Каталог каналов Новое Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Мониторинг Новое Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
736
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 346
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
366
ER
Общий
25.33%
Суточный
13.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 736 постов
Смотреть все посты
Пост от 29.12.2025 14:09
87
0
2
(ለዘላለም ሰው ሆነ) ታላቁ አምላክ እግዚአብሔር ወልድ አምላክነቱን ሳይቀንስ ሰውነት ጨመረ ። ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ ሆነ ።  ክርስቶስ ሰው የሆነው እስከ ሞት ድረስ ብቻ አይደለም ፤ ከትንሳኤውም በኋላ ላይቀየር ለዘላለም ሰው ሆነ ። አምላክ -ሰው ፣ ፍፁም አምላክ ፤ ፍፁም ሰው !! ክርስቶስ ሰው የሆነው ለዘላለም ነው ። ይሔም አምላክ ሰውን መወደዱን የሚያሣይበት ዘላለማዊ የፍቅር ምስል ነው ።
14
🔥 3
Пост от 27.12.2025 22:31
208
0
3
(የሰለሞን ፀሎት ) ሰለሞን በመፀሃፍ ቅዱሳችን በንግስና የምናውቀው ሰው ነው ። የአባቱን ዳዊት የንግስና መስመር በእሱ በኩል አልፏል ። ከሰለሞን ጋር ሲነሳ ቀድመን የምናነሳቸው ንግስና ፣ ቤተ መቅደስ ፣ ጥበብ በጥቂቱ መጥቀስ ይቻላል ። ሰለሞን በተለያየ ጊዜ የፀለየው ፀሎት በመፀሃፍ ቅዱሳችን ላይ ተጠቅሷል ። ከእነዚህም አንደኛው የቤተ መቅደሱ ፀሎት ነው ። ቤተመቅደሱ በንጉስ ዳዊት በኩል ተበረከተ ስጦታ ፣ ከሊባኖስ በሚመጣ ማቴሪያል ፣ በእዕላፍ ወርቅ ለአርባ ስድስት አመታት በብዙ ልፋት የተሰራ የእስራኤል የኩራት ምንጭ የሆነ የእግዚአብሔር መቅደስ ነው ። ይሔ መቅደስ በዚህ ዘመን ቢሆን በርካታ  ቢሊዮን ሊያስወጣ እንደሚችል እጅግ ግሩም ስራ እንደሆነ ይታመናል ። ከብዙ አመታት ልፋት በኋላ ቤተ-መቅደሱ ሲመረቅ ሰለሞን በዚህ ዕለት እንደዚህ ፀለየ። "ከሕዝብህ ከእስራኤል ወገን ያልሆነ፣ ግን ከስምህ ታላቅነት የተነሣ ከሩቅ የመጣ የባዕድ አገር ሰው ቢኖር፣  ሰዎች ከሩቅ የሚመጡት ስለ ታላቁ ስምህ፣ ስለ ጠንካራዪቱ እጅህ፣ ስለ ተዘረጋችው ክንድህ ሰምተው ነውና፤ እንግዳው መጥቶ ወደዚህ ቤተ መቅደስ ቢጸልይ፣  አንተ በማደሪያህ በሰማይ ሆነህ ስማ፤ የጠየቀህንም ሁሉ ፈጽምለት፤ ይኸውም የምድር ሕዝቦች ሁሉ ስምህን ዐውቀው፣ ሕዝብህ እስራኤል አንተን እንደሚፈሩት ሁሉ እንዲፈሩህ፣ እኔ የሠራሁትም ይህ ቤት በስምህ መጠራቱን እንዲያውቁ ነው።" 1 ነገሥት 8:41-43 የሰለሞን ፀሎት አህዛብ ቢፀልዩ አዳምጣቸው እንደማለት ነው ። ሰለሞን በወርቅ ባሸበረቀው መቅደስ ውስጥ የስርአቱ ሁኔታ ብቻ አላሳሰበውም ይልቁንም የአህዛብ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የፀሎቱ ትኩረት ነበር ። በብሉይ ኪዳን ሆኖ ስለ አህዛብ መቅረብና መዳን አሳሰበው ። አህዛብም እግዚአብሔር እንዲያመልኩ ናፈቀ ። የሰለሞን ፀሎት የመንግስቱ ጉዳይ ነው ፣ የሰለሞን ፀሎት የእግዚአብሔር የልብ አጀንዳ ነው ።  ከሰለሞን ፀሎት ምን እንማር ይሁን ? @cgfsd
18
🔥 2
Пост от 26.12.2025 22:46
253
0
3
(ጥሬ ፀሎት) ጥሬ ፀሎት የሚለው ቃል ፍሊፕ ያንሲን የሚጠቀመው ቃል ነው ። ያልተቀባባ ፀሎት ፣ ያልተሸፋፈነ ፀሎት እንደማለት ነው ። እግዚአብሔር ጥሬ ፀሎት ይወዳል ።  ጥሬ ፀሎት የሆንነውን ነን የምንልበት ፣ ያልቻልነውን አልቻልንም የምንልበት  ንፁህ ያልተቀባባ ፀሎት ነው ። የፈሪሳዊ ፀሎትና የቀራጩ ፀሎት በግልፅ የምናየው አይነተኛ ፀሎት ነው (ሉቃስ 18) ። ፈሪሳዊ ቅብ ፀሎት ያለበት ይመስላል ፣ በፀሎቱ ውስጥ ይመፃደቃል ፣ ራሱን በትዕቢት ይወጥራል ፣ ራሱን ከቀራጮች ጋር ያወዳድራል ። ቀራጩ ደግሞ አይኑን ቀና ማድረግ ከብዶት ፤ ደረቱን እየደቃ በድያለው ማረኝ ይላል  ። በጌታ ኢየሱስ ፊት ቀራጩ የፀለየው ፀሎት ጥሬ ፀሎት ነው ። በእግዚአብሔር ፊት ያልተቀባባ ፀሎት ነው ። የፈሪሳዊ ደግሞ ቅብ ፀሎት ራስን ፅድቅ ማስቆጠር የንግግር ችሎት የሚታይበት ፀሎት ነው ። በእግዚአብሔር ፊት ስንሆን በእግዚአብሔር ፊት እንደሆንን ማወቅ አለብን ። እግዚአብሔር ፊት የሚደበቅ የሚሰወር ምንም ነገር የለም ። በፊቱ ስንቀርብ እሱን በእርግጥም ስለሚያየን ራሳችን አጋልጠን መሆን አለበት ። ጥሬ ፀሎት በእግዚአብሔር እጅ ላይ መዋረድ ነው ። ፀሎት ላይ ስሌት ሳይሆን የሚያዋጣው ፍሰት ነው የተሻለው ። በእግዚአብሔር ፊት ማስላት ሳይሆን በእግዚአብሔር ፊት መፍሰስ  ነው ትልቁ ጉዳይ ለዚህም ነው ያልተቀባባ ጥሬ ፀሎት ያስፈለገው ። @cgfsd
🔥 11
7
👍 1
Пост от 26.12.2025 18:17
275
1
1
Изображение
18
🔥 3
Пост от 24.12.2025 09:07
372
0
4
ከመስቀሉ ፊቱን የሚያዞር ሰው ከእግዚአብሔር ነው ፊቱን የሚያዞረው እግዚአብሔር የተገለጠው በዛ ስፍራ ስለሆነ ።         ጳውሎስ ፈቃዱ
🔥 18
10
👍 2
Пост от 23.12.2025 19:03
457
1
5
Видео/гифка
13
👍 2
Пост от 21.12.2025 22:59
497
0
5
(ሳለ-አይሰጥ ) ስጋ ተመጋቢ አልፎም አጥንት ወዳጅ የሆነ ሰው ስለ ሳለ-አይሰጥ በደንብ አድርጎ ያውቃል ። በሳለ-አይሰጥ አጥንት የማይማረር ተመጋቢ አይኖርም ። ይሔ አጥንት ስጋ ያለው ነው ፤ ሲታይ ደስ ይላል ፣ ብሉኝ ፣ ብሉኝ ያሰኛል ነገር ግን ለመብላት አይመችም ። ምንም እንኳን ስጋ ያለው ቢሆንም  ዙሪያ ያለው አጥንት ወጣ ገባ ያለ በመሆኑ ለመብላት አዳጋችና ከባድ ያረገዋል ። ስለዚህ ስጋ እያለው አይሰጥም በሚል ሀሳብ ይሔ አጥንት ሳለ-አይሰጥ የሚል ስያሜ ወጣለት ።  ስጋ እያለው አይሰጥም ! ሳለ-አይሰጥ ለመንፈሳዊ ህይወታችን ጥሩ ምሳሌ ሊሆን የሚችል ማሳያ ነው ። ጥሩ ነገር እያለን ፣ ፀጋ እያለን ፣ በጎ መንፈሳዊ ልምምዶች እያሉን ፤  ለሌላው ለማካፈል ፣ ለመቆረስ አለመመቸት የሳለ-አይሰጥ ምሳሌ ነው ። በጎ መንፈሳዊ ልምምድ ፣ ዕውቀት አለን ማለት ለሌላው የምንመች የምናካፍል ነን ማለት አይደለም ። ክርስቲያን የክርስቶስ ህይወትና ብርሃን እያለው ግን ለሌሎች የማይመች የባህሪ ችግር ካለበት ፤  ስጋ እያለው ለመብላት እንዳልተመቸው አጥንት ምሳሌ ይሆናል ። ክርስቲያን ነኝ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚቆረስ የሚበላ ህይወትና ባህሪ አለን? የሚለው የሁልጊዜ ጥያቄ ነው ። ከሳለ-አይሰጥ ጌታ ይጠብቀን ። @cgfsd
12
🔥 6
Смотреть все посты