Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
697
334
3
0
7.3K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 377
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
383
ER
Общий
24.97%
Суточный
14.3%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 697 постов
Смотреть все посты
Пост от 09.01.2026 09:11
154
0
0
       (#ቃል ክርስቶስ) - የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ 1 ክፍል 1 የዩሀንስ ወንጌል አራተኛ የወንጌል መፀሃፍ ነው ። በርካቶች ዘንድ ተወዳጅ ተነባቢ በተደጋጋሚ የሚነሳ የቅዱሳት መፀሃፍ ክፍል ነው ። ዩሀንስ ወንጌል ከባድም ቀላልም ነው ። ጥቅል የሆኑ የክርስትና ትምህርቶች አሉበት ደግሞ ተግባራዊ ህይወት ይስተዋልበታል ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ሰፋ ያሉ ቁጥሮችንና ሀሳቦችን አካቶ ይዟል ። የምዕራፍ አንድ አተራረክ ከዘፍጥረት አንድና ከኢዮብ መፀሃፍ አንድ ጋር የሚያመሳስሉት ብዙ ሰዎች አሉ ። ከዘፍጥረት አንድ ጋር በንፅፅር ያስቀምጡታል ። የዘፍጥረት መፀሃፍ አጀማመሩ ከፍጥረት አጀማመር ያሳያል ። የዩሀንስ ወንጌል ደግሞ ከፍጥረት ጅማሬ በፊት ስለነበረው የሁሉ አስጀማሪው ስለሆነው ዘላለማዊ አምላክ ይናገራል ። በዚህ ንፅፅር መልክ የዩሀንስ ወንጌል ከዘፍጥረት እየተነፃፀረ ለመረዳት ይሞከራል ። የኢዮብ መፀሃፍ ደግሞ በምዕራፍ አንድ ላይ ኢዮብ ከመጣበት መከራ በፊት ስለመጣበት የመከራው ምክኒያት በትረካ መልክ መፀሃፉን ስናነብ እንመለከታለን ። በዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ቁጥር ሃያ ዘጠኝ ላይ ኢየሱስ ስለሚመጣበት የመከራ ምክኒያት ስለሚቀበለው መከራ " የአለምን ሀጢያት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ " ተብሎ ሲጠራ እናያለን ።  የሚመጣበትን  መከራ ምክኒያት የአለምን ሀጢያት ለማስወገድ እንደሆነ በክፍሉ ይገለፃል ። ከሚመጣበት መከራ በፊት ለምን መከራውን እንደሚቀበል አስረድቶን ያልፋል በዚህ ከእዮብ መፀሃፍ ጋር በንፅፅር ለመረዳት ሲሞከር ይስተዋላል ። የዘፍጥረትና የኢዮብ መፀሃፍ ሲተረጎሙ እንደ ዩሀንስ ወንጌል አንድ ነው ለማለት ሳይሆን ለንፅፅር በማቅረብና በተሻለ መልኩን ዩሀንስ ወንጌል ለመረዳት እንደ መነሻ ስለሚያገለግሉ ነው ። የዩሀንስ ወንጌል በዚሁ በምዕራፍ አንድ ስለ ዘላለማዊ ከምንም ነገር በፊት ስለነበረው  ስለ ቃል አምላክ (1:1) ፣ ስለፍጥረት መፈጠርና በቃል(ክርስቶስ) ስለመፈጠራቸው(1:4) ፣  ስጋ ስለበሰው ሰው ስለሆነው ቃል ክርስቶስ (1:14)፣ በብሉይ ኪዳን እየመጣ ሰውን ስለሚጎበኘው ቃል(1:9) ፣ የስላሴ ወኪል ስለሆነው አባቱን ስለሚያብራራው ቃል ክርስቶስ (1:18)፣ ለሞትና መከራን ለመቀበል ስለተዘጋው የእግዚአብሔር በግ ( 1:29-1:35) ፣ ደቀመዛሙር ስላስከተለው ረቢ መምህር (1:36) በስፋት ይነገራል ። በአጠቃላይ የክርስቶስ ዘላለማዊነት የሚያሳይ ፤ይሔም ዘላለማዊነት ክርስቶስ ከአባቱ ጋር ዘላለማዊ ያለህብረት ያለው መሆኑ ፣ ስለ ክርስቶስ ፈጣሪነት የሚያሳይ ፣ በፍጥረቱ መካከል ያለ መሆን የሚናገር ፣ ፍጥረቱ መሃል መሆኑ ብቻም ሳይሆን ሰው በመሆን የበለጠ የሰው ወገን የሆነ ፣ መከራን ለመቀበል የተዘጋጀ በግ መሆኑን ፣ ደቀመዛሙር በማስጠጋት መከተል የተባለ ህይወት እንዳለ እሱን በተግባር የመምሰል የመከተል ጉዞ እንዳለ ይታያል ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ሰፊ የሆነ የክርስቶስ የማንነትና ስራ የሚተረክበት አስደናቂ ምዕራፍ ነው ። @cgfsd
🔥 7
4
👍 1
Пост от 06.01.2026 14:37
297
0
3
(የብሉይ ኪዳንና የአዲስ ኪዳን ተዛምዶ) የብሉይ ኪዳንና የአዲስ ኪዳን መፀሃፍ ቅርብ የሆነ ዝምድና አላቸው ። በተለምዶ ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳንን ውስጥ ያሉ ክፍሎች ባለፈ የኪዳን ምልክቶች ተደርገው ይወሰዳሉ ። በዚህ ፅሁፍ ለመዳሰስ የምንሞክረው በብሉይና አዲስ ኪዳን መፀሃፍ መካከል ያለውን ትስስር ይሆናል ። መፀሃፍ ቅዱስ መጥቀስ በራሱ መፀሃፍ ቅዱሳዊ ነው ። መፀሃፍ ቅዱስ ክፍሎች ለማብራራት ራሱን መፀሃፍ ቅዱስ መጠቀም የመፀሃፍ ቅዱሳችን ባህሪ ነው ። የመፀሃፍ ቅዱስ ኮመንተሪ ራሱ መፀሀፍ ቅዱስ ነው እንደሚባለው ማለት ነው ። የብሉይ ኪዳን የአዲስ ኪዳን መፀሃፍት መካከል ያለው ዝምድና አንዱ ማሳያ የብሉይን ሀሳብ በአዲስ ኪዳን ውስጥ በመጥቀስ በመደገፍ እንደሆነ መረዳት ይቻላል ። በአዲስ ኪዳን ላይ ራሱ ጌታ ኢየሱስ የብሉይን መፀሃፍት ሲያስተምር ፣ ለአገልግሎቱ መጀመሪያ መነሻ ሲያደርግ እንመለከታለን ። ጌታ ኢየሱስ አገልግሎቱ ሲጀምር በምኩራብ በትንቢተ ኢሳያስ 61 ያለውን የመፀሃፍ ሀሳብ በማንበብ አገልግሎቱን አበሰረ (ሉቃስ 4) ። ሐዋሪያት የመንፈስ ቅዱስን መውረድ በበአለ ሃምሳ ቀን ሲያስረዱ (ሐዋ2) በትንቢተ እዮኤል 2:20 ያለውን ትንቢታዊ ቃል እንደተፈፀመ መፀሃፍ ቅዱሳዊ መልስ ሰጡ ። በመቀጠል ሐዋሪያው ጴጥሮስ የክርስቶስ ትንሳኤ ለማስረዳት መዝመሩ ዳዊትን እንደ አብነት አነሳ ። ሐዋሪያው ጳውሎስም ስለ ክርስቶስ ውልደት ፣ ሞትና ትንሳኤ ለመግለፅ መፀሃፍ እንደሚል የሚል አገላለፅ ተጠቀመ (1ቆሮ 15:3) ። ከዚህም የምንረዳው የብሉይና አዲስ ኪዳን ተዛምዶ ነው ። የብሉይ ኪዳን መፀሃፍት ላይ በዚህ ዘመን ጥቃት ይበዛበታል ። በአግባቡ አይተረጎምም ወይም ብሉይን ለመረዳትና ለማንበብ ፍላጎት አይኖረንም ። ጌታ ኢየሱስ ሆነ ሐዋሪያት የብሉይ ኪዳን መፀሃፍ ከተጠቀሙበት እኛም ልንጠቀምበት ይገባል ። ብሉይ ኪዳንን ለመረዳት አዲስ ኪዳንን፣ አዲስ ኪዳንን ለመረዳት ብሉይ ኪዳንን መፀሃፍት መረዳት ያስፈልገናል ። የእግዚአብሔር ሙሉ የሆነ የመዋጀት ፣ የማዳን ታሪክ ለመረዳት ሁለቱም ያስፈልጉናል ። ኦገስቲን እንደሚለው ብሉይ ኪዳን ቤቱ ነው አዲስ ኪዳን ደግሞ መብራቱ ነው ። ስለዚህ የሁለቱንም አስፈላጊነት መረዳት እንችላለን ። በስብከቶቻችን ፣ መፀሃፍ ቅዱስ ጥናቶቻችን አንድ ላይ ብናጠናቸውና ትኩረት ብናደርግባቸው በተሻለ መልኩ የእግዚአብሔር ሀሳብ ከመፀሃፍ ቅዱሳችን መገንዘብ እንችላለን ። @cgfsd
14
🔥 2
Пост от 06.01.2026 00:09
343
0
1
(ሥላሴያዊ አምልኮ) የክርስትና ትምህርት ሁሉ ምንጭ ሥላሴ ነው ። የትምህርቶችና የአስተምሮዎች ሁሉ ቁንጮ ሥላሴ ካልሆነ ምን ሊሆን ይችላል? በሥላሴ አማኞች  ላይ ከሚነሱ ጥያቄዎች መካከል ቃል በቃል ሥላሴ የሚለው ቃል በመፀሃፍ ቅዱሳችን አለ ወይ ? የሚል ነው ። ለዚህ ሀሳብ ብዙ ርቀት ሳንሄድ የምንሰጠው መልስ ግልፅ ነው ቃል በቃል ባይኖርም  አስተምሮው በመፀሃፍ ቅዱሳችን ስላለ እናምናለን ። ሥላሴ ሶስትነት የሚል ትርጓሜው አለው ። ስላሴ ስንል በሶስት አካል የሚኖር አንድ አምላክ ነው ። የማይደባለቅ ሶስትነት የማይነጠል አንድነትን ያሳያል ። በስም ፣ በግብር ፣ በአካል ሶስት ደግሞ በመለኮነት  በባህሪ አንድ አምላክ ። ያለን አንድ አምላክ እንጂ ሶስት አይደለም ። ነገር ግን ሶስት አካላት አሉ ግን አንድ ባህሪ ያለው አንድ አምላክ ። ሥላሴን ስናስብ የማንደባልቀው ሶስትነትና የማንከፋፍለውን አንድነት ለይተን ማወቅ አለብን ። ወደ ክርስቲያናዊ ኑሮአችንና አምልኮአችን ስንመጣ የማይነጣጠለው አንድነት የማይደባለቀውን ሶስትነት መሰረትና ማዕከል ማድረግ አለብን ። ገና ሰው ከፈጠረበት የፍጥረት ጅማሪ አንስቶ የተፈጠረው በሥላሴ ምክር ነው፤ ኑ በመልካችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር በሚል መነሳት ነው ። ፍጥረቱን በሥላሴ ነው የሆነው ። የሰው ፍጥረት ሥላሴያዊ ነው ። ሰው በሀጢያት ከወደቀ በኋላ ሰውን ለማዳን የተሰራው የማዳን ስራም ሥላሴያዊ ነው ። አብ ልጁን በመስጠት ፣ ልጁ ራሱን በመስጠት ፣ መንፈስ ቅዱስ የተሰራውን ስራ በመፈፀም የተደረገው የመዳን ምክኒያቱም አድራጎቱም ሥላሴያዊ ነው ። ፍጥረታችን ሥላሴያዊ እንደሆነ ሁሉ መዳንችንም ሥላሴያዊ ነው ፤ ስለዚህ ከዳንን በኋላ ያለን አምልኮም ሆነ ከአምላክ ጋር ያለን ህብረት ሥላሴያዊ መሆን አለበት ። አንዳንድ መንፈሳዊ ህብረቶቻችን ውስጥ የሚስተዋለው የአምልኮ ወይም መንፈሳዊ ተግባራችን አንደኛውን የሥላሴ አካል ላይ ብቻ የሆነ ሌላውን የረሳ ይመስላል ። ክርስቶስን ማዕከል ማድረግ ማለት የአብን አባትነትና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለን ህብረት እርግፍ ማድረግ አይደለም ። እንደውም ክርስቶስን ማዕከል ማድረግ ልከኛ የሚሆነው ለአብ ክብር በመንፈስ ቅዱስ ሃይል የሆነ ሲሆን ነው ። አብንና መንፈስ ቅዱስን ያገለለ ክርስቶስን ማዕከል ማድረግ ክርስቶስ ማዕከል ማድረግ አይደለም ።  በሌላው ጎን መንፈስ ቅዱስ መጠማት ከእርሱ ጋር የሚኖርን ህብረት መለማመድ አብንና ወልድ በመፀሀፍ ቅዱስ እንደሚለው ትኩረት ያደረገ ካልሆነ መስመር ሊለቅ ይችላል ። መንፈስ ቅዱስ ጋር የሚኖር ህብረት ክርስቶስን ማዕከል ያደረገና ለአብ ክብር የሆነ የሚሆን ከሆነ ትክክለኛ ህብረት ይሆናል ።  መንፈሳዊ ልምምዶቻችን መፀሃፍ ቅዱስ እንደሚለን ሥላሴያዊ መሆን አለበት ። ሶስትም አንድም ነው እግዚአብሔር ! በመሆኑም ሶስትነቱ በመፍጠር ፣ ሰውን በማዳን ካልተጋጨ እኛ በአምልኮ ስርአታችንና በመንፈሳዊ ልምምዳችን አንደ መፀሃፍ ቅዱሳዊ አማኝ ሊጋጭብን አይችልም ። እውነተኛ መንፈሳዊ ህብረትና ልምምድ ሥላሴያዊ ነው ። @cgfsd
10
🔥 4
👍 1
Пост от 04.01.2026 10:48
365
0
4
ዘወትር በፀሎት በፊትህ ልደፋ በውስጤ ያኖርከው እሳቱ እንዳይጠፋ ገና ላገልግልህ  በኋይል ተሞልቼ ጉብዝናዬን ሁሉ  ለአንተ ሰጥቼ 🎶 what a song 😭
🔥 17
9
😢 2
Пост от 04.01.2026 08:56
367
0
8
ጌታ ይባርካችሁ !! ከውስጤ ተረበሸ ታሪክ ላይ የተዘመረው መዝሙር ። @cgfsd
Видео/гифка
🔥 10
4
Пост от 04.01.2026 00:39
500
0
9
(ውስጤ ተረበሸ) አይ ወንጌል !! ቁር ያዝ ያደረገው ብርዳማ ቀን ነበር ። በገደብ ከተማ የመፀሃፍ ቅዱስ ትምህርት ይሰጣል። ለፕሮግራሙ አረፋፍጄ ነበር የደረስኩት ። ሰአት ስለሄደ በቀጥታ ወለም ዘለም ሳልል ወደ ትምህርቱ የገባነው ። የተለያዩ አይነት ሰዎች በመንፈሳዊ ርሃብ ሳቢያ ተሰብስበዋል ። አንድ አባት ትምህርት ከሚከታተሉት መካከል በልዩነት ትኩረት ይስባሉ ። ማስተማር ከተጀመረበት ሰአት ጀምሮ በእንባ ነው የሚከታተሉት ። የሚከታተሉበት ንቃት ቢያስገርምም እንባቸው ስለተደጋገመብኝ ሰረቅ ሰረቅ እያደረኩ አያቸዋለሁ ። ሳልዋሽ በውስጤ ለጌታ ነው እያልኩ ቅዱስ ቅናት እየቀናሁም ነበር ። ፕሮግራማችን ስንጨርስ ወደኋላ ቀርተው ጠበቁኝና በስም ተዋወቅን ። እንባቸው አሁን አልደረቀም ፊታቸው ላይ ይተራመሳል ። ጌታ ይባርክህ ልልህ የቀረሁት ፤ ግን ጌታ ይባርክህ ልል ሳስብ ከዛሬ 16 አመት በፊት ለወንጌል ስራ ወደ ሌላ አካባቢ ባለቤቴን እንሂድ ስላት እንቢ ብላ ተቃወመችኝ ። ስንከራተት ኖርን አሁን ከእዚህ አልንቀሳቀስም አለችኝ ። ያኔ የዘመርኩት መዝሙር ትዝ አለኝ ልዘምርልህ ብለው አዝማቹን እንዲህ ተቀኙልኝ    "ወንጌል ይዛችሁ የምትሄዱ      አስቸጋሪ ቢሆንም መንገዱ      የኋላ የኋላ አክሊል  አለ      ለእግዚአብሔር የሚሳነው የታለ      ጌታ ይባርካችሁ (2)       ፀጋውን ያብዛላችሁ " እንባቸው እየጠራረጉ ጌታ ይባርክህ ብለው ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ተነሱ ፕሮግራም ስንጨርስ መሽቷል ። አንድ ሰአት መንገድ አለብኝ ብለው ተሰናበቱኝ ። ነገ ፕሮግራማችን ላይ ይዘምሩን ስላቸው ደስ እያላቸው ክራር ይዘው እንደሚመጡ ነግረውኝ እንባቸውን ጠራርገው ሄዱ ። በነገታው በጠዋት የአንድ ሰአት ሩቅ ከነበረው ቤታቸው ቀድመውን መጥተዋል ። ከጎናቸው ክራራቸውን እንደ ከዘራ ደገፍ አረገው ይዘው ጠበቁን ። ዛሬም በእንባ ነው ትምህርቱ ሲጀመር ጀምሮ የሚከታተሉት በልባቸው እየተደነኩ በራሴ እያፈርኩ ትምህርቱን ቀጠልን ። በተነጋገርነው መሰረት ክራራቸውን አስተካከለው ከልጃቸው ጋር ሁለት መዝሙር በእንባ ዘመሩልን ። በርካታ አመታት ወንጌል ሰርቻለሁ አሁን ግን የበለጠ ውስጤ ተረበሸ አሉን ። በእንባ ዘመሩ ጉባኤውም በእንባ አብሮ ወንጌልን በመውደድ ርሃብ አብሯቸው ቀለጠ ። ጌታን እንደዚህ የሚወዱ ለእግዚአብሔር አጀንዳ ሽንፍ ያሉ ውስጤ ተረበሸ የሚሉ ሰዎች አሉ ። ጌታ እንዲህም ይናፈቃል ። @cgfsd
14
🔥 7
😢 5
🥰 1
Пост от 02.01.2026 13:10
390
0
0
(መለኮታዊ ሰብአዊ) የመፀሃፍ ቅዱስን ባህሪ በተመለከተ ማወቅ ካሉብን ነገሮች መካከል መለኮታዊም ሰብአዊ መሆኑን ነው ። ይሔ የመፀሃፍ ቅዱስ ባህሪ በቀላሉ መፀሃፍ ቅዱሳችን ለመረዳት ትክክለኛና ህብረት እንዲኖረን ይረዳናል ። በተቃራኒው ደግሞ ይሔን ባህሪው መረዳትና መገንዘብ ከተሳነን ለመፀሃፍ ቅዱስ ሀሳብ ሩቅ እንደሆናለን ። መፀሀፍ ቅዱስ መለኮታዊ ነው ሲባል በእግዚአብሔር ምሪት የተፃፈ ፣ እስትንፈሳ እግዚአብሔር ያለበት ቅዱስ ቃል ነው ። በእግዚአብሔር መንፈስ ምሪት የተከናወነ በእግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ የመለኮት ስራና እስትንፈስ ያለበት እንደሆነ መገንዘብ እንችላለን ።  መፀሃፍ ቅዱሳችን ሰብአዊ ነው ስንል ደግሞ ሰዋዊ ባህሪም እንዳለው መረዳት እንችላለን ። የእግዚአብሔር ሀሳብ ቢሆንም በሰው እጅ ፣ ቋንቋ ፣ ባህል ፣ አኗኗር ፣ ልማድ ፣ ወግና ታሪክ የተፃፈ ነው ። እነዚህ ነገሮች መፀሃፍ ቅዱስ ሰብአዊም ባህሪ እንዳለው ያረጋግጡልናል ። መፀሀፍ ቅዱስ ሰብአዊ ባህሪ አለው ስንል  በመለኮት ምሪት ውጪ የተፃፈ ማለት ሳይሆን ሰዋዊ ባህሪ እንዳለው ለመጠቆም ነው ። መፀሃፍ ቅዱሳችን ልዩ የሚያደርገው በእግዚአብሔር ምሪት ፣ በሰው ቋንቋ በሰው ለሰው በአምላክ መሪነት የፃፈ ነው ። መለኮታዊም ሰብአዊም መሆኑ የመፀሃፍ ቅዱሳችን ውበት ነው ። መፀሃፍ ቅዱስን ለመረዳት መለኮታዊ በመሆኑ የመለኮት የአምላካዊ ብርሃን ሰብአዊ በመሆኑ ደግሞ ሰዋዊ ቋንቋ ፣ ባህል ፣ታሪክ ማግኘት በቀላሉ ከመፀሃፍ ቅዱስ ጋር ጤነኛ ግንኙነትና ህብረት እንዲኖረን ያደርጋል ። @cgfsd
7
👍 3
🔥 1
Смотреть все посты