Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
736
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 391
Сегодня
+12
Просмотров на пост
Всего
368
ER
Общий
25.45%
Суточный
13.9%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 736 постов
Смотреть все посты
Пост от 10.01.2026 08:57
163
0
1
(ፀጋ እንደ ውሃ ) ተወዳጁ ፊሊፕ ያንሲን የወንጌላዊያን ፀሃፊና አስተማሪ ነው። በሁሉም አለም ማለት በሚቻል መልኩ መፀሃፉ ተደራሽ ነበር ።   ወንጌላዊው ቢሊግርሃም ከፀሃፊዎች መካከል ፊሊፕ ያንሲን የምወደው ፀሃፊ ነው በማለት በመፀሃፉ ላይ አስተያየት ሰጥቷል ። ቅይማት ፣ ያላወኩት ኢየሱስ ፣ ፀሎት በእውን ለውጥን ያደርጋል? የተሰኙ መፀሃፎቹ ወደ አማረኛ ተተርጉመዋል ። በእነዚህ መፀሃፎች ተግባራዊ ህይወት የተሞገትንበትና ለመንፈሳዊ ህይወታችን የታነፀበት እንደሆነ የሁላችንም ሀቅ ነው ። ለመጀመሪያ ጊዜ ያነበብኩት" ያላወኩት ኢየሱስ" የተሰኘውን ነበር ። ኢየሱስን የቅርብ እንደሆነ በማንነቱ የተደነቁበትና የተገረምኩበት ስራ ነው ። በተለይ ልቤ ውስጥ የቀረ አንድ አባባል ነበረው " ኢየሱስ ተገናኝቶ እንደቀድሞ ሁኖ መኖር አይችልም " የሚለው ቃል በጣም ወድጄዋለው ። የኢየሱስ ማንነትና ስራ ብርቱ ለዋጭ መሆን ያስገነዝበናል ። ፍሊፕ እጅግ በጣም ተወዳጅ ብዙ ሰዎች የጠቀመ መንፈሳዊ ሰው ነው ። ከሰሞኑን የ75 አመቱ ፍሊፕ ያንሲን ስለ አንድ የህይወት ክፍሉ በግልፅ ተናገረ ። ቀድሞውንም ቢሆን ግልፀኝነት መታወቂያው ነው ። በአጭር ግለ ታሪክ ህይወቱ በፃፈበት ፅሁፍ ላይ ለራሱ ሳይሳሳ ፍርጥር አድርጎ ተናግሮ ነበር ። ሰሞኑን በተናገረው ላይ የበለጠ ራሱ ላይ ያለውን ክፍተት አጋራ ። ከ55 አመት አካባቢ የሚጠጋ የትዳር ቆይታ ውስጥ አለ ግን በዚህም ውስጥ ሁኖ  ያለፉትን ስምንት አመታት ከሌላ ሴት ከትዳር ውጭ ይሄድ እንደነበረ ተናገረ ። ራሱን ለማየት ከብዙ ነገር አግልሎ ለመመለስ እንደሚፈልግ ተናገረ ። ባለቤቱም ይቅርታ እንደምታደርግ ይሔ የክርስቶስ ያሳየው የፍቅር ባህሪ ነው አለች ። ፍሊፕ ወደ ፊት በመውጣት በህይወት እያለ ለእግዚአብሔርና ለህዝብ ያለውን ክብር አሳይቷል። ዘሪቱም ከበደ በድፍረት የፀጋውን ጥንካሬ ያለፍራቻ ድካሟንና ውድቀቷን በመናገር ፀጋው እንዳገዛት ለራሷ ለክብሯ ሳትሳሳ በግለ ታሪኳ አሳይታን ነበር። ሀጢያት በጨለማ ውስጥ ሲደበቅ ይፋፋል ለሀጢያት ምቹ ቦታ ጨለማ ነው ድብቅ መሆኑ ፤ ብርሃን ደግሞ ያከስመዋል የእግዚአብሔር እውነት በዛ ስላለ ። አስቀድሞ ፊሊፕ ፀጋን በውሃ ምሳሌ አርጎ አውርቶናል ። " ፀጋው እንደ ውሃ ነው ዝቅ ወዳለው ስፍራ ይፈሳል " ። እውነት ከፍ ካለው አምላክ ዝቅ ወዳለው ወደ ትሁቱ ፣ ወደ ተሰበረው ፣ ለደከመው ፣ አቅም ወደሌለው ወደ ታች ቁልቁል ይፈሳል። ዝቅ ላለው ይበዛለታል ። ፊሊፕ ራሱን ዝቅ አድርጓል ። ለደከመው ወደ ፀጋው ዙፋን ተመላለሱ ያለው አምላክ ይረዳዋል ። ደጉ ጌታ ፀጋውን ለፍሊፕ ያብዛለት ። ፀጋው ግን እንደ ውሃ መፍሰሱን አያቆምም ከፀጋ በታች ካለን እናገኘዋለን ። ፀጋው ባይኖር ምን ይውጠን ነበር ? ስንት ጉድ ሸፈነልን ፣ ስንት ጉዳችን አስወገደልን ። የፀጋ ሁሉ አምላክ ይባረክ  ! ለፀጋው ክብር ምስጋና ይሁንለን ። @cgfsd
9
👍 2
🔥 1
Пост от 09.01.2026 09:11
222
0
0
       (#ቃል ክርስቶስ) - የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ 1 ክፍል 1 የዩሀንስ ወንጌል አራተኛ የወንጌል መፀሃፍ ነው ። በርካቶች ዘንድ ተወዳጅ ተነባቢ በተደጋጋሚ የሚነሳ የቅዱሳት መፀሃፍ ክፍል ነው ። ዩሀንስ ወንጌል ከባድም ቀላልም ነው ። ጥቅል የሆኑ የክርስትና ትምህርቶች አሉበት ደግሞ ተግባራዊ ህይወት ይስተዋልበታል ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ሰፋ ያሉ ቁጥሮችንና ሀሳቦችን አካቶ ይዟል ። የምዕራፍ አንድ አተራረክ ከዘፍጥረት አንድና ከኢዮብ መፀሃፍ አንድ ጋር የሚያመሳስሉት ብዙ ሰዎች አሉ ። ከዘፍጥረት አንድ ጋር በንፅፅር ያስቀምጡታል ። የዘፍጥረት መፀሃፍ አጀማመሩ ከፍጥረት አጀማመር ያሳያል ። የዩሀንስ ወንጌል ደግሞ ከፍጥረት ጅማሬ በፊት ስለነበረው የሁሉ አስጀማሪው ስለሆነው ዘላለማዊ አምላክ ይናገራል ። በዚህ ንፅፅር መልክ የዩሀንስ ወንጌል ከዘፍጥረት እየተነፃፀረ ለመረዳት ይሞከራል ። የኢዮብ መፀሃፍ ደግሞ በምዕራፍ አንድ ላይ ኢዮብ ከመጣበት መከራ በፊት ስለመጣበት የመከራው ምክኒያት በትረካ መልክ መፀሃፉን ስናነብ እንመለከታለን ። በዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ቁጥር ሃያ ዘጠኝ ላይ ኢየሱስ ስለሚመጣበት የመከራ ምክኒያት ስለሚቀበለው መከራ " የአለምን ሀጢያት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ " ተብሎ ሲጠራ እናያለን ።  የሚመጣበትን  መከራ ምክኒያት የአለምን ሀጢያት ለማስወገድ እንደሆነ በክፍሉ ይገለፃል ። ከሚመጣበት መከራ በፊት ለምን መከራውን እንደሚቀበል አስረድቶን ያልፋል በዚህ ከእዮብ መፀሃፍ ጋር በንፅፅር ለመረዳት ሲሞከር ይስተዋላል ። የዘፍጥረትና የኢዮብ መፀሃፍ ሲተረጎሙ እንደ ዩሀንስ ወንጌል አንድ ነው ለማለት ሳይሆን ለንፅፅር በማቅረብና በተሻለ መልኩን ዩሀንስ ወንጌል ለመረዳት እንደ መነሻ ስለሚያገለግሉ ነው ። የዩሀንስ ወንጌል በዚሁ በምዕራፍ አንድ ስለ ዘላለማዊ ከምንም ነገር በፊት ስለነበረው  ስለ ቃል አምላክ (1:1) ፣ ስለፍጥረት መፈጠርና በቃል(ክርስቶስ) ስለመፈጠራቸው(1:4) ፣  ስጋ ስለበሰው ሰው ስለሆነው ቃል ክርስቶስ (1:14)፣ በብሉይ ኪዳን እየመጣ ሰውን ስለሚጎበኘው ቃል(1:9) ፣ የስላሴ ወኪል ስለሆነው አባቱን ስለሚያብራራው ቃል ክርስቶስ (1:18)፣ ለሞትና መከራን ለመቀበል ስለተዘጋው የእግዚአብሔር በግ ( 1:29-1:35) ፣ ደቀመዛሙር ስላስከተለው ረቢ መምህር (1:36) በስፋት ይነገራል ። በአጠቃላይ የክርስቶስ ዘላለማዊነት የሚያሳይ ፤ይሔም ዘላለማዊነት ክርስቶስ ከአባቱ ጋር ዘላለማዊ ያለህብረት ያለው መሆኑ ፣ ስለ ክርስቶስ ፈጣሪነት የሚያሳይ ፣ በፍጥረቱ መካከል ያለ መሆን የሚናገር ፣ ፍጥረቱ መሃል መሆኑ ብቻም ሳይሆን ሰው በመሆን የበለጠ የሰው ወገን የሆነ ፣ መከራን ለመቀበል የተዘጋጀ በግ መሆኑን ፣ ደቀመዛሙር በማስጠጋት መከተል የተባለ ህይወት እንዳለ እሱን በተግባር የመምሰል የመከተል ጉዞ እንዳለ ይታያል ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ሰፊ የሆነ የክርስቶስ የማንነትና ስራ የሚተረክበት አስደናቂ ምዕራፍ ነው ። @cgfsd
🔥 9
5
👍 1
Пост от 06.01.2026 14:37
361
0
3
(የብሉይ ኪዳንና የአዲስ ኪዳን ተዛምዶ) የብሉይ ኪዳንና የአዲስ ኪዳን መፀሃፍ ቅርብ የሆነ ዝምድና አላቸው ። በተለምዶ ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳንን ውስጥ ያሉ ክፍሎች ባለፈ የኪዳን ምልክቶች ተደርገው ይወሰዳሉ ። በዚህ ፅሁፍ ለመዳሰስ የምንሞክረው በብሉይና አዲስ ኪዳን መፀሃፍ መካከል ያለውን ትስስር ይሆናል ። መፀሃፍ ቅዱስ መጥቀስ በራሱ መፀሃፍ ቅዱሳዊ ነው ። መፀሃፍ ቅዱስ ክፍሎች ለማብራራት ራሱን መፀሃፍ ቅዱስ መጠቀም የመፀሃፍ ቅዱሳችን ባህሪ ነው ። የመፀሃፍ ቅዱስ ኮመንተሪ ራሱ መፀሀፍ ቅዱስ ነው እንደሚባለው ማለት ነው ። የብሉይ ኪዳን የአዲስ ኪዳን መፀሃፍት መካከል ያለው ዝምድና አንዱ ማሳያ የብሉይን ሀሳብ በአዲስ ኪዳን ውስጥ በመጥቀስ በመደገፍ እንደሆነ መረዳት ይቻላል ። በአዲስ ኪዳን ላይ ራሱ ጌታ ኢየሱስ የብሉይን መፀሃፍት ሲያስተምር ፣ ለአገልግሎቱ መጀመሪያ መነሻ ሲያደርግ እንመለከታለን ። ጌታ ኢየሱስ አገልግሎቱ ሲጀምር በምኩራብ በትንቢተ ኢሳያስ 61 ያለውን የመፀሃፍ ሀሳብ በማንበብ አገልግሎቱን አበሰረ (ሉቃስ 4) ። ሐዋሪያት የመንፈስ ቅዱስን መውረድ በበአለ ሃምሳ ቀን ሲያስረዱ (ሐዋ2) በትንቢተ እዮኤል 2:20 ያለውን ትንቢታዊ ቃል እንደተፈፀመ መፀሃፍ ቅዱሳዊ መልስ ሰጡ ። በመቀጠል ሐዋሪያው ጴጥሮስ የክርስቶስ ትንሳኤ ለማስረዳት መዝመሩ ዳዊትን እንደ አብነት አነሳ ። ሐዋሪያው ጳውሎስም ስለ ክርስቶስ ውልደት ፣ ሞትና ትንሳኤ ለመግለፅ መፀሃፍ እንደሚል የሚል አገላለፅ ተጠቀመ (1ቆሮ 15:3) ። ከዚህም የምንረዳው የብሉይና አዲስ ኪዳን ተዛምዶ ነው ። የብሉይ ኪዳን መፀሃፍት ላይ በዚህ ዘመን ጥቃት ይበዛበታል ። በአግባቡ አይተረጎምም ወይም ብሉይን ለመረዳትና ለማንበብ ፍላጎት አይኖረንም ። ጌታ ኢየሱስ ሆነ ሐዋሪያት የብሉይ ኪዳን መፀሃፍ ከተጠቀሙበት እኛም ልንጠቀምበት ይገባል ። ብሉይ ኪዳንን ለመረዳት አዲስ ኪዳንን፣ አዲስ ኪዳንን ለመረዳት ብሉይ ኪዳንን መፀሃፍት መረዳት ያስፈልገናል ። የእግዚአብሔር ሙሉ የሆነ የመዋጀት ፣ የማዳን ታሪክ ለመረዳት ሁለቱም ያስፈልጉናል ። ኦገስቲን እንደሚለው ብሉይ ኪዳን ቤቱ ነው አዲስ ኪዳን ደግሞ መብራቱ ነው ። ስለዚህ የሁለቱንም አስፈላጊነት መረዳት እንችላለን ። በስብከቶቻችን ፣ መፀሃፍ ቅዱስ ጥናቶቻችን አንድ ላይ ብናጠናቸውና ትኩረት ብናደርግባቸው በተሻለ መልኩ የእግዚአብሔር ሀሳብ ከመፀሃፍ ቅዱሳችን መገንዘብ እንችላለን ። @cgfsd
14
🔥 2
Пост от 06.01.2026 00:09
395
0
1
(ሥላሴያዊ አምልኮ) የክርስትና ትምህርት ሁሉ ምንጭ ሥላሴ ነው ። የትምህርቶችና የአስተምሮዎች ሁሉ ቁንጮ ሥላሴ ካልሆነ ምን ሊሆን ይችላል? በሥላሴ አማኞች  ላይ ከሚነሱ ጥያቄዎች መካከል ቃል በቃል ሥላሴ የሚለው ቃል በመፀሃፍ ቅዱሳችን አለ ወይ ? የሚል ነው ። ለዚህ ሀሳብ ብዙ ርቀት ሳንሄድ የምንሰጠው መልስ ግልፅ ነው ቃል በቃል ባይኖርም  አስተምሮው በመፀሃፍ ቅዱሳችን ስላለ እናምናለን ። ሥላሴ ሶስትነት የሚል ትርጓሜው አለው ። ስላሴ ስንል በሶስት አካል የሚኖር አንድ አምላክ ነው ። የማይደባለቅ ሶስትነት የማይነጠል አንድነትን ያሳያል ። በስም ፣ በግብር ፣ በአካል ሶስት ደግሞ በመለኮነት  በባህሪ አንድ አምላክ ። ያለን አንድ አምላክ እንጂ ሶስት አይደለም ። ነገር ግን ሶስት አካላት አሉ ግን አንድ ባህሪ ያለው አንድ አምላክ ። ሥላሴን ስናስብ የማንደባልቀው ሶስትነትና የማንከፋፍለውን አንድነት ለይተን ማወቅ አለብን ። ወደ ክርስቲያናዊ ኑሮአችንና አምልኮአችን ስንመጣ የማይነጣጠለው አንድነት የማይደባለቀውን ሶስትነት መሰረትና ማዕከል ማድረግ አለብን ። ገና ሰው ከፈጠረበት የፍጥረት ጅማሪ አንስቶ የተፈጠረው በሥላሴ ምክር ነው፤ ኑ በመልካችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር በሚል መነሳት ነው ። ፍጥረቱን በሥላሴ ነው የሆነው ። የሰው ፍጥረት ሥላሴያዊ ነው ። ሰው በሀጢያት ከወደቀ በኋላ ሰውን ለማዳን የተሰራው የማዳን ስራም ሥላሴያዊ ነው ። አብ ልጁን በመስጠት ፣ ልጁ ራሱን በመስጠት ፣ መንፈስ ቅዱስ የተሰራውን ስራ በመፈፀም የተደረገው የመዳን ምክኒያቱም አድራጎቱም ሥላሴያዊ ነው ። ፍጥረታችን ሥላሴያዊ እንደሆነ ሁሉ መዳንችንም ሥላሴያዊ ነው ፤ ስለዚህ ከዳንን በኋላ ያለን አምልኮም ሆነ ከአምላክ ጋር ያለን ህብረት ሥላሴያዊ መሆን አለበት ። አንዳንድ መንፈሳዊ ህብረቶቻችን ውስጥ የሚስተዋለው የአምልኮ ወይም መንፈሳዊ ተግባራችን አንደኛውን የሥላሴ አካል ላይ ብቻ የሆነ ሌላውን የረሳ ይመስላል ። ክርስቶስን ማዕከል ማድረግ ማለት የአብን አባትነትና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለን ህብረት እርግፍ ማድረግ አይደለም ። እንደውም ክርስቶስን ማዕከል ማድረግ ልከኛ የሚሆነው ለአብ ክብር በመንፈስ ቅዱስ ሃይል የሆነ ሲሆን ነው ። አብንና መንፈስ ቅዱስን ያገለለ ክርስቶስን ማዕከል ማድረግ ክርስቶስ ማዕከል ማድረግ አይደለም ።  በሌላው ጎን መንፈስ ቅዱስ መጠማት ከእርሱ ጋር የሚኖርን ህብረት መለማመድ አብንና ወልድ በመፀሀፍ ቅዱስ እንደሚለው ትኩረት ያደረገ ካልሆነ መስመር ሊለቅ ይችላል ። መንፈስ ቅዱስ ጋር የሚኖር ህብረት ክርስቶስን ማዕከል ያደረገና ለአብ ክብር የሆነ የሚሆን ከሆነ ትክክለኛ ህብረት ይሆናል ።  መንፈሳዊ ልምምዶቻችን መፀሃፍ ቅዱስ እንደሚለን ሥላሴያዊ መሆን አለበት ። ሶስትም አንድም ነው እግዚአብሔር ! በመሆኑም ሶስትነቱ በመፍጠር ፣ ሰውን በማዳን ካልተጋጨ እኛ በአምልኮ ስርአታችንና በመንፈሳዊ ልምምዳችን አንደ መፀሃፍ ቅዱሳዊ አማኝ ሊጋጭብን አይችልም ። እውነተኛ መንፈሳዊ ህብረትና ልምምድ ሥላሴያዊ ነው ። @cgfsd
10
🔥 4
👍 1
Пост от 04.01.2026 10:48
394
0
4
ዘወትር በፀሎት በፊትህ ልደፋ በውስጤ ያኖርከው እሳቱ እንዳይጠፋ ገና ላገልግልህ  በኋይል ተሞልቼ ጉብዝናዬን ሁሉ  ለአንተ ሰጥቼ 🎶 what a song 😭
🔥 17
10
😢 2
Пост от 04.01.2026 08:56
393
0
8
ጌታ ይባርካችሁ !! ከውስጤ ተረበሸ ታሪክ ላይ የተዘመረው መዝሙር ። @cgfsd
Видео/гифка
🔥 10
5
Пост от 04.01.2026 00:39
550
0
9
(ውስጤ ተረበሸ) አይ ወንጌል !! ቁር ያዝ ያደረገው ብርዳማ ቀን ነበር ። በገደብ ከተማ የመፀሃፍ ቅዱስ ትምህርት ይሰጣል። ለፕሮግራሙ አረፋፍጄ ነበር የደረስኩት ። ሰአት ስለሄደ በቀጥታ ወለም ዘለም ሳልል ወደ ትምህርቱ የገባነው ። የተለያዩ አይነት ሰዎች በመንፈሳዊ ርሃብ ሳቢያ ተሰብስበዋል ። አንድ አባት ትምህርት ከሚከታተሉት መካከል በልዩነት ትኩረት ይስባሉ ። ማስተማር ከተጀመረበት ሰአት ጀምሮ በእንባ ነው የሚከታተሉት ። የሚከታተሉበት ንቃት ቢያስገርምም እንባቸው ስለተደጋገመብኝ ሰረቅ ሰረቅ እያደረኩ አያቸዋለሁ ። ሳልዋሽ በውስጤ ለጌታ ነው እያልኩ ቅዱስ ቅናት እየቀናሁም ነበር ። ፕሮግራማችን ስንጨርስ ወደኋላ ቀርተው ጠበቁኝና በስም ተዋወቅን ። እንባቸው አሁን አልደረቀም ፊታቸው ላይ ይተራመሳል ። ጌታ ይባርክህ ልልህ የቀረሁት ፤ ግን ጌታ ይባርክህ ልል ሳስብ ከዛሬ 16 አመት በፊት ለወንጌል ስራ ወደ ሌላ አካባቢ ባለቤቴን እንሂድ ስላት እንቢ ብላ ተቃወመችኝ ። ስንከራተት ኖርን አሁን ከእዚህ አልንቀሳቀስም አለችኝ ። ያኔ የዘመርኩት መዝሙር ትዝ አለኝ ልዘምርልህ ብለው አዝማቹን እንዲህ ተቀኙልኝ    "ወንጌል ይዛችሁ የምትሄዱ      አስቸጋሪ ቢሆንም መንገዱ      የኋላ የኋላ አክሊል  አለ      ለእግዚአብሔር የሚሳነው የታለ      ጌታ ይባርካችሁ (2)       ፀጋውን ያብዛላችሁ " እንባቸው እየጠራረጉ ጌታ ይባርክህ ብለው ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ተነሱ ፕሮግራም ስንጨርስ መሽቷል ። አንድ ሰአት መንገድ አለብኝ ብለው ተሰናበቱኝ ። ነገ ፕሮግራማችን ላይ ይዘምሩን ስላቸው ደስ እያላቸው ክራር ይዘው እንደሚመጡ ነግረውኝ እንባቸውን ጠራርገው ሄዱ ። በነገታው በጠዋት የአንድ ሰአት ሩቅ ከነበረው ቤታቸው ቀድመውን መጥተዋል ። ከጎናቸው ክራራቸውን እንደ ከዘራ ደገፍ አረገው ይዘው ጠበቁን ። ዛሬም በእንባ ነው ትምህርቱ ሲጀመር ጀምሮ የሚከታተሉት በልባቸው እየተደነኩ በራሴ እያፈርኩ ትምህርቱን ቀጠልን ። በተነጋገርነው መሰረት ክራራቸውን አስተካከለው ከልጃቸው ጋር ሁለት መዝሙር በእንባ ዘመሩልን ። በርካታ አመታት ወንጌል ሰርቻለሁ አሁን ግን የበለጠ ውስጤ ተረበሸ አሉን ። በእንባ ዘመሩ ጉባኤውም በእንባ አብሮ ወንጌልን በመውደድ ርሃብ አብሯቸው ቀለጠ ። ጌታን እንደዚህ የሚወዱ ለእግዚአብሔር አጀንዳ ሽንፍ ያሉ ውስጤ ተረበሸ የሚሉ ሰዎች አሉ ። ጌታ እንዲህም ይናፈቃል ። @cgfsd
14
🔥 7
😢 5
🥰 1
Смотреть все посты