Каталог каналов Новое Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Мониторинг Новое Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
736
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 346
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
370
ER
Общий
22.15%
Суточный
13.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 736 постов
Смотреть все посты
Пост от 27.12.2025 22:31
131
0
3
(የሰለሞን ፀሎት ) ሰለሞን በመፀሃፍ ቅዱሳችን በንግስና የምናውቀው ሰው ነው ። የአባቱን ዳዊት የንግስና መስመር በእሱ በኩል አልፏል ። ከሰለሞን ጋር ሲነሳ ቀድመን የምናነሳቸው ንግስና ፣ ቤተ መቅደስ ፣ ጥበብ በጥቂቱ መጥቀስ ይቻላል ። ሰለሞን በተለያየ ጊዜ የፀለየው ፀሎት በመፀሃፍ ቅዱሳችን ላይ ተጠቅሷል ። ከእነዚህም አንደኛው የቤተ መቅደሱ ፀሎት ነው ። ቤተመቅደሱ በንጉስ ዳዊት በኩል ተበረከተ ስጦታ ፣ ከሊባኖስ በሚመጣ ማቴሪያል ፣ በእዕላፍ ወርቅ ለአርባ ስድስት አመታት በብዙ ልፋት የተሰራ የእስራኤል የኩራት ምንጭ የሆነ የእግዚአብሔር መቅደስ ነው ። ይሔ መቅደስ በዚህ ዘመን ቢሆን በርካታ  ቢሊዮን ሊያስወጣ እንደሚችል እጅግ ግሩም ስራ እንደሆነ ይታመናል ። ከብዙ አመታት ልፋት በኋላ ቤተ-መቅደሱ ሲመረቅ ሰለሞን በዚህ ዕለት እንደዚህ ፀለየ። "ከሕዝብህ ከእስራኤል ወገን ያልሆነ፣ ግን ከስምህ ታላቅነት የተነሣ ከሩቅ የመጣ የባዕድ አገር ሰው ቢኖር፣  ሰዎች ከሩቅ የሚመጡት ስለ ታላቁ ስምህ፣ ስለ ጠንካራዪቱ እጅህ፣ ስለ ተዘረጋችው ክንድህ ሰምተው ነውና፤ እንግዳው መጥቶ ወደዚህ ቤተ መቅደስ ቢጸልይ፣  አንተ በማደሪያህ በሰማይ ሆነህ ስማ፤ የጠየቀህንም ሁሉ ፈጽምለት፤ ይኸውም የምድር ሕዝቦች ሁሉ ስምህን ዐውቀው፣ ሕዝብህ እስራኤል አንተን እንደሚፈሩት ሁሉ እንዲፈሩህ፣ እኔ የሠራሁትም ይህ ቤት በስምህ መጠራቱን እንዲያውቁ ነው።" 1 ነገሥት 8:41-43 የሰለሞን ፀሎት አህዛብ ቢፀልዩ አዳምጣቸው እንደማለት ነው ። ሰለሞን በወርቅ ባሸበረቀው መቅደስ ውስጥ የስርአቱ ሁኔታ ብቻ አላሳሰበውም ይልቁንም የአህዛብ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የፀሎቱ ትኩረት ነበር ። በብሉይ ኪዳን ሆኖ ስለ አህዛብ መቅረብና መዳን አሳሰበው ። አህዛብም እግዚአብሔር እንዲያመልኩ ናፈቀ ። የሰለሞን ፀሎት የመንግስቱ ጉዳይ ነው ፣ የሰለሞን ፀሎት የእግዚአብሔር የልብ አጀንዳ ነው ።  ከሰለሞን ፀሎት ምን እንማር ይሁን ? @cgfsd
14
🔥 2
Пост от 26.12.2025 22:46
218
0
3
(ጥሬ ፀሎት) ጥሬ ፀሎት የሚለው ቃል ፍሊፕ ያንሲን የሚጠቀመው ቃል ነው ። ያልተቀባባ ፀሎት ፣ ያልተሸፋፈነ ፀሎት እንደማለት ነው ። እግዚአብሔር ጥሬ ፀሎት ይወዳል ።  ጥሬ ፀሎት የሆንነውን ነን የምንልበት ፣ ያልቻልነውን አልቻልንም የምንልበት  ንፁህ ያልተቀባባ ፀሎት ነው ። የፈሪሳዊ ፀሎትና የቀራጩ ፀሎት በግልፅ የምናየው አይነተኛ ፀሎት ነው (ሉቃስ 18) ። ፈሪሳዊ ቅብ ፀሎት ያለበት ይመስላል ፣ በፀሎቱ ውስጥ ይመፃደቃል ፣ ራሱን በትዕቢት ይወጥራል ፣ ራሱን ከቀራጮች ጋር ያወዳድራል ። ቀራጩ ደግሞ አይኑን ቀና ማድረግ ከብዶት ፤ ደረቱን እየደቃ በድያለው ማረኝ ይላል  ። በጌታ ኢየሱስ ፊት ቀራጩ የፀለየው ፀሎት ጥሬ ፀሎት ነው ። በእግዚአብሔር ፊት ያልተቀባባ ፀሎት ነው ። የፈሪሳዊ ደግሞ ቅብ ፀሎት ራስን ፅድቅ ማስቆጠር የንግግር ችሎት የሚታይበት ፀሎት ነው ። በእግዚአብሔር ፊት ስንሆን በእግዚአብሔር ፊት እንደሆንን ማወቅ አለብን ። እግዚአብሔር ፊት የሚደበቅ የሚሰወር ምንም ነገር የለም ። በፊቱ ስንቀርብ እሱን በእርግጥም ስለሚያየን ራሳችን አጋልጠን መሆን አለበት ። ጥሬ ፀሎት በእግዚአብሔር እጅ ላይ መዋረድ ነው ። ፀሎት ላይ ስሌት ሳይሆን የሚያዋጣው ፍሰት ነው የተሻለው ። በእግዚአብሔር ፊት ማስላት ሳይሆን በእግዚአብሔር ፊት መፍሰስ  ነው ትልቁ ጉዳይ ለዚህም ነው ያልተቀባባ ጥሬ ፀሎት ያስፈለገው ። @cgfsd
🔥 11
7
👍 1
Пост от 26.12.2025 18:17
248
1
1
Изображение
17
🔥 3
Пост от 24.12.2025 09:07
339
0
4
ከመስቀሉ ፊቱን የሚያዞር ሰው ከእግዚአብሔር ነው ፊቱን የሚያዞረው እግዚአብሔር የተገለጠው በዛ ስፍራ ስለሆነ ።         ጳውሎስ ፈቃዱ
🔥 18
10
👍 2
Пост от 23.12.2025 19:03
429
1
5
Видео/гифка
13
👍 2
Пост от 21.12.2025 22:59
489
0
5
(ሳለ-አይሰጥ ) ስጋ ተመጋቢ አልፎም አጥንት ወዳጅ የሆነ ሰው ስለ ሳለ-አይሰጥ በደንብ አድርጎ ያውቃል ። በሳለ-አይሰጥ አጥንት የማይማረር ተመጋቢ አይኖርም ። ይሔ አጥንት ስጋ ያለው ነው ፤ ሲታይ ደስ ይላል ፣ ብሉኝ ፣ ብሉኝ ያሰኛል ነገር ግን ለመብላት አይመችም ። ምንም እንኳን ስጋ ያለው ቢሆንም  ዙሪያ ያለው አጥንት ወጣ ገባ ያለ በመሆኑ ለመብላት አዳጋችና ከባድ ያረገዋል ። ስለዚህ ስጋ እያለው አይሰጥም በሚል ሀሳብ ይሔ አጥንት ሳለ-አይሰጥ የሚል ስያሜ ወጣለት ።  ስጋ እያለው አይሰጥም ! ሳለ-አይሰጥ ለመንፈሳዊ ህይወታችን ጥሩ ምሳሌ ሊሆን የሚችል ማሳያ ነው ። ጥሩ ነገር እያለን ፣ ፀጋ እያለን ፣ በጎ መንፈሳዊ ልምምዶች እያሉን ፤  ለሌላው ለማካፈል ፣ ለመቆረስ አለመመቸት የሳለ-አይሰጥ ምሳሌ ነው ። በጎ መንፈሳዊ ልምምድ ፣ ዕውቀት አለን ማለት ለሌላው የምንመች የምናካፍል ነን ማለት አይደለም ። ክርስቲያን የክርስቶስ ህይወትና ብርሃን እያለው ግን ለሌሎች የማይመች የባህሪ ችግር ካለበት ፤  ስጋ እያለው ለመብላት እንዳልተመቸው አጥንት ምሳሌ ይሆናል ። ክርስቲያን ነኝ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የሚቆረስ የሚበላ ህይወትና ባህሪ አለን? የሚለው የሁልጊዜ ጥያቄ ነው ። ከሳለ-አይሰጥ ጌታ ይጠብቀን ። @cgfsd
12
🔥 6
Пост от 21.12.2025 08:02
424
0
2
(ሶስቱ ዘፀአት ) ዘፀአት ትክክለኛ ትርጓሜው መውጣት ማለት ነው ። ይሔን ሀሳብ በይበልጥ የምናውቀው እስራኤላዊያን ከ430 ሰላሳ አመት ከግብፅ ባርነት የወጡትን መውጣት ያሳያል ። ሶስት ዘፀአት በመፀሃፍ ቅዱሳችን እንደነበረ በግልፅ እንመለከታለን ። የመጀመሪያው በግብፅ የነበረው ዘፀአት ነው ፣ ሁለተኛው በባቢሎን የታየው ዘፀአት ፣ ሶስተኛ ደግሞ በኢየሩሳሌም የሆነው ታላቁ ዘፀአት ነው ። የግብፅ ዘፀአት(መውጣት) እስራኤላዊያን እየደረሰባቸው ከነበረው አስከፊ ባርነት የወጡት መውጣት ነው ። በዚህ ዘፀአት ዋነኛ አላማው ከባርነት ህዝቡን ማላቀቅ ይሁን እንጂ  መጨረሻ ዋነኛው የሆነው በእስራኤል አምላክ እንዳለ በግብፅም ሆነ በቀሩት የአህዛብ መንግስታት መካከል የእግዚአብሔር ስም ታወቀ ፤ ስሙ ከፍ አለ ። የፀና ክንዱ ፤ የበረታች እጁ በሁሉ ታየ ። በዚህ መውጣት ዘፀአት ውስጥ በርካታ ተአምራት ተደርገዋል ከተአምራቱ ጀርባ ያለው ከግብፅ አማልክት በላይ እግዚአብሔር አምላክ እንደሆነ ታየበት ። በግብፅ የተደረጉት አስሩም መቅሰፍትና ተአምራት በግብፅ እንደ አምላክ ይቆጠሩ ነበር ። ለምሳሌ ጓጉንቸር ይመለካል ፣ ውሃ ወደ ደም ሲቀየር ውሃ ይመለክ ነበር ፣ በኩር ሲሞት በኩር ይመለክ ነበር ። በግብፅ ዘፀአት የተደረገው ተአምራት እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ እንደሆነ ስሙ የገነነበት ዘፀአት ነበር ። ከባርነት ተላቀው ባደረጉ የአርባ አመት ጉዞአቸው ውስጥ የእግዚአብሔር ያልተቋረጠ አቅርቦትና መጋቢነት ነበር ። መና ይመገባሉ ፣ የማያልቅ ልብስ ይለብሳሉ ። እግዚአብሔር ከበረበት ! ሁለተኛ ዘፀአት ደግሞ በባቢሎን የነበረው ዘፀአት ነው ። ህዝበ እስራኤል ወደ ባቢሎን ለሰባ አመታት በግዞት ተወስደዋል ።  በባቢሎን ቆይታቸው የኩራት የክብር መገለጫ የሆነው የኢየሩሳሌሙ መቅደስ ፈረሰ ፣ ህዝቡ ተሰደበ፣ የከተማው በር ቅጥሮች ፈረሱ ፣ ከተማው ወደመ ። በባቢሎን ምርኮ ሁነው ህጉን መማር ናፈቃቸው  ። እግዚአብሔር 70 አመቱ አልቆ በባቢሎን ፈንታ ፋርስ ሲነግስ ። እስራኤላዊያን መመለስ ጀመሩ ። የባብሊሎን ዘፀአት መንፈሳዊ ተሃድሶ ያለው ነበር ። ይሔ ዘፀአት የእግዚአብሔር ፊት ለመፈለግ የመጡበት ነበር ፣ መቅደሱን ለመስራት የተመለሱበት በዓላማ የወጡበት ዘፀአት ነበር ። በባቢሎን ዘፀአት ምንም እንኳን መከራ ቢኖረውም እግዚአብሔር ስሙ በእነ ዳንኤል የከረበት የእስራኤል አምላክ ተብሎ ስሙ የተጠራበት ነበር ።ከዚህ ዘፀአት ጀርባ የእግዚአብሔር ስም የከበረበት ነበር ። ሶስተኛው ዘፀአት በመፀሃፍ ቅዱሳችን የተገለጠው የኢየሩሳሌሙ አዲሱ ዘፀአት ወይም መውጣት ነው ። ይሔ መውጣት በክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ የተፈፀመ መውጣት ነው ። ሰው ተረግጦ ከተያዘበት የሀጢያት ፣ የሞት ፣ የሰይጣን ባረነት በክርስቶስ ህይወት ፣ ሞትና ትንሳኤ ሊወጣ ዘፀአት ሊሆን ተችሏል ። በዚህ ምክኒያት በዚሁም ዘፀአት መውጣት ውስጥ እግዚአብሔር ከበረ ሰውን የገዛውን የሀጢያትና የሞት ሰንሰለት ስለተበጠሰ እግዚአብሔ ስለ ፀጋው ክብር ከበረ ። ዘፀአት መውጣት  ለምን ሆነ  ? ለምን ?ወጡ ሲባል  በአላማ ተለይተው ለእግዚአብሔር ህዝብ ለመሆን ወጥተዋል (ዘፀአት) ሁኗል ይባላል ። ይሔ በክርስቶስ የተፈፀመው አዲሱና ታላቁ ዘፀአት አስደናቂዊ ነው ። ሉቃስ 9 ላይ እንደምናገኘው ታሪክ በኢየሱስ የተፈፀመው ዘፀአት ታላቅ መሆኑን እናያለን ። በግብፅ ዘፀአት የሚታወቀው ሙሴ ፣ በነብይነት የሚታወቀው ኤሊያስ በደብረታቦር ተራራ ኢየሱስ ጋር ሲገናኙ ከብዙ አመት በኋላ ቢሆንም  የተገለጡት ከኢየሱስ ጋር ያደረጉት ንግግር በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው መውጣት(ዘፀአት) ነው ፤ እንጂ ስለ ግብፁ ዘፀአት ትንታኔ አልሰጡም ። ከሁሉ እንደሚበልጥ ምስክር ናቸው ። በዚህ ዘፀአት የእግዚአብሔር ህዝብ መሆንን፣ ዘላለማዊ ተስፋ ፣ የመዳን ብድራት ታይቶበታል ። በክርስቶስ መውለድ ፣ ሞትና ትንሳኤ ያየነው ዘፀአት ታላቁ ዘፀአት (The Great Exodus )ነው ። በታላቁ ዘፀአት ታላቁ እግዚአብሔር ታላቅ እንደሆነ ታየ ። @cgfsd
10
👏 3
Смотреть все посты