Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
1.1K
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 552
Сегодня
0
Просмотров на пост
Всего
463
ER
Общий
24.64%
Суточный
13.5%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 1 130 постов
Смотреть все посты
Пост от 08.07.2026 12:53
8
0
0
መንፈስ ቅዱስ በተመለከተ bible thinkers ላይ ጥናት ተጀመሯል ጠቃሚ ስለሆነ join አርጋችሁ እንድትማሩ recommended አረጋለሁ ።

በዚህ አጋጣሚ https://t.me/bibilicalthinker
channal ብትገቡ ብዙ ታተርፋላችሁ እምነታችን በአግባቡ የሚሞግት channal ስለሆነ ።
Пост от 08.07.2026 12:50
11
0
0
ዛሬ ምሽት(2:30) የጀመርነውን Pneumatology Class የመጨረሻ ክፍል እንማማራለን።
ባለፈው የአብንና የወልድን Eternal relations of origins አይተናል።
ዛሬ የመንፈስ ቅዱስን relation of origin to the Father and the Son እናያለን።
* መንፈስ ቅዱስ የሚሠርጸው(የሚወጣው) በምዕራቧ ቤተክርስቲያን(በካቶሊኮች እና በብዙ ፕሮቴስታንቶች) እንደሚታመነው Hypostetically ከአብ እና ከወልድ ነው ወይስ በምስራቋ ቤተክርስቲያን እና በሌሎች ኦርቶዶክሳዊያን እንደሚታመነው ከአብ ብቻ?
(እና ከወልድ Hypostetically ሳይሆን Economically)
* መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? Should we affirm the Filioque("..And the Son")?
*ሁለቱም የላቲን እና የግሪክ አባቶች(Augustine, Cyril, Basil the great, Gregory Of Nyssa, Athanasius ) ምን አስተማሩ?
Hypostetical(Personal)processionን ወይስ Just Economic procession?
ይኼ ከነበሩት ቤተክርስቲያንን በ 1054 ዓ.ም ለሁለት ከከፈሉት ጉዳዮች አንዱ ነበር። ሁለቱም አብያተክርስቲያናት ተወጋግዘዋል(ካቶሊኮች በ Lyon ጉባኤ Filioqueን ዶግማ አድርገዋል። የምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ደግሞ በበኩሏ ይሄንን ትምህርት Soul damning የሆነ አደገኛ ምንፍቅና ነው ብለው ያምናሉ። ውግዘቱ እኛንም የሚመለከት ነው ምክንያቱም ሁሉም የፕሮቴስታንት ሪፎርመሮች የ Filioqueን Clause affirm ስላደረጉ።)

በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የራሳችሁን Research ሰርታችሁ ኑ። እንወያይበታለን። ኦርቶዶክሳዊያን ቢኖሩ ደግሞ የእነርሱንም Perspective ከራሳቸው ለመስማት More በጣም አሪፍ ይሆናል።
Пост от 06.07.2026 12:57
113
0
4
@cgfsd
Видео/гифка
👏 2
Пост от 05.07.2026 05:34
5
0
0
ክርስቶስን ጌታ አድርጋችሁ በልባችሁ ቀድሱት። እናንተ ስላላችሁ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ፤ ነገር ግን ይህን ሁሉ በትሕትናና በአክብሮት አድርጉት፤
1 ጴጥሮስ 3:15
Пост от 04.07.2026 06:12
5
0
0
አስር ልጆቿንና ባሏን በጦርነት ያጣች የትግራይ እናት በአንድ ቪዲዮ ተመለከትኩ ፤ ሀዘኗን መቋቋም አቅቷት መናገር ስትቸገር። ምን ያህል ጦርነት አስከፊ እንደሆነ ፀያፍ ተግባር እንደሆነ ግልፅ ነው ። አሁንም የጦርነት ቅስቀሳ አለ እያሉ እናቶች ሲያለቅሱ ልጆቻቸውን ስደት ሲልኩ ማየት እጅግ ያማል። ትግራይ የመሄድ እድል ባይገጥመኝም እዛም ዘመድ ባይኖረኝም እንኳን ከጓደኞቻችን ፣ ከማህበራዊ ሚዲያ፣ በእየ ከተማው ተሰደው የሚመጡን ወጣቶችና አዛውንቶች ሳይ ምን ያህል ጉዳዩ አስከፊ እንደሆነ መረዳት እችላለሁ።

ግን ለምን ? ከትናንት ስሕተቶች የማንማረው ይህን ህዝብ ልናፅናናው ከጎን ልንቆም ይገባል ። መፅናናት ያስፈልጋቸዋል! ስለ ሰው ለማዘን ለመጨነቅ የግድ ከእኛ ዘር ሀረግ መሆን የለበትም ለክርስቲያን ባልንጀራው ያገኘው የሰው ልጅ በጠቅላላ እንጂ የዘር ሀረጉ ብቻ አይደለም ።ጦርነት እንዲቆም ፣ እናቶችና አባቶች እንዲፅናኑ ፣ ልጆች በሰላም እንዲኖሩ የመፀለይ ግዴታ አለብን ። እግዚአብሔር ሆይ በቃ በለን 😭 ህዝብን አስብ ። እንፀልይ !😭😭
Пост от 02.07.2026 21:35
3
0
0
ልጅነቴ ያላለቀ ነኝና ብላቴና
 ሙሉ ሰው አድርገኝ ጌታ
  ቃልህን : አብላኝና.......

🎶 ተስፋዬ ጋቢሶ(ጋሼ)
Пост от 02.07.2026 13:29
1
0
0
(አጭሩና ረጅሙ መዝጊያ)



በአዲስ ኪዳን መጽሐፍት መካከል ከፍተኛ ውዝግብ ከሚያስነሱ ክፍሎች መካከል የማርቆር ወንጌል መዝጊያ አንዱ ነው ። ክርክሩ የማርቆስ ወንጌል የሚያበቃው ምዕራፍ 16 ቁጥር 8 ላይ ነው ወይስ ምዕራፍ 16 ቁጥር 20 ላይ ነው ማለቂያው የሚል የቆየ የሙግት ሀሳብ አለ ። 16:8 የሚሉት አጭሩ መዝጊያ በመባል ሲጠሩ 16:20 ደግሞ ረጅሙ መዝጊያ በመባል ይታወቃሉ ።

አጭሩ መዝጊያ የሚያምኑ መነሻ የሆናቸው የተወሰኑ የድሮ የመፀሃፍ ቅዱስ ማንስክሪፕት ቅጂዎች ላይ እስከ ቁጥር ስምንት ድረስ ብቻ መገኘቱ ነው ። በተለይ ከ3ተኛና 4ተኛ ክፍለ ዘመን በኋላ በርካታ ቅጂዎች ይገኛሉ ፤ከእነዚህም ውስጥ ከአንድ ሺ ከሚበልጡ ቅጂ ውስጥ ሶስት ቅጂ ላይ የማርቆስ 16:8 ድረስ ብቻ ሲሆን ከቁጥር 9-20 አይገኝም ። እነዚህም ቅጂዎች :- ቫቲካነስ ኮዴክስና ሲናይቲከስ ኮዴክስ ይገኙበታል ። በእነዚህ ቅጂዎች ላይ የማርቆስ 16:8 በኋላ ያሉ ቁጥሮች የለም ። በአንድኛው ባዶ ቦታ በሌላኛው ተራርቆ በተፃፉ ፊደላት ምክኒያት ባዶ ቦታውን  ወደ ሉቃስ ወንጌል የሚያስገባ መሸጋገሪያ በመሆን ተቀምጧል። በእነዚህ ክስተት ምክኒያት የማርቆስ ወንጌል 16:9-20 ያለው ሀሳብ የተጨመረ በቀድሞ ኦሪጂናል ጥቅቅል መፀሃፍ ውስጥ የለም የሚል መላምት መበራከት ቀጥሏል ። ከዛም ከቁጥር 9-20 ያለው ስነፅሁፋዊ ይዘቱም ከሌሎቹ ማርቆስ ወንጌል መፀሃፍ ጋር የተለየ ነው የሚል ውስጣዊ ሙግትም ይሰነዝራሉ ። ብለው አንዳንድ አስተምሮዎች ከ9-20 ያለው ከሙሉ የመፀሃፍ ቅዱስ ትምህርት እንደሚጋጭ ያምናሉ በተለይም መርዝ ብትጠጡ አይገላችሁም ፣ እባብ ብትጨብጡ የሚለው ጥቅስ በመምዘዝ ከክርስትና ትምህርት ይጋጫል የሚል እይታ አላቸው ፤ ነገር ግን ይህ እይታ ውሃ የማያነሳ ነው የሁልጊዜ አስገዳጅ ሁኖ አልቀረብም ፣ ከዛም ከተልዕኮ አንፃር የተጠቀሰም በመሆኑ ተአምራዊ መልክ ሊኖር እንደሚችል ማሰብ ያስፈልጋል ። ከዛም በመቀጠል በታሪካዊ ማስረጃ በመጥቀስ የቤተክርስቲያን ታሪክ አባት ተደርጎ በሚቆጠረው አውሳብዮስ የለም እንዳሉ በመጥቀስ ይነሳል አውሳብዮስ የማርቆስ 16:9-20 ያነሱት የተጨመረ ነው  ከማለት አንፃር ሳይሆን ከሌሎች የወንጌላት መፀሃፍ ጋር ትንሳኤውን እንደማይጋጭ ግልፅ ከማድረግ አንፃር ነው ።

አጭሩ መዝጊያ 16:8 ልክ ያልሆነበት ሌላኛው አግባብ ማርቆስ ቁጥር 8 የጨረሰው ሆን ብሎ(intentionally ) የሚል ሀሳብ ያነሳሉ ( book from perspective on ending mark  )።  ይህ ሀሳብ አሳማኝ ሊሆን የሚችለው ከአንድ ነገር ጎን ብቻ ሊሆን ይችላል የማርቆስ ወንጌል አፃፃፍ ጥድፊያ የተሞላ እንደመሆኑ መጠን በቶሎ የማርቆስ ወንጌል ፀሃፍ ዘግተት ሊሆን ይችላል ። ምን አልባት እንደ አንድ ሙግት ነው ግን በቂ አይደለም ። ምክኒያቱም የማርቆስ ወንጌል ከጴጥሮስ ስብከት ተመሳሳይነት አለው በተለይም የሐዋሪያት ስራ ላይ  ጴጥሮስ ለቆርነሌዎስ የሰበው ስብከት ውስጥ ማርቆስ ወንጌል ጋር የይዘት መመሳሰል ሊኖረው ይችላል ። እንደተባለው ማርቆስ ወንጌሉን ከጴጥሮስ ሰምቶ ወይም በጴጥሮስ ንድፍ ከፃፈ ፤ ጴጥሮስ ደግሞ በስብከቱ ውስጥ የክርስቶስ ትንሳኤ በተደጋጋሚ ያነሳል አልፎ ተርፎ አይን እማኝ እንደሆነ ግልፅ ነው ። ስለዚህ ከትንሳኤ በኋላ ያለው ክስተት ትዕዛዝ  ሊነሳ ያስፈልጋል ። ከማርቆስ ወንጌል አመጣጥ አንፃር በጥድፊያ የተሞላና ስለማገልገል ሲነሳ ስለተመለከት በቀደሙት ምዕራፍ በመጨረሻው ላይ ተልዕኮን የሚያክል አደራ ያለበት የአገልግሎት ትዕዛዝ የማያሳይ ከሆነ አሁንም ከፅሁፍ ውስጣዊ ባህሪ አንፃር ይጋጫል ። በቁጥር ስምንት የሚያልቅ ከሆነ ትንሳኤውን እንደ መልካም ዜና ማየት ይከብዳል ምክኒያቱ በብዥታ ስለሚያልቅ ።

አሳማኝ የሆነው የማርቆስ መዝጊያ ረጅሙ ነው ። በቁጥር 20 የሚያልቀው ነው ። ከውስጣዊውም ፣ ከውጫዊም ፣ ከታሪካዊ ማስረጃ ብንመለከት አሳማኙ ረጅሙ መዝጊያ ነው ። በእርግጥ በሶስቱ ቅፆች ከቁጥር 8 በኋላ አለመገኘቱ ጥርጣሬ ቢያስነሳም በሌሎች በሺ የሚቆጠሩ መጣጥፎች ላይ መገኘቱ በርካታ መረጃ እንዳለ ያሳያል( እውነት ለሁሉ ገፅ የማርቆስ ወንጌል 16:9-20 ትክክለኝነት) ። በቤተክርስቲያን አባቶች ከሶስቱ ቅጂዎች በፊት ከቁጥር 9 እስከ 20 ያለው ጠቅሰው በማስተማራቸውና በመፃፋቸው ምን ያህል ማርቆስ 16:9-20 የመፀሃፍ ቅዱሳችን አካል እንደሆነ ማረጋገጫ ይሆናል ።

@cgfsd
Смотреть все посты