Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
716
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 415
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
355
ER
Общий
20.75%
Суточный
11.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 716 постов
Смотреть все посты
Пост от 05.02.2026 12:19
125
0
0
(የድነት መልኩ )



ድነት የመፀሃፍ ቅዱሳች የታሪኩ ልብ ነው ። መፀሃፍ ቅዱሳችን የድነት መፀሃፍ ነው (salvic book) ፣ አምላካችን አዳኝ የሆነ አምላክ ነው ፣ ቤተክርስቲያን የዳነች ማህበር ህብረት ናት። በዚህ ሁሉ መፀሃፍ ቅዱሳችን በድነት ሀሳብና እውነት የታጨቀ እንደሆነ መገንዘብ እንችላለን። ድነትን በመፀሃፍ ቅዱሳዊ ልኩና መልኩ መረዳት መፀሃፍ ቅዱሳችን በአግባቡ ለመተርጎም በር ይከፍትልናል። ሐዋሪያት በመፀሃፍ ቅዱሳችን የድነት መልክና ባህሪ በሚገባን መንገድ ገልፀውልናል ።

ሐዋሪያው ጳውሎስ ድነትን ወደ እግዚአብሔር ፊት መዞር ነው ወይንም ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው ይለናል ። በዛው የድነትን አላማ ሲያብራራ ደግሞ እውነተኛውን አምላክ  እግዚአብሔር ክብር እየተገዙ ማምለክ መሆኑን ጳውሎስ ፍንጭ ይሰጠናል።
      " በእንዴት ያለ አቀባበል እንደ ተቀበላችሁንና ሕያውና እውነተኛ የሆነውን አምላክ ለማገልገል ከጣዖታት ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንደ ተመለሳችሁ እነርሱ ራሳቸው ይናገራሉ፤ "
1 ተሰሎንቄ 1:9

ሐዋሪያው ጴጥሮስ ድነት የእግዚአብሔር በጎነት ወይም ታላቅ ስራ እንደሆነ ያበስረናል ። እግዚአብሔር ባህሪውን የገለጠበት ፣ ራሱን የገለጠበት መንገድ ነው ። ድነት እግዚአብሔር የማወቂም ጭምር ነው ።
     "እናንተ ግን ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃኑ የጠራችሁን የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ እንድታውጁ፣ የተመረጠ ትውልድ፣ የንጉሥ ካህናት፣ ቅዱስ ሕዝብ፣ እግዚአብሔር ለራሱ የለያችሁ ሕዝብ ናችሁ።"
1 ጴጥሮስ 2:9

ሐዋሪያው ዩሀንስ ድነት ከእግዚአብሔር የሚደረግ ህያው ህብረት እንደሆነ ይጠቁመናል ። መዳን ግቡ ከእግዚአብሔር የሚኖር ህብረት ሰለመሆኑ በዩሀንስ ፅሁፍ ውስጥ ተንፀባርቋል ።
      "እናንተም ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ፣ ያየነውንና የሰማነውን እንነግራችኋለን፤ ኅብረታችንም ከአብ፣ ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው። "
1 ዮሐንስ 1:3


@cgfsd
5
🔥 1
Пост от 03.02.2026 22:48
246
0
3
ወንጌሉን መወደድ ከሁሉ የሚቀድም የክርስትና ተግባር ነው ። ወንጌሉ ማለት እግዚአብሔር የገለጠውን እውነት የማዳን መንገድ ፣ የክርስቶስ የቤዛነት ስራ ወይንም የክርስትና አስተምሮዎች አጠቃሎ የሚይዝ ሀሳብ ነው። ወንጌሉን ስንል ወተን የምንሰራውን የወንጌል ስርጭት ብቻ እያልን አይደለም የክርስትና ትምህርቶቻችንም የወንጌሉ አካል ናቸው ። 

እውነተኛ ክርስቲያን የዳነበትን ወንጌል ይወዳል፣ እውነተኛ አገልጋይ በደስታ እየወደደው የሚያገለግለው የተገለጠውን የወንጌል እውነት ነው ። ወንጌሉን መወደድ ሲባል ጥቅቅ አርገን ወንጌሉን አውቀን እንጨርሰዋለን ለማለት ሳይሆን ሁሌ እያወቅነው እየተደመምንበት ፣ እየተገረምንበት እንኖርበታለን ። ግሪኮች ለአፈ -ታሪኮቻቸው ፍቅር አላቸው፣ ንጉሶች ለዙፋኖቻቸው መወደድ አላቸው ፣ መርከበኞች ለመልህቆቻቸው ፍቅር አላቸው፣ ክርስቲያኖች ለወንጌሉ ፍቅር አላቸው ምክኒያቱ አምላካቸው ራሱን የገለጠላቸውና ህብረቱን ያደረገው በወንጌሉ ስለሆነ ነው። በተቀበልነው ወንጌል ረክተናል? ደስተኛ ነን ወይ?
19
👍 1
Пост от 01.02.2026 05:40
335
0
0
ከቤተክርስቲያን ታሪክ ምን እንማር ?

@cgfsd
Звукозапись
🔥 4
Пост от 30.01.2026 17:57
405
1
4
ደረተ ወርቅ ራሰ በረዶ
ይደገፍሃል ዘላለም ወዶ
እንኳን አውርተህ ዝም ብለህ
ፍጥረት ይርዳል ከግርማህ ፊት
ኩሩ ማዕበል እጅ ይነሳሃል
ተራራ ጭሶ  አለው ይልሃል

🎶
10
🔥 9
Пост от 30.01.2026 16:10
414
0
0
የእግዚአብሔርን ውበት በባህሪው ውስጥ በግልፅ ይታያል። እግዚአብሔር ባህሪው እሱነቱ ነው። በትክክል የአምላክ የውበት ድምቀት ባህሪው ውስጥ አለ። ስለ እግዚአብሔር ባህሪ ሲታሰብ በአንዱ ባህሪው ብቻ እሱ እንዲዚህ ብቻነው አይባልም። እግዚአብሔር ፍቅር ነው ደግሞ ፃዲቅ ነው። የእግዚአብሔር ርህራሄ ብቻ አለው አንልም ። በእርሱ ዘንድ የባህሪ መጋጨት የለም። መሃሪም ፣ አፍቃሪም ፣ ፃዲቅ ፣ፈራጅም ነው። መጋጨትም መከፋፈልም እሱን አያቀውም። እሱ በባህሪውም ድምር ስልተሰራ በባህሪዎቹ መካከል መካፈልም አያቀውም።

የማንነቱ ውበት በባህሪዎቹ ውስጥ ታይተዋል። ሰውን ሲፈጥር በድነትም ባህሪውን ለሰው ልጅ አካፈለ። በእርግጥ ያካፈለው ያላካፈለውም ባህሪ አለው። ፍቅር ፣ርህራሄው ሌላም አካፍሏል። የእሱነቱ የብቻው መገለጫ የሆኑትን ሁሉን አዋቂነት ፣ በሁሉ ቦታ መገኘትና ሁሉን መቻል አላካፈለም። ምክኒያቱም የማያጋራው የብቻው ባህሪው ነው። የሚያካፍለው ደግሞም የማያካፍለው ባህሪ መኖሩ የባህሪው ውበት ያሳያል። ማካፈሉ ህብረት ማረግ የሚችል የሚወደድ መሆኑን አለማካፈሉም ልዩነት ልዩ የሆነ ረቂቅ አይደረሴ እንደሆነ ያሳያል።

የእግዚአብሔር ባህሪ ማወቅ የማንነቱ ውበት ለመረዳት፣ መፀሃፍ ቅዱሳችን የተገለጠውን እግዚአብሔርን በትክክል ለመረዳት ፣ ትክክለኛ አምልኮ እንዲኖረን ፣ እግዚአብሔር የመፍራትና የማክበር ምልልስ እንዲኖረን ፣ ወደነው እንድንኖርና እንድንገዛ ያደርጋል ።

@cgfsd
8
🔥 1
Пост от 28.01.2026 15:16
411
0
0
ውይይት-ሽመልስ እና ዳዊት...
ዴቭ ይመልሳል። "...እኔ ምን ላድርግ፣ እግዚአብሔርን በክርስቶስ ሳየው፣ ደግ፣ ርኅሩኅና ትኁት ነው፣ ዞር ብዬ በምድር የሚሆነውን ስመለከት ደግሞ ክፉ፣ ጨካኝና አምባገነን ይሆንብኛል። ...ኢየሱስ ለኃጢአቴ በከፈለው መሥዋዕትነት ልቤ ይነካል፤ ሆኖም በዚህ አመስግኜ፣ ከቤቴ ስወጣ የማየው... መከራና ግፍ ...እርሱ ሳይፈቅድ የመጣ እንዳልሆነ ስለማስብ ኢ-ፍትሃዊነቱ ...ያናድደኛል። የእኔ እምነት በተቃርኖ የተሞላ ነው። ...ከዚህ ጥያቄ ባርፍ ደሰ ይለኛል፤ አእምሮዬ ግን እሺ አይለኝም .."። ሽሜ ግን ይለዋል። "እግዚአብሔር መርምረን የምደርስበት "ጥያቄ" ሳይሆን፣ ተረድተን የማንጨርሰው "ፍቅር" ነው። እንዳንከፋ፣ አቅኚ አይጥፋ።

✍️ አለማየሁ ማም
11
👏 1
Пост от 27.01.2026 12:07
407
0
1
የክርስቶስ መወለድ አምላክነቱ አላስተውም ፤ ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ (Godman ) ነው ። የክርስቶስ ማረግ ሰውነቱን አላስተወውም ፤ ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ ነው ። ማንነት አይቀየርም !
15
Смотреть все посты