 08:52
377
0
1
(የክርስቶስ ተግባቦት)


የመግባባት ልክ ክርስቶስ ሰው የሆነበት እውነት ነው ። እጅግ በጣም ለፍጥረቱ አብዝቶ ቅርብ የሆነበት የበለጠ  ደግሞ ሰው ጋር ሰው በመሆን የሰው ወገን በመሆን መቀራራብ መግባባት (communication) በክርስቶስ ታይቷል ። አምላክ ሰው ሆነ ስንል ከምናስባቸው ጉዳዮች አንድኛው  አምላክ ፍጥረቱን ሰውን የቀረበት አስደናቂው ቅርበት ነው ።  ማቴ 1:23.. ክርስቶስ ሰው በመሆን ሂደቱ ውስጥ ከተጠራባቸው ስሞች አንዱ አማኑኤል ነው " እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው " ። በክርስቶስ ሰው መሆኑን እግዚአብሔር ከፍጥረቱ ጋር አብዝቶ መግባባት ፣ ቅርበት ፣ መጠጋጋት ያየንበት ውብ እውነት ነው ። ክርስቶስ በምድር ቆይታው ራሱን " የሰው ልጅ " እያለ ይጠራ ነበር ። ይሔም ደግሞ የሚያሳየው ራሱን ከሰው ጋር ያደረገው ቅርበት ነው ። ክርስቶስ ሰው በመሆን ያስተዋልነው ተግባቦት የፍቅር ተግባቦት ነው ። የክርስቶስ ሰው መሆን እጅግ አስደናቂው ተግባቦት(communication) ነው ። ይሔ መግባባት ዝምድናን አስገኘልን ። ክርስቶስ እውነተኛ ፍፁም ሰው በመሆኑ የሰው ልጅ የሚለው ስም ወከለው ፣ ሰው የሚለው መጠራያ መለያው ሆነ ፣ ስለዚህ የሰው ልጅ በሙሉ ዘመዱ ፣ ወገኑ ፣ ሆነው ። እግዚአብሔር እንደዚህ ተግባባን ቀረበን።

@cgfsd
10
Пост от 20.05.2026 09:59
357
0
4
The Holy sprit is The workhouse of Trinity. He is the love between father and son. He is the grace between christ and the beliver. He is the power of God's presence and the presence of God power in both creation and redemption

   Michael F.bird

@cgfsd
27
Смотреть все посты