Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
730
334
3
0
7.3K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 424
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
237
ER
Общий
13.62%
Суточный
9.2%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 730 постов
Смотреть все посты
Пост от 16.03.2026 11:54
155
0
3
(ይህም ቃጠሎ ነው!)


መጋቢ ሰለሞን አበበ ገብረመድህን እንዲህ ይላሉ "ወንጌል በተነካ ጊዜ ካላመመን ያ ወንጌል የኛ አይደለም ። በተነካ ጊዜ የማይቆረቁረን እውነት የኛ እውነት አልሆነም። ይሔ ወንጌል የምንሰብከው ብቻ ሳይሆን በተነካ ጊዜ የምንቆምለት ነው" ። መጋቢው ትክክለኛ ሀሳብ ያነሱት ። መንፈሳዊ ግለት መቃጠል የፀሎትና የአምልኮ ጊዜ ላይ ብቻ አይገደብም ። ወንጌል ሲበላሽ ሲበረዝ መቃጠል መንፈሳዊ ቃጠሎ ነው ። ጌታችንም ኢየሱስ ያለው ይህን ነው " የቤትህ ቅናት ይበላኛል " ። በመንፈስ መቃጠል ሁለገብ ነው ። ወንጌል ሲበላሽና ሲያጣመም መታመም  ወንጌሉን የመወደድ ምልክት ነው ።

ሰሞኑን የሐዋሪያት ቤተክርስቲያን ወይም በስፋት ስንጠራቸው ኦንሊ ጂሰስ የተባሉት  ዋራ በተባለ ስፍራ ትልቅ ኮንፈራስ አድርገዋል ። ቤተ እምነቱ እንደሚታወቀው በስላሴ የማያምን ነው ። በአለም ላይ ካለው ኦንሊ ጂሰስ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ያለው ። ዶክተር ተስፋዬ ሮቤሌ ይፋ ባደረጉ ጥናታቸው በየወሩ 5000 ሰው ከወንጌል አማኝ ወደ ኦንሊ ጂሰስ ይፈልሳል ።አስደንጋጭ ቁጥር ነው ፤ ይሔን አለመደንገጥ የጤና አይደለም ። ሰሞኑን የዋራ ኮንፈራንስ ቤተ እምነቱ ይፋ እንዳደረገው 12,296 ሰዎች የኦንሊ ጂሰስ እምነት አምኖ እንደተጠመቀ ተናግረዋል ።  ይህ የሚያሳየው በምን ያህል እንቅስቃሴያቸው በንቃት እያደረጉት እንዳለ መረዳት ይቻላል ።

ትልቅ የቤት ስራ አለብን እውነተኛ ያልሆነው ወንጌል ያውም የእምነታችን ምንጭ የሆነው የስላሴ አስተምሮን የማያምን ቤተ እምነት በእውነተኛው ወንጌል እንቅፋት ሁኖ ተነስቷል  ። በዚህ ጊዜ መንፈሳዊ ቃጠሎ ያስፈልጋል ስለ እውነተኛው ወንጌል ደግሞ ከበሰለ በእውቀት ከዳበረ እንቅስቃሴ ጋር ! እንደ ቤተክርስቲያን መሰረታዊ እምነት መማር አለብን ። የመሰረታዊ እምነት ትምህርቶችን ደህንነትና ደቀ መዝሙር ስንማር ብቻ ጨርሰናቸው ማለፍ የለብንም  ። መሰረታዊ እምነት የሁልጊዜ ነው ። የእሁድ መድረኮቻችን ፣ የተከታታይ ትምህርቶቻን ፣ ኮንፈረሶቻችን ፣ የአመት እቅዶቻችን ውስጥ ሊገቡ አስፈላጊ ነው ። ሁሌ የምንጓጓለት የምንጠብቀው ተሃድሶ የዚህን አይነት መንፈሳዊ ቃጠሎ ሊጨምር ይገባል ።


@cgfsd
🔥 9
3
😢 2
Пост от 14.03.2026 13:49
223
0
2
(ውብ ፀጋ )



አምላክ እግዚአብሔር የፀጋ ሁሉ አምላክ ባለጠጋ ነው ። ለባለጠጋነቱ ወደር ሆነ ስፍር የሌለው ። የባለጠግነቱን ልክ ታላቅ ነው ከማለት ውጭ ምንም ማብራሪያ ሆነ መለኪያ አይገኝለትም ። ለዚህ አንዱ ማሳያ የፀጋው ባለጠግነት ነው ። ፀጋ ስጦታ ነው ። ካሪስ የሚለው የፀጋ ቃል ሲተረጎም በውስጡ  ከእግዚአብሔር የሚሰጥ ቸርነት ፣ ፍቅር ፣ ምህረት ፣ ሞገስ እንደማለት ነው ።

የእግዚአብሔር ፀጋ በአዲስ ኪዳን ብቅ ያለ አዲስ ክስተት አይደለም ። በብሉይ ኪዳን በብዙ መንገድ ሲታይ ሲገለጠ ነበር ። በብሉይ በአንድ ስፍራ፣ ምህረት ፣ ሞገስ ፣ ፍቅር እየተባለ የተጠሩ ቃላት በአዲስ ኪዳን ፀጋ ብለን የምንጠራው ነገሮች ይወክላሉ ። በወፍ በረር ከብሉይ ኪዳን ፀጋ ትንሽ እንመልከት ። እግዚአብሔር ፍጥረት ከመፍጠሩ ጀምሮ ፀጋውን ለፍጥረቱ ሲያድል ሲምበሸብሽ ነበር ። እግዚአብሔር ፍጥረት ካጎናፀፈው ውበት ጀርባ ፀጋ አለ ። ፍጥረት ሲንከባከብና ሲጠብቅ ፀጋው እየተገለጠ ነው ።  ሰው በእግዚአብሔር መልክና አምሳል ተፈጥሮ ፍጥረትን እንዲገዛና ሲያደርገው የእግዚአብሔር ወኪል በመሆነ የፀጋ ገዢ አደረገው ባላደራ ሆነ ። እግዚአብሔር ግን የባህሪ ገዢ ምክኒያቱም ሁሉ ለእሱ ይገባል ፈጣሪ ነው ። ሰው ግን በአደራ በእግዚአብሔር ስጦታ በፀጋው ባላደራው ገዢ ሆነ እዚህም ላይ የእግዚአብሔር ፀጋ ያለ ልክ ይታያል ።

ሰው ሲወድቅ አሁን ያ የእግዚአብሔር ፍቅር ፣ ምህረትና ይቅርታ ለአዳም መጣ ራቆቱን በኤደን ገነት ሸፈነለት ። ለኖህ ሞገስ ሆነው ፀጋው ። ለእስራኤል ህዝብ በኪዳን ውስጥ ያለ ርህራሄ ፣ የአስፈሪ ህዝብነት ሞገስ ሆናቸው ። ብሉይ ኪዳን የሚታዩት ሞገስ ፣ ምህረት ፣ ፍቅር በአዲስ ኪዳን ፀጋ ብለን የምንረዳቸው ናቸው ። እግዚአብሔር በብሉይ ፀጋው ሲሰጥ ነበር ፀጋው ውስጥ ስስት የለም ።

በአዲሱ ኪዳን ደግሞ ሀጢያት የሚያስክደው ፀጋ ተገለጠ (ቲቶ 2:11) ። ብርቱ ፀጋ ቀድሞም ነበር ነገር ግን በግልጠት መጣ። የአዲሱ ኪዳን ፀጋ መገለጥ ከብሉይ ኪዳኑ ለየት የሚያረገው በክርስቶስ ቤዛነት ስራ ይፋ መሆኑ ነው ። ድነት በክርስቶስ ስራ በኩል ስጦታ ሆነ ለሁሉ ተሰጠ ። የመኖር አቅም ሆነ በክርስቶስ የሰማይ ሊቀካህነት ስራ ምክኒያት በእየለት ህይወታችን ውስጥ በዛ ። ወደ እግዚአብሔር በመግባታችን ወደ ፀጋ መግባት ተባለልን (ሮሜ5:2) ፣ በፊቱ በድፍረት እንድንመላለስ ስንደክመን እገዛን እንድናገኝ በክርስቶስ የተጠጋነው ዙፋን የፀጋ ዙፋን ብሎ ጠራል (ዕብ 4:15-16) ። ቀድሞውን በብሉይ እግዚአብሔር ፍቅር ፣ ምህረቱን ፣ ሞገሱን የገለጠበት ፀጋ ደግሞ በአዲሱ ኪዳን በኢየሱስ ምክኒያት የበለጠ እንድናጣጥመው ሁሌ እንድናገኘው በልጁ ምክኒያት የበለጠ አፈሰሰልን ። ፀጋው ምነኛ ግሩም ! እንዴት ታላቅ ነው!


@cgfsd
9
👍 1
Пост от 07.03.2026 07:30
222
0
1
የአዲሱ ኪዳን የአምልኮ ትርጉም በዕብራዊያን መልዕክት ውስጥ አምልኮን " ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ከመግባት " ጋር ያገናኘዋል ። ክርስቶስ እንደ ሰማያዊ ሊቀ-ካህን መጋረጃውን ቀዶ መንገድ ስከፈተልን ፣ አማኞች በድፍረት ወደ ፀጋው ዙፋን መቅረብ እንደምንችል ያስተምረናል(ዕብ4:16)። ይህም እኛ አማኞች አምልኮን ከስርአት ባለፈ በክርስቶስ በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ወደሚደረግ ጥልቅና የግል ግንኙነት እንድንመጣ ይጋብዘናል።

@cgfsd
8
🔥 3
Пост от 06.03.2026 10:33
273
0
2
ክርስቶስ የእግዚአብሔር ክብር ነፀብራቅ ነው (ዕብ1:3) ። ፀሐይ ካለ ብርሃን ማሰብ እንደማይቻል ሁሉ ፣ እግዚአብሔር አብንም ያለ ወልድ ማወቅ አይቻልም ። ብርሃኑ ከፀሐዩ ጋር አንድ እንደሆነ ፣ ወልድም ከአብ ጋር በመለኮት አንድ ነው ።

@cgfsd
14
👍 3
Пост от 06.03.2026 07:10
298
0
0
(ታላቁ መገለጥ)


መገለጥ የክርስትና ጉልበት ነው ። እግዚአብሔር ራሱን በተደጋጋሚ ገልጧል ። በመፀሃፍ ቅዱስ ውስጥ ከታሪክ ወደ ታሪክ ፤ ከዘመን ወደ ዘመን በአለፍን ቁጥር እግዚአብሔር ራሱን እየገለጠ እንመለከተዋለን ። መገለጥ በእግዚአብሔር እና እኛ መሃል ለሚኖረው በመተዋወቅ ፣ መገዛት ፣ አምልኮ እጅግ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ነው ። የእግዚአብሔር ታላቅነት ፣ ረቂቅ መሆን በፍጥረት በሰው አቅም መታወቅ ፣ መረዳት ፣ መገንዘብ የማይቻል በመሆኑ እግዚአብሔር ራሱን ሊገልጥል ግድ ይላል ።

መገለጥ አስፈላጊ የሆነው እግዚአብሔርን ከራሱ ካልሆነ በትክክል ልናውቀው ስለማንችል ነው ። መገለጥ ውስጥ የእግዚአብሔር ርህራሄ ፣ ምህረት ፣ አፍቃሪነት ይታያል ፤ ምክኒያቱም እግዚአብሔር ቢራራ ነው ራሱን የሚገልጠው ቢወድ ነው ራሱን ይሄው ብሎ የሚገልጠው ። እግዚአብሔር ራሱን በብዙ ሁኔታ ገልጧል ። ፍጥረት ሲፈጥር በፍጥረቱ ውበት ውስጥ ፈጣሪ እንደሆነ ገልጧል(መዝ19:1) ፤ እኛን ሲፈጥር በውስጣችን ህሊና በማስቀመጥ ህሊናችን ስለ እሱ ምስክር ሁኗል (ሮሜ 2) ፣ ለእስራኤል ህዝብ ጋር ኪዳን በመግባት እየመገበ ፣ እየተንከባከባቸው ፣ በህጉ ፣ በነቢያት ፣ በመቅደሱ  በብዙ እልፍ መንገዶች መንገዱን  እየተናገረ እያስተማረ ራሱን ገለጠ ። 
  
ታላቁ መገለጥ ከሁሉ የሚልቀው መገለጥ ግን ራሱን በልጁ የገለጠበት መገለጥ ነው(ዕብ1:1-3) ። እግዚአብሔር በጊዜ ሂደት ውስጥ ራሱን በብዙ መንገድ ቢገልጥም እሱን ለመግለጥ ሙሉ አቅም ያለው መገለጥ የልጁ ኢየሱስ መገለጥ ነው ። ይሔው ነው ታላቁ መገለጥ ። ኢየሱስ ሰው ሲሆን ሰው ለማዳን ፣ ለሰው ለመሞት ቢመጣም ደግሞ በዚህ ውስጥ ቀዳሚ አላማው በይበልጥ ግልፅ የሆነልን ነገር የአምላክ እግዚአብሔር ማንነት ሊገልጥል ነበር ።  ክርስቶስ ኢየሱስ በስላሴ መካከል የመገለጥ ማዕከል ነው (Gorden fee)። የመገለጥ ወኪል ከሆነ አብን የተረዳንበት ፣ መንፈስ ቅዱስ በስሙ በማመን የተቀበልንበት ነው(ጳውሎስ ፈቃዱ) ። በኢየሱስ በኩል እግዚአብሔር ለፍጥረቱ በይበልጥ በማይደበቅ ፣ በማይሸፈን መልኩ ራሱን ግልፅ አርጓል ። አልታወቅም ብሎ የተቀመጠ አምላክ የለም እንዲታወቅ ራሱን በራሱ አብራራልን ። ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖረን ህብረት ውብ የሚሆነው ራሱን በገለጠልን መንገድ ህብረት ስናደርገው ነው ።

እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በተለያየ ጊዜና በልዩ ልዩ መንገድ በነቢያት በኩል ለአባቶቻችን ተናግሮ፣  በዚህ መጨረሻ ዘመን ግን ሁሉን ወራሽ ባደረገውና ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ ለእኛ ተናገረን።  እርሱ የእግዚአብሔር ክብር ነጸብራ ቅና የባሕርዩ ትክክለኛ ምሳሌ ሆኖ፣ በኀያል ቃሉ ሁሉን ደግፎ ይዞአል፤ የኀጢአት መንጻት ካስገኘ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ።
ዕብራውያን 1:1-3

@cgfsd
9
Пост от 05.03.2026 01:30
322
3
6
🔑እግዚአብሔርን መፈለግ

                    #SUBTITLE_2
                       በፅድቅ ኑሮ

በፊሊሞን ነጋ
Видео/гифка
11
🔥 3
Пост от 01.03.2026 07:31
413
0
2
ደቀ መዛሙርቱም በደስታና በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ።
ሐዋርያት ሥራ 13:52

በእግዚአብሔር መርካትና መደሰት የሚቻለው መንፈስ ቅዱስ በአማኞች መሃል የእግዚአብሔር ጥልቅ ፍቅር፣ ደስታ ሲሞላና ሲያፈስ የሚገኝ ነው።
15
Смотреть все посты