Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
709
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 413
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
364
ER
Общий
15.82%
Суточный
13.7%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 709 постов
Смотреть все посты
Пост от 27.01.2026 00:31
22
0
1
ጌታ በህይወቴ እሳትህ ጣል  በአገልግሎቴ እሳትህን ጣል በአረማመዴ እሳትህን ጣል 🔥   🎶 የቀድሞ መዘምራን
7
Пост от 26.01.2026 22:33
93
0
0
እግዚአብሔር ፍጥረት ከፈጠረ በኋላ መጋቢነቱን አሳይቷል ። ፍጥረት ፈጥሮ ብቻ አልተወውም ። ፈላስፎች እንዳሉት " እግዚአብሔር ፍጥረት ፈጥሮ ትቶት ሂዷል " ።  እግዚአብሔር ፈጥሮ ትቶ አልሄደም ለፍጥረቱ መጋቢ ነበር ፤ ለምሳሌ ወቅቶች ወቅታቸውን ጠብቀው መፈራረቃቸው ፣ እንስሳ የህይወት ዑደት ጠብቀው መኖራቸው ምግባቸውን ማግኘታቸው መጥቀስ ይቻላል። እግዚአብሔር ፍጥረቱን እየመገበ ያስኬዳል፣ ይንከባከባል ለፍጥረቱ ፈጣሪውም እንደሆነ ሁሉ መጋቢውም ነው ። የመዳንችንም ታሪክ ይሔው መልክ ይታይበታል ። ተዋጅተን ብቻ አልተወንም ምልጃ በሰማይ መቀጠሉ ፈጥሮ መጋቢ እንደሆነው ሁሉ ፤ ዋጅቶም ማላጅ ሆነ   ። ፍጥረት ከተፈጠረ በኋላ መጋቢው እንደሆነው ፤ ከዋጀ በኋላ ምልጃም እንክብካቤውንና አብሮ እንዳለ ማሳያው ነው ። እግዚአብሔር መጋቢነቱ የፍጥረት ፈጣሪ ለመሆኑና ለፍጥረቱ ያለውን ያንፀባረቀበት ነው ። ምልጃም ዘላለማዊ ፍቅርና ርህራሄ በመዋጀቱ በኩል የተገለጠበት ድንቅ እውነት  ነው ። @cgfsd
9
Пост от 23.01.2026 13:22
269
0
2
(የአጋፋሪው ስጋት) አጋፋሪው እንደሻው የታዋቂው ደራሲ የጋሽ ስብሃት ገብረእግዚአብሔር የልቦለድ ስራ ላይ ያለ አንድ ገፀባህሪ ናቸው ። አጋፋሪው እንደሻው ጨዋታ የሚመስል ነገር በገፀባህሪው ውስጥ ቢታይም የሰውን አንዳንድ ሁኔታዎች ቁልጭ አድርገው ይገልፃሉ ። አጋፋሪው እንደሻው በልቦለዱ ውስጥ አብዝተው ሞትን ይፈራሉ ። የልቦለዱ ታሪክ አጋፋሪው ሞትን ሽሽት ከሰፈር ፣ሰፈር ከመንደር መንደር ስንቃቸውን ጭነው እየተዘዋወሩ ነው ። በአካባቢው የለቅሶ ድምፅ ፣ የተጣለ ድንኳን ፣ መርዶ ፣ የታመመ ካለ አካባቢውን ለቀው ይወጣሉ ። ወደ አንድ አካባቢ ሲገቡ በመጀመሪያ መንደርተኞቹን የሚጠይቁት ጥያቄ " እዚህ ሰፈር የሞተ አለ ? መርዶ አለ? የታመመ አለ ? የሚለው ይሆናል ። አዎ ከተባሉ ፈረሳቸውን እየጋለቡ አልፈው ይሄዳሉ ። አንዱ ገፀባህሪ አዎ ቢሆን መልሳችን ብሎ ሲጠይቃቸው እየሄዳለሁ ካልሆነ ከመንደር ውጭ እቀመጣለሁ እያሉ ይመልሳሉ ። በ66 አመታቸው ከወዳጃቸው ጋር እየጠጡ በድንገት ትንታ ይዛቸዋል ። በዛ መሃል ሞት የማይቀር መሆኑን ሲረዱ ይሔ ሁሉ ሽሽት በከንቱ እያለ ያጉረመርማሉ ። አጋፋሪው እንደሻው የሞት ፍርሃታቸውን በልቦለዱ ውስጥ የገሃዱን አለም ፍርሃት ያሳየኑናል ። የአጋፋሪው እንደሻው ስጋትና ፍርሃት የሰው ልጆች ፍርሃት ነው ። ምንም እንኳን እንደ አጋፋሪው አይነት ከመንደር መንደር የሚያንከራትት ፍርሃት ባይሆንም ለሞት እንግዳ የሆነ ስሜት አለን ። ለዚህም ነው ሞት የማይለመድ ዜናነው የሚባለው ። ሞት  የሰውን ልጅ ጠላት ነው ። መፀሃፍ ቅዱስ በሮሜ 5 እንደሚነግረን ሞት ነግሶ ነበር ይለናል ። ከሁሉ በላይ የሰውን ልጅ የሞት ፍርሃት እንዳለበት በራሱ መፀሃፍ ቅዱሳች ይናገራል ።     እንዲሁም በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ በሞት ፍርሀት ባርነት የታሰሩትን ነጻ እንዲያወጣ ነው። ዕብራውያን 2:15 የሰው ልጅ በጠቅላላ በሞት ፍርሃት እንደተያዘ የዕብራውያን ፀሃፊ ይነግረናል ። የሰው ልጅ ትልቁም ጠላቱ እሱ ነው ። የአጋፋሪው እንደሻው ገፀባህሪ ግነት ቢኖረው የሰውን ትልቁን ፈተና ፍርሃት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል ። ነገር ግን በሞት ፍርሃት ተቆራምተን ከመኖር ባለፈ መፀሃፍ ቅዱሳችን ሞት ድል የሚደረግበት መንገድ እንዳለን ይነግረናል ። እርሱም ትንሳኤ ይባላል ። የክርስቶስ ትንሳኤ አብረነው እንደምነነሳ ተስፋ የተሰነቀበት ድንቅ የክርስትና እውነት ነው ። የሞት ፍርሃት ሞት አይቀርላችሁም ለተባለለት የሰው ልጅ የክርስቶስ ትንሳኤ በአዲስ ትንሳኤ አካል ትነሳለችሁ በክርስቶስ ዳግም መምጣት ይፈፀምላችኋል  የሚል ፅኑም ተስፋ ያሰንቃል። @cgfsd
14
👍 1
Пост от 22.01.2026 22:03
309
0
2
"አንድ ሰው ባመጸብህ ግዜ ባትወድደው እኳን ቢያንስ ይቅርታን በጠየቀ ግዜ ፍቅርን አሳየው" ✍️ቅዱስ አውግስጢኖስ @cgfsd
22
👍 2
Пост от 22.01.2026 15:59
392
0
1
የእግዚአብሔር መንግስት ትርጓሜ ያለው ንጉስ ጋር ወይም ገዢው ጋር ነው ። kingdom የሚለው ቃል የሚገልፀው ንጉሱ ላይ ጥገኛ የሆነን የአገዛዝ ስርአት ነው ። ስለ እግዚአብሔር መንግስት ስናሳብ የንጉሱ ገዢነት ላይ ማተኮር ያለብን ። ሐዋሪያው ጳውሎስ በመልዕክቶቹ ውስጥ በጣም ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔር መንግስት የሚል ቃል አልተጠቀመም ። ይሔን ቃል ስላልተጠቀመ ስለእግዚአብሔር መንግስት አልፃፈም ማለት ግን አይደለም ። በይበልጥ እንደውም በመልዕክቶቹ ውስጥ ስለ እግዚአብሔር መንግስት ፅፏል ። የጳውሎስ ትኩረት የነበረው ገዥነቱ ላይ ስለነበር ። በተለይ ክርስቶስ ብዙ ቦታ "ጌታ" እያለ ፅፏል ። ጌታ ማለት ገዢነት የሚያሳይ ቃል ነው ። አብዝቶ ጌታ በማለት የእግዚአብሔን መንግስት አስተማረ ። ጳውሎስ የእግዚአብሔር መንግስት ኢየሱስ ጌታ ነው በማለት የመንግስቱን ጉዳይ የገዢነት ስርአቱን በግልፅ ከእነ አላማው አሳይቷል ። የእግዚአብሔር መንግስት የእግዚአብሔርን የገዢነት አገዛዝ ይጠቁማል ። @cgfsd
9
🥰 3
Пост от 17.01.2026 17:21
489
1
7
ለቁስሌ የሚሆን ዘይት በእጅህ አለ ያልጨመረ በእኔ  ስንቱን ቤት ያከመ ዛሬም ከእኔ ደርሶ አይቀንስ ጉልበቱ ፈሶ ያድነኛል ያደርገኛል ብርቱ 🎶
🔥 18
16
😢 5
🥰 3
Пост от 14.01.2026 16:47
412
0
1
(የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ 1)               - ዩሀንሰ ምዕራፍ 1 እና የመዋጀት ታሪክ                  (ክፍል 3) የዩሀንስ ወንጌል የመዋጀት ታሪክን (redemptive story) የሚያሳይ መፀሃፍ ነው ። የዩሀንስ ምዕራፍ አንድ አወቃቀር መፀሀፍ ቅዱስ የመዋጀት ታሪክ እንደሆነ ያሳየናል ። የመዋጀት ታሪክ ማለት ምን ማለት ነው ?  ይሔ ጥያቄ የመፀሀፍ ቅዱሳችን የጀርባ አጥንት የሆነ ጥያቄ ነው ። ምክኒያቱም የመዋጀት ታሪክ የመፀሃፍ ቅዱሳችን ግልፅ መልዕክቱ ነው ። የመዋጀት ታሪክ ማለት የእግዚአብሔር የማዳን ታሪክ ነው ፤ እግዚአብሔር ለፍጥረቱ ራሱን የገለጠበት የማዳንና ሰውን የራሱ የማድረግ ሂደት እርሱ የመዋጀት ታሪክ በመባል ይታወቃል ። የእግዚአብሔር የማዳን(የመዋጀት) ታሪክ አብዛኛውን ጊዜ በአዲስ ኪዳን መፀሃፍ ውስጥ የተገደበ ይመስለናል። ከአዲስ ኪዳንም ደግሞ በክርስቶስ የመስቀል ሞትና ትንሳኤ ላይ ያለ ብቻ እንደሆነ አንንዳንድ ቦታ ይታያል ። በእርግጥ መስቀሉና ትንሳኤው የመዋጀቱ ትልቁ መፈፀሚያ ስራዎች ናቸው ። ቢሆንም ግን የመዋጀት ታሪክ የመስቀሉና የትንሳኤው ገፅታ ብቻ አይደለም ። የሰው ልጅ ከወደቀበት ጊዜ አንስቶ እግዚአብሔር የመዋጀት ታሪክ ጉዞ ተስፋ በመስጠት ከኤደን ገነት ሲያጀምር እናያለን ። ያኔ ተስፋ ገባ በእስራኤል ውስጥ ስለ መዋጀቱ መንገድ ጠረጋ ነበር ። ብሉይ ኪዳን የሚነግረን ነገር ቢኖር እግዚአብሔር ከኤደን ገነት ጀምሮ በሰው ልጅ በፍጥረቱ መካከል የማዳን መንገድ ጀምሯል ። በኋላም በመስቀሉና ትንሳኤው ስራውን ወደ ፍፃሜ አምጥቷል ። ሁሉም የመፀሃፍ ቅዱሳችን ሀሳብ የመዋጀት ታሪክ ግባቸው ነው ። መፀሃፍ ቅዱስ የመዋጀት ታሪክ ነው ፣ የእግዚአብሔር ታሪክ የመዋጀት ታሪክ ነው ቢባል አሳማኝ ነው ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ የመዋጀት ታሪክ መስቀሉ ጋር ብቻ አያስቀረውም ። ምዕራፍ አንድ የሚያስገነዝበን የእግዚአብሔር የመዋጀት ታሪክ መስቀሉ ጋር ብቻ አልጀመረም ፤ ይሔን ስራ ቀድሞውን ጀምሯል በመስቀሉ የበለጠ ፈፀመው የሚል እይታ ያስገነዝበናል ። በዩሀንስ 1 የምናየው አምላክ የመዋጀት ታሪክ ስራን ለመፈፀም የሚተጋ አምላክ ነው ። ከፍጥረት በፊት ነበር (ዩሀ1:1)፣ ፍጥረትንም እሱ ፈጠረ(ዩሀ1:4)፣ በብሉይ ብርሃን ሆኖ እየመጣ ተገልጧል (ዩሀ1:9)፣ ሰው ሆኖ መጣ (ዩሀ1:14)፣ ለሞት የተዘጋጀ ሆነ (ዩሀ 1:29) ። ይሔ ሁሉ ትረካ የእግዚአብሔር መዋጀት ታሪክ በመስቀሉ ያልጀመረ በዚሁ ስራውን ተስፋ በመስጠት ፣ በማፅናት ፣ ሰው ሁኖ ማደስ በመጀመር ፣ በመስቀል ታልፎ ለመሰጠት በመዘጋጀት ስራው ይተርክልናል ። የእግዚአብሔር የማዳን ታሪክ ከጥንት የጀመረ እንደሆነ የዩሀንስ ወንጌል አንዱና ትልቁ ማሳያ ነው ። የመፀሃፍ ቅዱስ ሙሉ ዋና ትኩረት አቅጣጫ የመዋጀት ታሪክ በዩሀንስ አንድ ምዕራፍ ይንፀባረቃል ። @cgfsd
10
Смотреть все посты