Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
1.1K
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 497
Сегодня
-1
Просмотров на пост
Всего
423
ER
Общий
25.8%
Суточный
16.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 1 085 постов
Смотреть все посты
Пост от 02.06.2026 17:36
79
0
0
(መንፈሱና መስቀሉ )


በቆሮንቶስ መፀሃፍ ላይ መስቀል ጥበበ እግዚአብሔር ነው ። መስቀል በቆሮንቶስ መፀሃፍ ላይ እንዴት ተገለጠ ብንል ጥበብ እግዚአብሔር የሚለው መልስ ገላጭ ሁኖ እናገኘዋለን ። መስቀል የእግዚአብሔር አስደናቂ ጥበብ እንደሆነ ስዕል ይስልናል ። ጥበቡም የእግዚአብሔር ሃይል ፣ እቅድ ፣ ርህራሄ ፣ ማዳን ፣ ፍቅር ፣ቸርነት ፣ የፀጋውን ባለጠግነት ፣ ልብ የሚገልጥ ጥበብ ነው ። እግዚአብሔር ለአለሙ ምስቅልቅል የሰጠው መልስ በጥበብ ነው እርሱም መስቀል ነው ። ጥበብ እንደመሆኑ መጠን መስቀል በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ ያለው ምክር ለመረዳት መንፈስ ቅዱስ ያስፈልጋል ። መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ጥልቅ ነገር የሚገለጥበት የእውነት መንፈስ ነው ። ስለዚህ የጥበቡን ጥልቀት ለመረዳት የመንፈሱ እርዳታ ያስፈልጋል ። መግለጥ የመንፈሱ ስራ ነውና ።  በቆሮንቶስ መፀሃፍ የመስቀሉን ጥበብነት ሲገልጥ በአይን ያልታየ፣ በሰው ልብ ያልታሰበ(1ቆሮ 2:5) በማለት እቅዱ የእግዚአብሔር ብቻና አስደናቂ  እንደሆነ ይነግረናል።  መንፈሱን ደግሞ በመስቀሉ ዙሪያ የሚኖረው ሚና ገላጭ ነው ይለናል ።
 
  ይሁን እንጂ፣ እንደ ተጻፈው፣
“ዐይን ያላየውን፣
ጆሮ ያልሰማውን፣
የሰውም ልብ ያላሰበውን፣
እግዚአብሔር ለሚወዱት አዘጋጅቶአል፤”
እግዚአብሔር ግን ይህን በመንፈሱ አማካይነት ለእኛ ገልጦልናል።
መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራል።  በውስጡ ካለው ከራሱ መንፈስ በስተቀር ከሰው መካከል የአንድን ሰው ሐሳብ የሚያውቅ ማን አለ? እንደዚሁም ከእግዚአብሔር መንፈስ በስተቀር፣ የእግዚአብሔርን ሐሳብ የሚያውቅ ማንም የለም።
1 ቆሮንቶስ 2:9-11

   በነገራችን ላይ ይሔ ጥቅስ ስለ መስቀሉ እንደሚያወራ ልብ ማለት ያስፈልጋል ።

የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነውን የመስቀል ስራ በመንፈሱ አብሪነትና አስረጂነት ይብራራል ። ጥልቅ የመስቀሉን እውነት ለመረዳት የመንፈሱ አስረጂነት ያስፈልጋል ።


@cgfsd
2
🔥 2
Пост от 02.06.2026 08:10
125
1
3
የነርሲያው ቤኔዲክት ፀሎት


ቸርና ቅዱስ አባት ሆይ፤
ማንነትህ የማስተውልበት ጥበብ፣
አንተን የምረዳበት ብሩህ ልቡና
አንተን የምሻበት ትጋት
አንተን የምጠብቅበት ትዕግስት
አንተን የማይባቸው ዐይኖች
አንተን የማሰላስልበት ልብ
አንተን የማውጅበት ሕይወት
በመንፈስ ኋይልና በጌታችን
በኢየሱስ ክርስቶስ ስጠኝ ።

@cgfsd
14
🔥 3
👍 1
Пост от 01.06.2026 18:52
200
1
0
ፀጋ መቼም ቢሆን በኋጢያተኞች ላይ ፊቱ አይጠቁርም ፤ ለኋጢያት ደግሞ ፊቱ ፈገግ አይልም።

በርናባስ ዘመኔ
@cgfsd
17
🔥 8
Пост от 01.06.2026 13:01
240
0
0
(ፍቅር ያልታየበት ቦታ የለም)


አለም ሳይፈጠር በፊት እግዚአብሔር ሰው ፈጥሮ በስላሴ መካከል ያለውን ፍቅሩን ሊያካፍል ሲያስብ ፍቅሩ መወደዱ ታየ ።

ሰውን በመልኩና በአምሳሉ ሲፈጥር የመውደዱ ብዛት ፍቅሩ ታየ ።

ሰው በሀጢያት ሲወድቅ ለማዳን ተስፋ ሰጥቶ የሰውን ልጅ ሲቀርብ፣ተስፋ ሲሰጥ፣ የወደቀውን ሰው ደጋግሞ ሲቀርብ ፍቅሩን አሳየን ።

የእስራኤልን ህዝብ ጠርቶ ለአህዛብ ካህን አድርጎ ሲጠራ አለምን እንደወደደ እንደማይተው ፍቅሩን ታየ ።

አምላክ ሰው ሲሆን የሰውን ችግር ሲካፈል አ ሰው ሆኖ አብዝቶ ሰው ጋር በቅርበት ሲኖር ፍቅሩ ታየ ።

በመስቀል የውርደትን ሞት ሲሞት እስከምንድረስ ሰው እንደሚወድ ፍቅሩን ከፍ አድርጎ አስረዳን ።

በትንሳኤው በተስፋ ሞልቶን ከሞት ባሻገር አለምና ህይወት እንዳለ የፍቅርን ተስፋ አሳየን።

በክብር አርጎ ተመልሶ እንደሚመጣ በፍቅር አብረነው እንደምንኖር ፣ መንፈሱን እንደሚልክልን ፣ ካህን እንደሚሆነን በፍቅር ቋንቋ አወራን ።

በሰማይ ሊቀካህን በመሆን ወክሎን ሰማይ ስለእኛ ያለ ደጀን ፣ ጌታም አገልጋይ፣ የሚማልድ ፣ የሚራራ ፣ በሰማይ ያለ ወዳጅ ሆኖን ፍቅሩን አፀናልን ።

መንፈሱን አፈሰሰልን ፣ መንፈሱም አፅናኝ ፣ አብሮ የሚኖር  ፤ ይሔን ፍቅር በውስጣችን አፈሰሰው ፍቅሩን ደጋግሞ ሲያካፍለን ፍቅሩን አየን ።

ዳግም ተመልሶ በክብር ሲመጣልን ያኔ አብረነው ስንኖር ፍቅሩ ዘወትር መገረማችን ሲሆን ለዘላለም በፍቅሩ ስንሸፈን ድንቅ ፍቅሩ በዘላለም ውስጥ በግልፅ ይታየናል ።

   ፍቅሩ ያልታየበት ቦታ የለም !!!

@cgfsd
15
Пост от 29.05.2026 14:50
334
0
0
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ነባቤ_መለኮት (St. Gregory of Nazianzus)

​"እኛ የጰንጠቆስጤን በዓል እናከብራለን፤ የመንፈስ ቅዱስንም መውረድ እናከብራለን። ተስፋ የተሰጠበት ቀን መፈጸሙን አይተን ደስ ይለናል። መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜም ነበረ፣ አለ፣ ይኖራልም። መጀመሪያ የለውም፣ ፍጻሜም የለውም። እርሱ ሁልጊዜ ከአብ እና ከወልድ ጋር አንድ ነው... እርሱ ብርሃን ነው፣ ሕይወት ነው፣ የሕይወትም ምንጭ ነው።"
10
Пост от 27.05.2026 19:14
826
0
5
20
🔥 4
Пост от 27.05.2026 10:17
438
0
1
(የመስቀሉ አሰላሳይ )


መስቀሉ በተደጋጋሚ አስበው ካሳሰቡን ሰዎች መካከል ዘማሪ አዲሱ ወርቁ አንዱ ናቸው ። ጋሽ አዲሱ መዝሙራቸው የመስቀሉን ፍቅር እንድናስብ የሚጋብዝ በጥልቀት የታሰበ መንፈሳዊ ስራዎች ናቸው ። በሁለቱ አልበም መዝሙሮች ውስጥ በርካታ የመስቀሉ ስራዎች ታጭቀው እናገኛለን ። የአልበም መዝሙር ስራዎች ርዕስ ራሱ የመስቀሉ ፍቅር ይሰኛል ።

አንድ ጊዜ ኮብልላ ነበረ ነፍሴ ከእግዜር መንገድ .... ደሙን ለእኔ አፍስሶ አዳነኝ ...የሚለውን መዝሙር በሬዲዮ አፄ-ሀይለስላሴ ይሰማሉ ። ዘማሪውን አዲሱ ወርቁ በዛ መከራ ዘመን አስጠርተው አበረታቱት(የተጠራ ህይወት መጋቢ መርዕድ ለማ) ። ምን ያህል ዘመን ተሻጋሪ ለሁሉም ሰው መሆን የሚችል መዝሙር እንደሆነ ከዚህ ታሪክ መረዳት እንችላለን ።

ጋሽ አዲሱ የመስቀል ፍቅሩን እንጨት ላይ የሆነ አንድ ክስተት አርገው አያዩትም ። የእግዚአብሔር መንግስት እቅድ ፣ የአማኝ ህይወት ላይ የዕለት ዕለት ጉልህ ተፅዕኖ ያለው የእግዚአብሔር የልብ ምክር አደርገው ያቀርቡናል ፤ በዚህ ብቻ ሳይሆን አማኝ ደጋግሞ የመስቀል ፍቅሩን ማሰብ ማሰላለሰል እንደሚገባው ይጠቁማሉ። ሌላኛው በመዝሙራቸው ውስጥ የመስቀሉ ስራ ወደ ምስጋና ሲያመራቸው እናያልን ። የተዋጀ ሰው ምስጋና ፣ የዳነ ሰው ምስጋና አላቸው  ።  ምስጋናው ውስጥ መገረም ፣ መደነቅ ይታይባቸዋል ።
"
የነፍሳት ሁሉ ምስጋና ዙፋንህን ይክበበው
በቸርነትህ ተገርሟል  በልጅህ የዋጀኸው"

ምስጋናቸው መገረም ብቻ አይደለም ። በተግባራዊ የሆነ ምድር ላይ የወረደ መሆን እንዳለበት ፍንጭ ይሰጡናል ።
      " ጌታዬን አከብራለሁ ጌታዬን አከብራለሁ
                   በኑሮዬ ..................."

የጋሽ አዲሱ ወርቁ መዝሙሮች የመስቀሉን ፍቅር በማሰላለሰል ፣ የእግዚአብሔር ፍቅር በመረዳት ተግባራዊ የሆነ ህይወት ለመኖር ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ጥልቅ ህብረት እንዲኖር ጥሪ ያቀርብናል ። መዝሙሮቹን እንድትሰሙት አበረታታለሁ🙌 ።


@cgfsd
17
🥰 2
Смотреть все посты