Телеграм канал 'በክርስቶስ ( in christ)'

በክርስቶስ ( in christ)


563 подписчиков
73 просмотров на пост

Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin

Детальная рекламная статистика будет доступна после прохождения простой процедуры регистрации


Что это дает?
  • Детальная аналитика 4'186'310 каналов
  • Доступ к 1'470'428'171 рекламных постов
  • Поиск по 3'466'299'558 постам
  • Отдача с каждой купленной рекламы
  • Графики динамики изменения показателей канала
  • Где и как размещался канал
  • Детальная статистика по подпискам и отпискам
Telemetr.me

Telemetr.me Подписаться

Аналитика телеграм-каналов - обновления инструмента, новости рынка.

Найдено 409 постов

ጵራቅሊጦስ👉 ( አፅናኙ መንፈስ ቅዱስ) በምድር ላይ ለቅዱሳን አለኝታ ነው ።

ጵራቅሊጦስ 👉(ጠበቃው ኢየሱስ) በሰማይ ለቅዱሳኑ አለኝታ ነው።

@cgfsd
@ownkin
❤ 9
👍 1
🥰 1
(ራሃብተኛው ኢየሱስ)


  ኢየሱስ ራሃብተኛ ነው  ።ይርበዋል ፣ ይጠማዋል ደግሞ መራብ ብቻ ሳይሆን ይጠግባል ፤ይረካል ። ጌታ ኢየሱስ ሰው ይርበዋል ሰው ይጠማዋል !! የሰው ልጅ ሰው የሚርበው ብቸኝነቱን እንዲጋሩት ፣ ችግሩን እንዲረዱት ፣ ጎዶሎውን ለመሙላት ሲሆን ኢየሱስ ግን ሰው የሚርበው ህይወቱን እንዲካፈሉት ፣ ፍቅሩን እንዲቋደሱ ፣ በእሱ ክብር እንዲኖሩ ፣ ከእርሱ ጋር ህብረት እንዲያረጉ ሰው ይርበዋል ፣ ሰው ይናፍቀዋል ፣ የሰው ያለህ እያለ ሰውን ፍለጋ እስከ መስቀል ድረስ ተጉዞ መጥቷል ።

በአይሁድ እና በሰማሪያ መካከል ከፍተኛ አለመስማማት አለ ። ሰማሪያ ከሌሎች አህዛብ ጋር በመጋባታቸው  ለእስራኤል ከተሰጣቸው ትዕዛዝ ውጭ የሆኑ የማይታዘዙ ህዝቦች የተባሉ ናቸው ። በአይሁድ ማህበረሰብ ውስጥ የሃይማኖት መሪ የሆኑት ፈሪሳዊያን ሲያስተምሩ ደጋግመው ከሚፀየፉት ሶስት ነገሮች አሉ ከእነርሱም ውስጥ  ቀራጭ ፣ አመንዝራ እና ሰማሪዊ ይገኙበታል ። ሰማሪያዊ የሆነ ሰው ከአይሁዳዊ ሰው ጋር ዝምድና ፣ ማህበራዊ ህይወት መተባበር በመካከላቸው አይደረግም ። እየሩሳሌም ሊሄድ የተነሳ አይሁዳዊ በሰማሪያ አቋርጦ መሄድ ሲችሉ በሰማሪያ በኩል ሳያልፉ በሩቅ ዙረው ወደ ኢየሩሳሌም ይሄዱ ነበር ። ኢየሱስ በሰማሪያ ሊያለፍ ግድ ሆነበት ይሔ  ነገር  ለደቀመዛሙርቱ እንግዳ እንደሚሆን መገመት ይቻላል ። ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ በሰማሪያ ከደረሱ በኋላ ደቀመዛሙርቱ ምግብ ፍለጋ ወደ ሌላ ስፍራ ሄዱ ። ኢየሱስም በተራው ምግብ ፍለጋ ወደ ውሃ መቅጃ ጉድጓድ ተጓዘ ። በውሃ ጉድጓዱ ዙሪያ ርሃቡን ለማስታገስ ምግብ የሚሆን አንዳች ነገር በእርጋት ይጠባበቃል ። አንዲት ሰማሪያዊት ሴት በቀን ጠራራ ፀሃይ ውሃ ለመሙላት ከውሃ ጉድጓዱ ተገኘች። ይቺ ሴት ሰማሪያዊ ከመሆኗ ይልቅ ከባዱ ነገር ራሳቸው ሰማሪያዎች ያገለሏት ሴት መሆኗ ነው ። 5 ባሎች ነበሯት በመንደርተኞች ነውረኛ ብለው አግልለዋታል ። ኢየሱስ ግን በውሃ ጉድጓድ ያመጣው ጉዳይ ርሃቡ የዚች
ሰማሪያዊት ሴት ህይወት ነው ።  ኢየሱስ ግን ምን አይነት ርሃብተኛ ነው ?😭   ስለ አንድ ሰው ሰማሪያ የሚዘልቅ ፣ ብዙ እልፍ ሰዎች መካከል ተሰብስበው 2 አሳን እና 5 እንጀራን ሲያበዛ ባስተማረበት ቀን ያልተናገረው ሚስጥር ለአንዲት ሴት ለዛውም ሰማሪያዊት ከዛም የሚገርመው በሰው ለተገለለች አንዲት ሴት በእውነት በመንፈስ እንደሚመለክ ሚስጥሩን አካልፏል ።  ሰማሪያዊት ሴቷን የጠበቃት በዛ ስፍራ ጠምቶት አልነበርም የእሷን ጥም ሊያረካ ነበር መደፍረስ እና መንጠፍ የሚያቀውን ህያውን ምንጩን በውስጧ ተክሎ ለዘላለም ሊያረካት ነበር ። በኑሮዋ ውስጥ ያለውን የነፍስ ርሃቧን አንድ ጊዜ አግኝቶ በማንነቱ አጠገባት ። የሚገርመው እውነት መሲሁ ኢየሱስ ጋር ለጥቂት ደቂቃ አሳልፈው እድሜ ዘመናቸው የተለወጠ በርካታ ምስክሮች አሉን ። ይቺም ሰማሪያዊቷ ሴት ትልቅ ምስክራች ናት ።  ብዙ ጉድ ከቧታል ጉዷን ዘርዝሮ በማንነቱ ፊት አጋለጣት በእሱ ፊት መጋለጥ እንዴት ደስ ይላል !! በሰው ፊት መዋረድ ወርደት ነው ፤በሰይጣን ፊት መዋረድ ኩነኔ ነው ፤ በኢየሱስ መዋረድ ግን በተዋረዱበት እሱ ፊት ለመክበር ነው ። ውዱ ጌታ ጉዷን ገልጦ ፤ ጉድለቷን እና ክፍለቷን በራሱ ሞላላት ። እሷም ለወትሮ የፈራቻቸውን ጎረቤቶች ሰበሰበቻቸው ፣ለሰላምታ እንኳን ከኋላ የማያስከትሏትን ከፊታቸው ቀድማ ኑ ማ እዩ ጉዴን የነገረኝን ኑ ማ እዩ እሱ ነው ብላ ወደ ኢየሱስ አደረሰቻቸው ። ኢየሱስ ሰው የራባቸውን ሰዎች አጥጋቢ ያረጋቸዋል ።

ደቀመዛሙርቱ ተመልሰው ምግብ ይዘው ሲመጡ መምህር ሆይ ብላ ቢሉት እሱ ግን  በላሁ ፣ ጠገብኩ ነበር መልሱ ። እነርሱም ምግብ ያመጣለት ሰው ቢኖር ነው እንጂ የሚል ሀሳብ ውስጥ ገቡ ። እሱ ግን የበላው ምግብ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር ።ይሔ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሰው መዳን ነው ።  ኢየሱስ ሰው ይርበው ነበር !!ሰውንም ይናፍቅ ነበር ።

ለሰው ልጅ የሚሰጠውን ክብር ከጌታ ኢየሱስ እንማራለን ። እግዚአብሔር ሰው አክብሮ በመልክ አምሳሉ ፈጥሮት ሳለ በወደቀ ጊዜ እንኳን አልተወውም አንድ ልጁን ላከ በዚህም ልጁ በኩል ሰውን ፈለገ ። ኢየሱስ በምድር ላይ የራበው የጠማው ሰው ነበር ።ራሱ እንደነገረን የሰውን ልጅ ልፈልግ መጣሁ አለን ። እንግዲህ ምን ይባላል በፀጋው ጉልበት  ኢየሱስ የራበው ርሃብ ይራበን ፣ኢየሱስ ያጠገበው ጥጋብ ያጥግበን ብቻ ብለን በተራበ ልብ ወደ እርሱ በራሃብተኛ ልብ ሰው ወደ ሚርበው ሰው ራሃብተኛውን ኢየሱስ ወደ እሱ እንጣራለን ።


✍ ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
❤ 9
👍 3
🥰 1
ቅርብ ነው የምለው መሀሉ ታይቶኝ ነው
በእኔ እና አብ መሃል ያለው ኢየሱስ ነው
             
 
   🎼   
  @cgfsd
@ownkin
❤ 17
👍 4
🔥 1
የፅድቅ መስፈርቱ እና ልኩ ኢየሱስ ነው ። ለዛም ነው ኢየሱስ ፅድቃችሁ ከፈሪሳዊያን ፅድቅ ካልበለጠ ወደ መንግስተ ሰማያት ከቶ አትገቡም ያለው (ማቴ 5:20)። የፈሪሳዊያን ፅድቅ ግብዝነት ወይም ማስመሰል ያለበት ነው ሰው እንዲያያቸው የማያደርጉ ጥረት የለም የታይታ ፅድቅ ነው ። የፈሪሳዊያን ፅድቅ እስከ አደባባይ ሲሆን የኢየሱስ ፅድቅ እሰከ መስቀል ድረስ የተገለፀ ነው ። ኢየሱስ ሲጀመር በመስቀል ላይ የሞተው ስለ ፅድቅ እንደሆነ መፀሀፍ ቅዱሳችን ይነግረናል ። በመስቀል ላይ ኢየሱስ የእኛን  የሀጢያት እዳ በደሙ የከፈለው ዋጋ ስለ ፅድቁ ስለ ባህሪው ነው ። ዝም ብሎ ሀጢያታችሁን ትቼዋለሁ አላለም ምክኒያቱ ፃዲቅ (ትክክል) ነው ተበድሏል እንዳልተበደለ አይሆንም ሀጢያት ማየት አይችልም ስለዚህ የሀጢያታች ፍርድ ሞት ስለሆነ መሞት ይገባናል የእኛን ሞት ለማስቀረት እሱ ጌታ ሞተልን ይሔ የሚያሳየው ፅድቁን መፈፀም ነው ። በመስቀል ላይ የተፈፀመው ፅድቅ ያስደንቃል ። ኢየሱስ የፈፀመው ፅድቅ እሰከ ቀራንዮ ድረስ ስለ እኛ ብዙ ርቀት ተጉዞ ነው ። እኛም የፀደቅንበት ፅድቅ ኢየሱስ  በመስቀል ላይ በፈፀመው ፅድቅ በትንሳኤው በኩል ነው ፤ፀድቀናል ለማለት የማንፈራው እሱ በምን ያህል ልክ ፅድቅን እንደፈፀመልን እየተረዳን ነው ። ስለዚህ በፅድቅ ለመኖር እንደ ፈሪሳዊ እታች ላይ ማለት አይጠበቅብንም የፅድቅ ልክ እና መስፈርቱን ኢየሱስ በማየት በእርሱ በኩል  መመላለስ ነው ።


@cgfsd
@ownkin
👍 15
❤ 2
(ኢየሱስን መሳለም )

እነዚህ ሁሉ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል ሳያገኙ እምነታቸውን እንደ ጠበቁ ሞቱ፤ ሆኖም ከሩቅ አይተው ሰላም አሉት፤ በዚህ ምድር ሲኖሩ መጻተኞችና እንግዶች መሆናቸውን ተገንዝበው ነበርና።
ዕብራውያን 11:13

* የቀድሞ አባቶች በብሉይ ኪዳን የነበሩት በተስፋ በትንቢት የተነገራቸውን ክርስቶስ  አብዝተው ይናፍቁት ነበር ። በየትኛው ዘመን እንደሚመጣ እየመረመሩ እንግዳን እንደሚቀበል ሊቀበሉት ይወዱ ነበር ። በእነርሱ ዘመን ስላልመጣ በተስፋ ውስጥ በመጠበቅ በሩቁ ሰላም አሉት  በተነገራቸውን ትንቢት በኩል እየተሳለሙት (ሰላም) እያሉት ይጠብቁ ነበር ። በሩቅ እንደመጠበቅ የሚያደክም ምን አለ? በሩቁ ተሳለሙት ይመጣል እያሉ ናፈቁት ኧረ የመሲህ ያለህ በማለት ዘመናቸውን ኖሩ ። ከእነርሱ መካከል ሙሴ ክብርህን አሳየኝ ብሎ ይሔን መሲህ ሰላም ለማለት ፀለየ ፣ አብርሃምም በወለደው ይስሃቅ ዘር በኩል በመሲሁ እንደሚመጣ  ቀኑን አይቶ ተደሰተ በሩቁ ሰላም ብሎ አለፈ ። ዳዊት ደግሞ እሱ በነገሰበት ዙፋን ለዘላለም ሳይቋረጥ በዘር ሃረጉ የሚመጣው መሲህ ሲነግስ ተመልክቶ በደስታ በሩቁ ተሳልም  ሰላም ብሎ አለፈ ።

እነዚህ ሁሉም የእምነት አባቶች በከፍተኛ ጉጉት የመሲሁን መምጣት በመጠበቅ በተስፋ ቃል በትንቢት በሩቅ ተሳለሙ ወይም ሰላም ብለው እጅ ነስተው ተሻገሩ ። ለእኛ ግን በሩቅ አይደለም የተሳለምነው በቅርቡ ተሳለምነው እጅ ነስተን ሰላም አልነው በቅርቡ ጨበጥነው ፣ ስሙን ተዋብንበት፣ ፍቅሩን ለበስነው፣ የተወጋውን እጁ በመንፈሱ ዳሰስነው በቅርቡ ሰላም አልነው ። አዎ ኢየሱስ ቅርብ ነው ። እርሱ የሰው ልጅ በመሆኑ ሰው በሚለው መጠሪያ እንደኛው ተጠርቷል ። ሰው በመሆኑ ለሰው ልጆች ዘመድ የቅርብ ሰው ሁኗል የኛ ሰው ሁኗል ። ሰው ለሰው ዘመድ ነው !! የቀረበንን በቅርበቱ ተሳለምነው ። ቀርቦን ቀረብነው ፣ ተዛምዶን ተዛመድነው ፣ አግኝቶን አገኘነው ፣ ፈልጎን ፈለግነው ። አሁን በቅርብ የምንሳለው ጌታ አለን ፣ ፍቅሩ ከፀሃይ ይልቅ የምንሞቀው ፣ ደሙን ከውሃ ይልቅ በእምነት የምንጠጣው፣ ስጋውን ከእንጀራ ይልቅ የምንበላው አግኝተን የምንፈልገው የቅርብ ቅርብ ክርስቶስ ወገናችን አዎን እርሱ አለን ።

* ለማግኘት መፈለግ እና አግኝቶ መፈለግ የተለያዩ ናቸው በሩቅ የተሳለሙት ሊያገኙት ፈለጉት  እኛ ደግሞ በቅርብ የተሳለምነው ስላገኘነው ደግመን ፈለግነው ። መሲሁን ለማግኘት መፈለግ እና ያገኙትን መሲህ መፈለግ የሰማይ እና የምድር ያህል ይራቃቃል ። መሲሁን ለማግኘት መፈለግ ያላገኙትን  ለማግኘት ተስፋ አስቆራጭ ህይወት ውስጥ ተስፋን መፈለግ ሲሆን ያገኙት መሲህ መፈለግ ግን ያገኙችን መሲህ ለመከተል ነው ያገኙትን መሲህ እሱ እንደሚኖር ለመኖር መፈለግ ነው ፣ ያገኙትን መሲህ መፈለግ እሱን ለመምሰል መፈለግ ነው ።  አግኝተነዋል ደግሞ በመንፈሱ ምሪት እንፈልገዋል ዳግም ተመልሶ መምጣቱን በመጓጓት እንናፍቃለን የሞተልን፣ የደማለን፣የተሰቃየልን እርሱ ደግሞ ውቡ የሆነው ቤዛችን በሙሉ አይናችን ያለ ድንግዝግ ልናየው እንናፍቃለን ።

    የቀረበንን ቅርቡን ኢየሱስ መሳለም


✍ ፊሊሞን ነጋ
@cgfsd
@ownkin
👍 10
ኢየሱስ እንዴት ይታወቃል?


ኢየሱስ ለማወቅ የግድ እግዚአብሔር ራሱ ሊረዳን ይገባል ። እግዚአብሔር ኢየሱስ ካልገለጠልን ኢየሱስ እንደ አንድ ተራ ሰው ብቻ እንረዳዋለን ስለዚህ ኢየሱስን በማንነቱ ልክ ለማወቅ የግድ የእግዚአብሔርን ብርሃን ያስፈልገናል ።

ኢየሱስ መገለጥ ነው ። ካልተገልጠልን በእርሱ እንሰናከላለን በእርሱ ስር የምንሰደው ማንነቱ ሲገለጠልን እና ሲበራል ብቻ ነው ። የግድ ኢየሱስን ለማወቅ የልቦ አይኖቻችን የሚዳስስ የእግዚአብሔር እጅ ያስፈልጋል ።

መንፈስ ቅዱስ ወደዚህ ምድር ሲመጣ ጌታ ኢየሱስ የሰራውን ስራ እና ማንነት ለማስረዳት መጥቷል ። በመንፈስ ቅዱስ በኩል ይሔ የህይወት መፀሃፍ የሆነው ኢየሱስ ይገለጥልናል ።

መንፈስ ቅዱስ ሲገልጥልን ደግሞ በቅዱስ ቃሉ ውስጥ የተጠቀሰውን የመፀሃፍ ቅዱሱን ኢየሱስ ይሆናል ። ብዙዎች ኢየሱስ እንደሚገለጥላቸው ሲያስቡ ከመፀሃፍ ቅዱሱ ውጪ ይጠብቃሉ ይሔ ልክ አይደለም ። የመፀሃፍ ቅዱሱን ኢየሱስ መንፈስ ቅዱስ ያስተምራል ።


ኢየሱስ የሚታወቀው ከቅዱስ ቃሉ በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ነው ።

@cgfsd
👍 9
(የክርስቶስ ትንሳኤ )


በክርስቶስ ትንሳኤ ውስጥ ከክርስቶስ ጋር ያለ አንድነት አለ ።ከክርስቶስ ጋር ያለ አንድነት ማለት በእምነት የሆነ አንድነት ነው ። አማኝ የክርስቶስ ተካፋይ ናቸው ። ተካፋይ የሆነው በእምነት ከሆነ አንድነት ነው ። እንዴት ነው ከክርስቶስ ጋር በእምነት አንድነት የሚኖረው ከተባለ ሞቱን እና ትንሳኤውን በእምነት በመተባበር ነው ። የዛሬ 2000 ዓመት ኢየሱስ ሲሰቀል አልነበርንም ሲነሳም እንደዛው ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ በእምነት አብረን በእሱ ውስጥ ከእርሱ እንሞታለን ከእርሱ ጋር እንነሳለን ። ከክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ ጋር መተባበር ማለት እርሱ እኛን ለማዳን ከእኛ ጎን እንደቆመ ሁሉ ከዚህ በኋላ ለራሳችን ላንኖር ከእርሱ ጎን የምንቆምበት ነው ። እጅግ አብልጠን ለክርስቶስ የመኖር ፍላጎት በህይወታችን ሞልቶ የሚተርፈው ከክርስቶስ ጋር አብረን ከሙታን  እንደተነሳን በቅጡ ስንረዳ ነው ። ለክርስቶስ መኖር የትንሳኤ ኑሮ ነው ። ምክኒያቱም የራሳችን የመኖር ጉጉት ፣ አላማ ፣ መሻት መስቀል ላይ ከእርሱ ጋር ተሰቅሏል ለራሳችን እንዳንሆን እኛ  ተገለናል  አሁን እኛነታችን የለም በመስቀሉ ሂሳብ ሙተናል !! አለን የምንለው ኑሮ በትንሳኤው የተቀጠለ ነው ። ትንሳኤ ደግሞ የክርስቶስን ህይወት ለመኖር ፤ ለእግዚአብሔር ህያው ለመሆን ነው የጀመርነው ።ትንሳኤ የኔን ሞት ለሞተልኝ ለእርሱ እኖራለሁ ያስብላል ።ትንሳኤ የኔን ሞት ሙቷል የእሱን ህይወት እኖራለሁ ያስብላል ትንሳኤ የኔን ሀጢያት ወስዶልኛል በእርሱ ፅድቅ ፀድቀናል ያስብላል ። ለክርስቶስ መኖር በልባችን ውስጥ በብርቱ መሻት የምንፈልገው በትንሳኤው የክርስቶስን ህይወት ለመኖር እኛ ሙተን ለእርሱ በመነሳታችን  ነው ።



@cgfsd
@ownkin
👍 13
የመስቀሉን መንገደኛ ፣ የህማሙን ሰው ፣ ስቅዩን ኢየሱስ ፣የተወጋውን መድህን ፣የተቆሳቆለውን አዳኝ ፣ የተቆረሰውን ቤዛ፣ ባለችንካሩን መሲህ፣ የእሾህ አክሊል የደፋውን ንጉስ ፣የደማውን ጌታ አዎን በእርሱ በተሰቀለው ክርስቶስ ላይ ዘወትር የተመሰጠ በታላቁ የመስቀሉ ስራ ውስጥ ያለውን ጥልቁን የእግዚአብሔር ልብ ከልቡ ይማራል ።
      
   
@cgfsd
👍 7
        (ስቅዩ ኢየሱስ)

  *የህማም ሰው
            ነብዩ ኢሳያስ

  * የተሰቀለው ክርስቶስ
            ሐዋሪያው ጳውሎስ

* ቁስለኛው መድሃኒት
              ሐዋሪያው ጴጥሮስ


ስቅዩ ኢየሱስ ወይም የተጎሳቆለው አዳኝ ነው ። በስቃይ ጎዳና ውስጥ አልፏል የስቃዩ መንገድ ልዩ መጠሪያው አድርጎታል ። ስቅዩ ኢየሱስ ጎስቋላው አዳኝ
   
በእርግጥ መስቀል ህመም አለው ። የተከፈለው ዋጋ ስሜት ሊሰጠን የሚችለው ዋጋው የከፈውን  ህመም እንዳለው ትውስ ሲለን ነው ። የክርስቶስ የህማም ጉዳና የጀመረው መስቀል ላይ አልነበረም ማለት ሰው መሆኑ በራሱ አምላክ አይመጥንም ገና ሰው ከመሆኑ ራሱ የሄደበት መንገድ ህመሙን ይጠቁማል ። 
  "

አይተነው እንወደው ዘንድ ደምግባት የለውም ይሔ የሆነው ምን ያህል ህመማችን ሊወስድ ራሱ በትህትና ልህቀት ዝቅ አርጎ የገለጠበት ነው ። አሟሟቴን አሳምርልኝ በሚባልበት ዘመን እሱ ለሞት የማይመቸው ይሔው በወንጀለኛ መቅጫ የሞትን ፅዋ ቀመሰ ። መስቀል የሮማዊያን የአቀጣጥ ስልት ነው ። የሮማዊያን ዋነኛ አላማቸው በመስቀል መግደል ብቻ አይደለም የሚሞተውን አዋርዶ እርቃኑን ማጋለጥ የሰው መዘበቻ ማድረግ ነበር ።አይሁዳዊያን  የሚሰቀለውን ይፀየፉታል መሬታችን እንዳያረክስ ይላሉ ። ታዲያ ጌታችን የመዋረድን ጥግ የመፀየፍን ጥግ በመቅመስ የህማም ሰው የሆነው ለእኛ እንደሆነ መገንዘብ አለብን ።
  በመስቀል የሚሰቀለው ወንጀለኛ የሰውነቱ ክብደት በእጅ ላይ ስለሚሆን ከፍተኛ የስቃይ ስሜት ይኖረዋል ። የሚሰቅሉት ወታደሮች በሰፍነግ ሞልተው ሆምጣጤ ያጠጧቸዋል ምክኒያቱ ደግሞ የስቃዩን ስሜት እንዲያስረሳቸው እና እንዲቀንስላቸው በማሰብ ።ሆምጣጤው የወይን አይነት ነው ። ከጌታ ጋር በግራ በኩል የተሰቀለው ምናልባት ሆምጣጤውን ጠጥቶ ሳይሆን አይቀርም ይሆን በድፍረት እና በማናለብኝነት ጌታን ራስህን አድን እያለ የተናገረው ሆምጣጤው የስካር ስሜት  ስሚኖረው  ነው ። ኢየሱስ ግን የህመሙን የስቃዬን ስሜት ሊቀንስለት የሚችለውን ሆምጣጤውን ሲሰጡት ያልጠጣበት ምክኒያት የመስቀሉን ህመም ሲቃ ሊያጣጥመው ፈልጎ ነው ህመማችን መታመም ፈልጓል ስቃያችን ሊሰቃይ ራሱን አሳልፎ ሰጥቷል በሸላቶቹ ፊት ሊታረድ እንደሚሄድ በግ ዝም አለ የመታረድን ሰቆቃ ስለ እኛ ሲል ፈለገ ። ስለ እኛ መታመም ወደደ እውነትም የህማም ሰው ስለ እኛ እና ስለ እኛ ነው ።
  እግዚአብሔር አብም ቢሆን የህማሙ አካል ነው ። አንድ ልጅን ከመስጠት በላይ ህመም የለም በእቅፉ ያለ በዘላለማዊ ክብር አብረው  አምላካዊ ፍቅር  የሚቋደሰውን አንድ ልጁን ሲሰጥ ህመሙ ጣራ እንደሚነካ መገመት አይከብድም ።


@cgfsd
@ownkin
👍 10
    (ማዕከሉ ክርስቶስ )




መዝሙር መዘመር ደስ ይላል በተለይም ሲዘምሩ ማዳመጥ ደግሞም እንደዛው ፤ ከሁሉ በላይ ደግሞ የምንዘምረውን መዝሙር ግጥም እና ዜማ አብጠርጥሮ አውቀነው  መዘመርን ብቻ ሳይሆን መዝሙሩ የተዘመረበትን ጥልቅ ሀሳብ መልዕክት በደንብ ከውስጥ አዋህደን ማዜም እጅግ ደስ ይላል ።

    በዘመነ ኮሮና ከተቀቁት የምስል መዝሙር መካከል በዘማሪ ሃዋዝ ተገኝ የቀድሞ  የመዝሙር አልበም በአዲስ በምስል መልኩ የተሰራው  ይገኝበታል። ከዚህም መካከል መዳፉ በአይኖቼ ፍቅሩ በልቤ ነው የሚለውን መዝሙር እያዳመጥኩ በብዙ ስታነፅበት ነበር ።  ዘማሪው መዝሙሩን በለቀቀበት  በዛው ሰሞን ቃለ መጠየቅ ሲደረግለት በቃለ አዋዲ የቴሌቪዥን መስኮት ተከታተልኩ ።
    ጠያቂው ላዕከ  መዝሙሩ የዘመርከው ከ9 አመት በፊት ነው  ግን አሁን እንደ አዲስ በምስል መልሰህ ሰርተኸዋል አሁንም ድረስ ጉልበት ያለው ጠንካራ  ነው ለምን ይመስልሀል? ብሎ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጁ ጠየቀ ።
     ዘማሪውም የሚመስለኝ መዝሙሮቹ ክርስቶስ ማዕከል ያረጉ ስለሆኑ ነው ብሎ ለጠንካራ ጥያቄ ጠንካራ መልስ መለሰ።

    በጣም አንገብጋቢ ጉዳይ ይመስለኛል!!  የምን መሰልኝ  ነው እንጂ በመዝሙሮቻችን ክርስቶስን ሲያማክሉ እሱ ሲዘክሩ እሱን ሲሸቱ መዝሙሮቻን በተራ ጉዳዬች የማይደበዝዙ እና የማይፋቁ ይሆናሉ ። ጋሽ አዲሱ ወርቁ የመስቀሉ ፍቅር በተሰኘው የሰንዱቅ አልበማቸው  ውስጥ ጠቅላላ ማለት በሚቻል መልኩ እያንዳንዱ ነጠላ መዝሙር ከመስቀሉ ታላቅ ገድል ጋር የተገናኙ እና ያንን ጥልቅ የማዳን እውነት የሚያወሱ ናቸው እንደዚ አይነትም በስለት የተሳለ በገናም ያስፈልገናል።

  ስለዚህ መዝሙሮቻችን የተመሰረቱት ማን ማዕከል (ባማከለ )መልኩ ነው የሚለው ለሁላችን ቅዱሳን ልናስተውለው  ይገባል ።
ክርስቶስ ማዕከል ካረጉ መዝሙሮች መካከል ብዬ የማስባቸው  ስለ ክርስቶስ ሊቀ ካህነት ፣ ስለ መስቀሉ ፣ስለ ደሙ ፣ስለ ትንሳኤው ፣ ስለ ዳግም መምጣቱ  ከብዙዎቹ በጥቂቱ እነዚህ ይመስላሉ ክርስቶስ ማዕከል ያደረጉ መፀሀፍ ቅዱሳዊ  መልዕክቶች እነዚህ ናቸው።

መፀሀፍ ቅዱስ ክርስቶስን ማዕከል አርጎ የተፃፈ ህያው መፀሃፍ ነው ፣ እስራኤል መሲሁ ኢየሱስን ማዕከል አድርጎ የተመሰረ ህዝብ ነው ፣ ቤተክርስቲያን ክርስቶስን ማዕከል አድርጎ የተመሰረተ ቅዱስ ማህበር ወይም አካል ነው ።

  ክርስቶስን በሁሉ ረገድ ማዕከል እናርግ!!!!!


✍ ፊሊሞን ነጋ
@cgfsd
@ownkin
👍 12
አዲስ ኪዳን በእግዚአብሔር ያተኮረ፣  ክርስቶስን ያማከለ፣መንፈስ ቅዱስ የሞላበት ነው ።

  from review magnifiying God in christ

@cgfsd
👍 6
ኢየሱስ (ክፍል 5)

በየቀኑ ኢየሱስ አዲስ ነው።እርሱ ሙሽራም ነው።ሙሽራ ማለት በምክንያት የማይቀር ምክንያቱ መምጣት ብቻ የሆነ ነው።ሁለት ሰው በሚጋባበት ሁለት ሺህ አዳማቂዎች አሉ።በበጉ ዙፋን ፊት ሁላችንም አዳማቂ ሳንሆን ሙሽሪት ነን።ምድራዊው ሰርግ አንድ ቀን ሰማያዊው ግን የሁሌ ሰርግ ነው።መንግስትህ ትምጣ ብሎ መጸለይ ከክርስቲያን ጥራቶች አንዱ ነው። መልካካም መንግስቶች እንዲመጡ እየጸለይን መንግስትህ ትምጣ አለማለት አጀብ የሚያስብል ነው።መጠየቅ ያለበት ጉዳይ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር መሆኑ ሳይሆን እኛ ከእግዚአብሔር ጋር መሆናችን ነው።

እግዚአብሔር ሲያዝዝ ለምን ፤ ሲያደርግ እንዴት አይባልም።እኛ ካለ ነገር የሚኖር ነገር ማምጣት አልቻልንም እርሱ ግን ከሌለ ነገር የሚኖር ነገር አምጥቶ አሳይቶናል።የቁጥቋጦው ልምላሜ እሳቱን የእሳቱም ኃይል ቁጥቋጦውን አላቃጠለውም።ይህ ማለት የእስራኤል ጥረት የግብፅን መከራ የግብፅ መከራም እስራኤልን ሊያጠፋት አልቻለም።በስላሴ መንግስት መላክ እና መ`ላክ፤ማዘዝ እና መታዘዝ የክብር መበላለጥ ሳይሆን ሚስጥረ ፍቅር ነው።ከስሙ የወጣው ኃይል እኛን ሲያጸናን ጠላታችንን ግን ይጥለዋል።ቅርንጫፍ ከግንዱ ሲለይ ቅርንጫፉ እንጂ ግንዱ አይደርቅም።ልክ እንዲሁ እኛም ከጌታ ከተለየን የምንደርቀው እኛ እንጂ እርሱ አይደለም።

የኢየሱስ ፍጥረትን ማዘዙ አንዱ የአምላክነቱ ማረጋገጫ ነው።ይህም አምላክ ብቻ ሊያደርገው የሚችለው ነገር ነው።የሚያደርጋቸው ተዓምራቶች ራሱ የአምላክነቱ ማስረጃ ነው።ግን ይህንን እኮ ከኢየሱስ በበለጠ ሐዋርያት አድርገውታል።ነገርግን እነርሱ በእርሱ ስም እርሱ ግን በራሱ ስም አድርጎታል።ከድንግል መወለዱ፤ለኀጢአት ይቅርታ መስጠቱ፤ከሞት መነሳቱ፤ዳግም ምጽአቱ(ኢያሱ ጸሐይን አዘግይቶ ማታ እንዳይሆን በብርሃን እንዲቆዩ እንዳደረገ ኢየሱስም ጨለማችንን አስወግዶ በብርሃን እንድንመላለስ አድርጎናል።የመላው ብሉይ ኪዳን ትልቁ የትምህርት ማዕከል ኢየሱስ ነው።ከኀጢአት ማዳኑም ጭምር የአምላክነቱ ማሣያ ነው።በሥጋ ዘመዳችን ወንድማችን ሲሆን በመለኮቱ አምላካችን እና አባታችን ነው።እርሱ በሥጋ አይሁዶች የያዙት ሲሆን በመለኮቱ ግን አለምን የያዘ ነው።የማንሸፍነው መልካችን ኢየሱስ ነው መልኩን እንድንገልጥ እንድናሳይ እግዚአብሔር የሳለብን መልካችን እንዲገለጥ ጌታ ይርዳን። አሜን!!!

በረከት ከበደ
👍 7
የእግዚአብሔር ፀጋ የእርሱን ፍቅርና የምህረቱን ታላቅነት የሚያሳይ ስም ነው ። ስም ደግሞ ከማንነት የሚወሰድ ጥቅስ ነው ። ፀጋ ከእግዚአብሔር ማንነት የሚቀዳ ሕይወት የሚሰጥ ምንጭ ነው ። በእግዚአብሔር ፀጋ መኖር የእርሱን ወደር አልባ ፍቅር ፣ ምህረትና ቸርነት መቅሰም ፣ በእርሱ ዘወትር መደነቅ ነው።


   የፀጋው ዙፋን ገፅ 110

@cgfsd
👍 5
(በደም የቀላው ስም )


ኢየሱስ የሚለው የስምህ ጉልበት
አብ ከፍ ያደረገው የደምህ ዋጋ አለበት

        Hu fellow

ጌታ ኢየሱስን በሁለት መንገድ በስፋት መረዳት እንችላለን በማንነቱ እና በስራው ። ክርስቶስ
ኢየሱስ ማን ነው በሚለው እና ምን ሰራ በሚል ሀሳብ ውስጥ እሱን ማወቅ ይቻላል ። ብዙዎች ኢየሱስን ለመገንዘብ የሚፈልጉት በአንዱ ጉን ብቻ ነው ስለዚህ ስር ሰደደው ለማወቅ አልታደሉም  በማንነቱ ወይም በስራው በኩል አንዱ ላይ የተለየ ትኩረት በማረግ ለማወቅ ሲጥሩ ይታያል ይሔ ደግሞ በሆነ ጎኑ ብቻ ስለሚሆን የተንሸዋረረ እይታ ይፈጥራል ። ማንነቱ እና ስራው በአግባቡ መለየት ጌታችን እና መድሃኒታችን ኢየሱስ በቅጡ ለመረዳት ወሳኝ ነጥብ ነው ።  ስላሴን በተሻለ ልብ ለመገንዘብ የክርስቶስ ማንነት እና ስራ በለጠ  እግዚአብሔርን እንድንረዳ ያግዘናል ። ኢየሱስን ማወቅ ስላሴን ለመረዳት በር ነው ይሔ የሚሆነው ውዳችን ኢየሱስ በማንነቱ እና በስራው ስናወቅ ነው ።

ከላይ  ጠቅሰን የጀመርነው የመዝሙር ስንኝ
የክርስቶስን ማንነት እና ስራ ያሳያል ።

      በሰማይ በምድር ስምህ እንዲገንን
      አንተ ኢየሱስ ነህ  ክርስቶስ እንድንል
      የነበረው ማንነትህ
      ይልቁንም ከበረ በሰማይ አባትህ
      ኢየሱስ የሚለው የስምህ ጉልበት
     አብ አፍ ያደረገው የደምህ ዋጋ አለበት

መዝሙሩ የሚያጠነጥነው የኢየሱስ ስም ላይ ሲሆን ስሙን ከማንነቱ እና ከስራው ጋር እንድንመለከት ይጠቁመናል ።

ኢየሱስ የሚለው ስም የከበረ ነው ። ይሔ ክብር ግን ለጌታችን ያልነበረ ክብር አይደለም አስቀድሞ በአባቱ ዘንድ የከበረ ክቡር ነበር ። ነገር ግን ለቤዛነት ወደ አለም ወደ ሰው ልጆች የሰው ልጅ ሆኖ መጣ በሌላ አነጋገር አምላክ ሰው ሆነ !! 😱 ..ለአምላክ ሰውነት አይመጥነው ሰው በአምላክ የተፈጠረ ፍጡር ነው ። አምላክ የፈጠረውን ፍጡር ሆነ በፍጡሩ ሰው የሰው ልጅ ተብሎ ተጠራ ። ኢየሱስ ሰው ሲሆን አምላክነቱን ጥሎ አልነበረም አምላክነቱን የሆነ ቦታ አላስቀመጠው አምላክነት ሲጀመር እንዴት ይተዋል? እንዴት ይቀመጣል ? አምላክነቱ ሳይቀንስ ሰውነት ጨመረ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሎ እንደ ተጠራ የሰው ልጅም ተብሎ ተጠራ ። በመሆኑም ሰው መሆን ለአምላክ ወርደት ነው ማለትም የማይመጥነው የማይገባው ነውና ። ሰው በመሆኑ አምላክ የሆነው ወልድ ኢየሱስ ዝቅ አለ ፣ የባሪያን መልክ ያዘ ፣ ዘመን የማይቆጠርለት ዕድሜ ተቆጠረለት፣ ይሔ ጌታ ሰው በመሆኑ ዝቅ ብሏል ፣ ያነሰም አስመስሎታ ፣ ደካማ ተብሏል ይብሱኑ ሞተ ነገር ግን አምላክ ነውና ከሙታን ተነሳ ከፍ ከፍ አለ ከበረ ስሙ እጅግ ወድ ሆነ ስሙ ማንነቱን እና ስራው ተናገረ ። ኢየሱስ የሚለው ስም የኢየሱስን ማንነት እና ስራ በግልፅ ይናገራል ።
መዝሙሩ ሲጀምር
   " የነበረው ማንነትህ .
    ይልቁን ከበረ በሰማይ አባትህ" ይላል
ይሔ ሀሳብ ስራህን ፈፅመህ በማንነት ከብረሃል ልትሰራ የመጣኸው ስራ ከማንነት አላስተጓገለህ የሚል አንድምታ አለው ።

ኢየሱስ የሚለው ስም መድሃኒትነትን ወይም አዳኝ የሚል ትርጓሜ አለው ። ጌታ ኢየሱስ በተወለደበት ዘመን በርካታ ሰዎች በዚህ ስም ይጠሩ ነበር ለዚህም ነው የእኛን፣ የመፀሃፍ ቅዱሱን፣ የእግዚአብሔርን ኢየሱስ ለመለየት የናዝሬቱ ኢየሱስ በመባል በናዝሬት በመኖሩ መለያ ተደርጎ ይሔ ስም የተሰጠው ። የናዝሬቱ ኢየሱስ ግን ስም ብቻ አልነበረም ማንነትም ጭምር እንጂ በርካቶች በዚህ ስም ቢጠሩበትም እሱ ጋር ይሔ ስም ሊከብር ቻለ ሰውነቱ እና አምላክነቱ በዚህ ስም ተገናኙ ። ለዚህ ነው ኢየሱስ የሚለው ስም በማንነቱ እና በስራው ምክኒያት ሊገን የቻለው ።

ላነሳው የምፈልገው በጣም የገረመኝ ሀሳብ ግን ያለው በዚህ ስንኝ ውስጥ ነው
" ኢየሱስ የሚለው የስምህ ጉልበት
  አብ ከፍ ያደረገው  የደምህ ዋጋ አለበት"

የደምህ ዋጋ !! የደምህ ዋጋ !! ደም በመፀሃፍ ቅዱሳችን ዋና እና ግሩም ሀሳብ ነው ።  ደም ህይወትን ይወክላል በዚህም ምክኒያት ደም ሳይፈስ ስርየት የለም የተባለው ። ብዙዎቻችን የክርስቶስ ደም ሲባል ትዝ የሚለን በቀራንኒዮ ላይ የተንጠባጠበው ሲገረፍ የደማውን ፈሳሽ ነው በእርግጥም ትክክል ነው ነገር ግን ከዛ የሰፋ ትርጉም አለው ። የክርስቶስ ደም የሚወክለው ጠቅላላ ክርስቶስ የሰራውን ስራ ነው ። ከተወለደ ጀምሮ  በንፅህና ያለ አንዳች በደል  የተመላለሰበት ኑሮውን፣ የመስቀል ሞቱን ፣ ዋጋ መክፈሉን አጠቃሎ ይይዛል ።የክርስቶስ ደም የክርስቶስ ስራ የሚወክል ወኪል ነው ።  በክርስቶስ ስራ ደግሞ አብ ተረክቷል ፣ መስዋዕትነቱን ተቀብሏል ። አብ ከረካ ደግሞ መስዋዕቱን ከተቀበለ ለርካታው የሚሰጥ ምላሽ አለ እሱም መክበር ይባላል። በክርስቶስ መክብር ውስጥ አብ ለልጁ ስራ ማለትም ለደሙ  የሰጠው የርካታ ምላሽ አለ።
አብ ከፍ ያደረገው የደም ዋጋ አለበት በክርስቶስ ስም መክበር ውስጥ ግልፅ የማያሻማ የደም ዋጋ አለ ማለት በምድር ላይ በንፅህና የኖረው ፣ የታዘዘበት፣ የቀረበው መስዋት በደሙ ውስጥ አለ ። ኢየሱስ የሚለው ስም በደም የቀላ ነው በዚህ ደም የተዋበ ውብ መጠሪያም ፣ ህያው ማምለጫ ነው ። በዚህ ስም ውስጥ ደሙ ይሰማል ፣ደሙ ይጮኸል፣ ደሙ ይሸታል ፣ ደሙ ያውዳል ፣ ደሙ ያምራል ፣ ደሙ በድምቀት ይታያል ።

ኢየሱስ የሚለው የስምህ ጉልበት
አብ ከፍ ያደረገው የደምህ ዋጋ አለበት

✍ ፊሊሞን ነጋ

@ownkin
@cgfsd
👍 9
የእግዚአብሔር ምህረት ለበደላችን የተደረገ ይቅርታ ብቻ ሳይሆን በፍርድ ወንበር ለቆመ ሰው የተደፋለት የክብር አክሊል ነው ።

   የፀጋው ዙፋን ገፅ 68

@cgfsd
👍 9
👎 1
ጌታ ኢየሱስ በጣር በጭንቅ ከተንጠለጠለበት እንጨት ላይ ወደ አባቱ እንዲህ ሲል ጮኸ "ኤሎሂ አሎሂ ለማሰበቅታኒ  አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ "። አብ አባት ደግሞ በዝምታው ውስጥ እንዲህ ይል ነበር "የተሰዋውን ወልድን ተቃረጡት ፣ የተቆረሰውን መሲህ ቅመሱት ፣ ውዱን ልጄን ይሔው እንኩ ።"

@cgfsd
👍 10
የወልድ ሰው መሆን ፤የድንቆች ድንቅ ፣ የምስራቾች ሁሉ የምስራች ነው ። የማይታየው እግዚአብሔር ይታይና ይዳሰስ ጀመር ።በእርሱ ያመኑ በስጋና ደም እንደሚካፈሉ እርሱም ያንኑ ስጋና ደም ተካፈለ (ዕብ2:14) ። ከመጀመሪያ በፍጥረቱ ላይ ያደረገውን በራሱ ላይ አደረገ ። እግዚአብሔር ወልድ በእርሱ ለእርሱ በተፈጠረው ዓለም ውስጥ ተወለደ ፤ የፈጠረውን ሰውነት ተካፈለ ። ፍጥረቱን የሆንነው እኛ ከራሱ ጋር ለማስታረቅ ራሱ ፍጥረቱን ሆነ ።የእግዚአብሔር ልጅ ከሕግ በታች ተወለደ (ገላ4:4) ፤ ራሱን ዝቅ አድርጎ ሰው በመሆን የባሪያን መልክ ያዘ (ፊል 2:7_8) ። መንፈስ የሆነው አምላክ ከልዕልና ወደ ትሕትና መጣ ። መለኮት ከሰው ጋር ተዛመደ ፤ የስጋችን ቁራጭ ፣ የዐጥንታች ፍላጭ ሆነ ፤ " በአጭር ቁመት " ፣ በጠባብ ደረት ተገለጠ ። በነገር ሁሉ እኛን መሰለ ። ይህ የተአምራት ሁሉ ተአምር ነው !

   የእግዚአብሔር ልጅ ገፅ 126
      በጳውሎስ ፈቃዱ

@cgfsd
👍 13
እንዲያውም ጌታችን ሰው ለመሆን ራሱን በትሕትና ዝቅ ያደረገበት ውሳኔው የመስቀሉ መሰረት ነውና ስርየት የሚጀምረው ወልድ ሰው ለመሆን ከመፍቀዱ ነው ። እናም ጎልጎታ የወንጌል መልከዐ ምድር ማዕከላዊ ኮረብታ እንጂ በተናጠል የቆመ ተራራ አይደለም ። ጎልጎታ አምላክ ሰው ሆኖ የመወለዱን፣ የኋጢያት የለሽ ሕይወቱን ፣ የትንሳኤውን ፣ የዕርገቱንና የዳግም ምፅአቱ ጎዳናዎቹ ሁሉ ዐቅፎ የያዘ ድንቅ ኮረብታ ነው ። የስርየት ስራው በትስጉት (ሰው በመሆኑ) መነፀር መታየት የሚያስፈልገው ለዚህ ነው ።


ገፅ 388 የእግዚአብሔር ልጅ
    ጳውሎስ ፈቃዱ

@cgfsd
👍 9
በትልቅነቱ እና በልግስናው የሚያስደነግጠው መለኮት የሆነው እግዚአብሔር ወልድ ወደ  የሰው ልጅ መንደር ንቀት በማያቀው ቅርበቱ ከላይ ወደታች የሰው ህማም ሊካፈል ራሱን ቆረሰ ።

@cgfsd
👍 16
የአብ አባትን ልብ በልጁ ኢየሱስ ሰውን ፍለጋ ውስጥ አግኝተነዋል 😍 ።

@cgfsd
👍 16

Найдено 409 постов