Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Telegraph-статьи Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы
Защита от накрутки Создать своего бота Продать/Купить канал Монетизация

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
736
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 351
Сегодня
+3
Просмотров на пост
Всего
371
ER
Общий
24.04%
Суточный
13.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 736 постов
Смотреть все посты
Пост от 06.01.2026 00:09
55
0
1
(ሥላሴያዊ አምልኮ) የክርስትና ትምህርት ሁሉ ምንጭ ሥላሴ ነው ። የትምህርቶችና የአስተምሮዎች ሁሉ ቁንጮ ሥላሴ ካልሆነ ምን ሊሆን ይችላል? በሥላሴ አማኞች  ላይ ከሚነሱ ጥያቄዎች መካከል ቃል በቃል ሥላሴ የሚለው ቃል በመፀሃፍ ቅዱሳችን አለ ወይ ? የሚል ነው ። ለዚህ ሀሳብ ብዙ ርቀት ሳንሄድ የምንሰጠው መልስ ግልፅ ነው ቃል በቃል ባይኖርም  አስተምሮው በመፀሃፍ ቅዱሳችን ስላለ እናምናለን ። ሥላሴ ሶስትነት የሚል ትርጓሜው አለው ። ስላሴ ስንል በሶስት አካል የሚኖር አንድ አምላክ ነው ። የማይደባለቅ ሶስትነት የማይነጠል አንድነትን ያሳያል ። በስም ፣ በግብር ፣ በአካል ሶስት ደግሞ በመለኮነት  በባህሪ አንድ አምላክ ። ያለን አንድ አምላክ እንጂ ሶስት አይደለም ። ነገር ግን ሶስት አካላት አሉ ግን አንድ ባህሪ ያለው አንድ አምላክ ። ሥላሴን ስናስብ የማንደባልቀው ሶስትነትና የማንከፋፍለውን አንድነት ለይተን ማወቅ አለብን ። ወደ ክርስቲያናዊ ኑሮአችንና አምልኮአችን ስንመጣ የማይነጣጠለው አንድነት የማይደባለቀውን ሶስትነት መሰረትና ማዕከል ማድረግ አለብን ። ገና ሰው ከፈጠረበት የፍጥረት ጅማሪ አንስቶ የተፈጠረው በሥላሴ ምክር ነው፤ ኑ በመልካችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር በሚል መነሳት ነው ። ፍጥረቱን በሥላሴ ነው የሆነው ። የሰው ፍጥረት ሥላሴያዊ ነው ። ሰው በሀጢያት ከወደቀ በኋላ ሰውን ለማዳን የተሰራው የማዳን ስራም ሥላሴያዊ ነው ። አብ ልጁን በመስጠት ፣ ልጁ ራሱን በመስጠት ፣ መንፈስ ቅዱስ የተሰራውን ስራ በመፈፀም የተደረገው የመዳን ምክኒያቱም አድራጎቱም ሥላሴያዊ ነው ። ፍጥረታችን ሥላሴያዊ እንደሆነ ሁሉ መዳንችንም ሥላሴያዊ ነው ፤ ስለዚህ ከዳንን በኋላ ያለን አምልኮም ሆነ ከአምላክ ጋር ያለን ህብረት ሥላሴያዊ መሆን አለበት ። አንዳንድ መንፈሳዊ ህብረቶቻችን ውስጥ የሚስተዋለው የአምልኮ ወይም መንፈሳዊ ተግባራችን አንደኛውን የሥላሴ አካል ላይ ብቻ የሆነ ሌላውን የረሳ ይመስላል ። ክርስቶስን ማዕከል ማድረግ ማለት የአብን አባትነትና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለን ህብረት እርግፍ ማድረግ አይደለም ። እንደውም ክርስቶስን ማዕከል ማድረግ ልከኛ የሚሆነው ለአብ ክብር በመንፈስ ቅዱስ ሃይል የሆነ ሲሆን ነው ። አብንና መንፈስ ቅዱስን ያገለለ ክርስቶስን ማዕከል ማድረግ ክርስቶስ ማዕከል ማድረግ አይደለም ።  በሌላው ጎን መንፈስ ቅዱስ መጠማት ከእርሱ ጋር የሚኖርን ህብረት መለማመድ አብንና ወልድ በመፀሀፍ ቅዱስ እንደሚለው ትኩረት ያደረገ ካልሆነ መስመር ሊለቅ ይችላል ። መንፈስ ቅዱስ ጋር የሚኖር ህብረት ክርስቶስን ማዕከል ያደረገና ለአብ ክብር የሆነ የሚሆን ከሆነ ትክክለኛ ህብረት ይሆናል ።  መንፈሳዊ ልምምዶቻችን መፀሃፍ ቅዱስ እንደሚለን ሥላሴያዊ መሆን አለበት ። ሶስትም አንድም ነው እግዚአብሔር ! በመሆኑም ሶስትነቱ በመፍጠር ፣ ሰውን በማዳን ካልተጋጨ እኛ በአምልኮ ስርአታችንና በመንፈሳዊ ልምምዳችን አንደ መፀሃፍ ቅዱሳዊ አማኝ ሊጋጭብን አይችልም ። እውነተኛ መንፈሳዊ ህብረትና ልምምድ ሥላሴያዊ ነው ። @cgfsd
4
🔥 2
👍 1
Пост от 04.01.2026 10:48
211
0
3
ዘወትር በፀሎት በፊትህ ልደፋ በውስጤ ያኖርከው እሳቱ እንዳይጠፋ ገና ላገልግልህ  በኋይል ተሞልቼ ጉብዝናዬን ሁሉ  ለአንተ ሰጥቼ 🎶 what a song 😭
🔥 14
8
😢 2
Пост от 04.01.2026 08:56
239
0
6
ጌታ ይባርካችሁ !! ከውስጤ ተረበሸ ታሪክ ላይ የተዘመረው መዝሙር ። @cgfsd
Видео/гифка
🔥 9
4
Пост от 04.01.2026 00:39
304
0
7
(ውስጤ ተረበሸ) አይ ወንጌል !! ቁር ያዝ ያደረገው ብርዳማ ቀን ነበር ። በገደብ ከተማ የመፀሃፍ ቅዱስ ትምህርት ይሰጣል። ለፕሮግራሙ አረፋፍጄ ነበር የደረስኩት ። ሰአት ስለሄደ በቀጥታ ወለም ዘለም ሳልል ወደ ትምህርቱ የገባነው ። የተለያዩ አይነት ሰዎች በመንፈሳዊ ርሃብ ሳቢያ ተሰብስበዋል ። አንድ አባት ትምህርት ከሚከታተሉት መካከል በልዩነት ትኩረት ይስባሉ ። ማስተማር ከተጀመረበት ሰአት ጀምሮ በእንባ ነው የሚከታተሉት ። የሚከታተሉበት ንቃት ቢያስገርምም እንባቸው ስለተደጋገመብኝ ሰረቅ ሰረቅ እያደረኩ አያቸዋለሁ ። ሳልዋሽ በውስጤ ለጌታ ነው እያልኩ ቅዱስ ቅናት እየቀናሁም ነበር ። ፕሮግራማችን ስንጨርስ ወደኋላ ቀርተው ጠበቁኝና በስም ተዋወቅን ። እንባቸው አሁን አልደረቀም ፊታቸው ላይ ይተራመሳል ። ጌታ ይባርክህ ልልህ የቀረሁት ፤ ግን ጌታ ይባርክህ ልል ሳስብ ከዛሬ 16 አመት በፊት ለወንጌል ስራ ወደ ሌላ አካባቢ ባለቤቴን እንሂድ ስላት እንቢ ብላ ተቃወመችኝ ። ስንከራተት ኖርን አሁን ከእዚህ አልንቀሳቀስም አለችኝ ። ያኔ የዘመርኩት መዝሙር ትዝ አለኝ ልዘምርልህ ብለው አዝማቹን እንዲህ ተቀኙልኝ    "ወንጌል ይዛችሁ የምትሄዱ      አስቸጋሪ ቢሆንም መንገዱ      የኋላ የኋላ አክሊል  አለ      ለእግዚአብሔር የሚሳነው የታለ      ጌታ ይባርካችሁ (2)       ፀጋውን ያብዛላችሁ " እንባቸው እየጠራረጉ ጌታ ይባርክህ ብለው ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ተነሱ ፕሮግራም ስንጨርስ መሽቷል ። አንድ ሰአት መንገድ አለብኝ ብለው ተሰናበቱኝ ። ነገ ፕሮግራማችን ላይ ይዘምሩን ስላቸው ደስ እያላቸው ክራር ይዘው እንደሚመጡ ነግረውኝ እንባቸውን ጠራርገው ሄዱ ። በነገታው በጠዋት የአንድ ሰአት ሩቅ ከነበረው ቤታቸው ቀድመውን መጥተዋል ። ከጎናቸው ክራራቸውን እንደ ከዘራ ደገፍ አረገው ይዘው ጠበቁን ። ዛሬም በእንባ ነው ትምህርቱ ሲጀመር ጀምሮ የሚከታተሉት በልባቸው እየተደነኩ በራሴ እያፈርኩ ትምህርቱን ቀጠልን ። በተነጋገርነው መሰረት ክራራቸውን አስተካከለው ከልጃቸው ጋር ሁለት መዝሙር በእንባ ዘመሩልን ። በርካታ አመታት ወንጌል ሰርቻለሁ አሁን ግን የበለጠ ውስጤ ተረበሸ አሉን ። በእንባ ዘመሩ ጉባኤውም በእንባ አብሮ ወንጌልን በመውደድ ርሃብ አብሯቸው ቀለጠ ። ጌታን እንደዚህ የሚወዱ ለእግዚአብሔር አጀንዳ ሽንፍ ያሉ ውስጤ ተረበሸ የሚሉ ሰዎች አሉ ። ጌታ እንዲህም ይናፈቃል ። @cgfsd
13
🔥 7
😢 5
🥰 1
Пост от 02.01.2026 13:10
289
0
0
(መለኮታዊ ሰብአዊ) የመፀሃፍ ቅዱስን ባህሪ በተመለከተ ማወቅ ካሉብን ነገሮች መካከል መለኮታዊም ሰብአዊ መሆኑን ነው ። ይሔ የመፀሃፍ ቅዱስ ባህሪ በቀላሉ መፀሃፍ ቅዱሳችን ለመረዳት ትክክለኛና ህብረት እንዲኖረን ይረዳናል ። በተቃራኒው ደግሞ ይሔን ባህሪው መረዳትና መገንዘብ ከተሳነን ለመፀሃፍ ቅዱስ ሀሳብ ሩቅ እንደሆናለን ። መፀሀፍ ቅዱስ መለኮታዊ ነው ሲባል በእግዚአብሔር ምሪት የተፃፈ ፣ እስትንፈሳ እግዚአብሔር ያለበት ቅዱስ ቃል ነው ። በእግዚአብሔር መንፈስ ምሪት የተከናወነ በእግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ የመለኮት ስራና እስትንፈስ ያለበት እንደሆነ መገንዘብ እንችላለን ።  መፀሃፍ ቅዱሳችን ሰብአዊ ነው ስንል ደግሞ ሰዋዊ ባህሪም እንዳለው መረዳት እንችላለን ። የእግዚአብሔር ሀሳብ ቢሆንም በሰው እጅ ፣ ቋንቋ ፣ ባህል ፣ አኗኗር ፣ ልማድ ፣ ወግና ታሪክ የተፃፈ ነው ። እነዚህ ነገሮች መፀሃፍ ቅዱስ ሰብአዊም ባህሪ እንዳለው ያረጋግጡልናል ። መፀሀፍ ቅዱስ ሰብአዊ ባህሪ አለው ስንል  በመለኮት ምሪት ውጪ የተፃፈ ማለት ሳይሆን ሰዋዊ ባህሪ እንዳለው ለመጠቆም ነው ። መፀሃፍ ቅዱሳችን ልዩ የሚያደርገው በእግዚአብሔር ምሪት ፣ በሰው ቋንቋ በሰው ለሰው በአምላክ መሪነት የፃፈ ነው ። መለኮታዊም ሰብአዊም መሆኑ የመፀሃፍ ቅዱሳችን ውበት ነው ። መፀሃፍ ቅዱስን ለመረዳት መለኮታዊ በመሆኑ የመለኮት የአምላካዊ ብርሃን ሰብአዊ በመሆኑ ደግሞ ሰዋዊ ቋንቋ ፣ ባህል ፣ታሪክ ማግኘት በቀላሉ ከመፀሃፍ ቅዱስ ጋር ጤነኛ ግንኙነትና ህብረት እንዲኖረን ያደርጋል ። @cgfsd
6
👍 3
🔥 1
Пост от 31.12.2025 16:53
332
0
0
(እነሆ- እነሆኝ) እነሆ ማለት ይሔው ተመልከቱ ይሔው እንኩ እንዳማለት ነው ። በመፀሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ እግዚአብሔር አብ እነሆ ብሎ አንድኛ ልጁን ሲሰጥ እንመለከታለን ። ልጁም ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ እነሆኝ ብሎ ራሱን ሲሰጥ ይታያል ። ለዚህም ሁለት ጥቅሶች በዩሀንስ ወንጌል መፀሃፍ ውስጥ እንቃኝ ። በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስከ መስጠት ድረስ ዓለምን እንዲሁ ወዶአልና፤ ዮሐንስ 3:16 እግዚአብሔር አብ አንድኛ ልጁን እንዲሁ ሰጠ ። እነሆኝ በማለት ለአለሙ እግዚአብሔር ወዶ ፈቅዶ ሰጠ ። ይሔም ሰጪነቱን ለጋስነቱ በማዳን እቅድ ውስጥ ያረገውን ቸርነት ያሳያል ። እነሆ ልጄን ብሎ ሰጠ ። የሰጪነት ጥግ !! ስለ ወዳጆቹ ሕይወቱን አሳልፎ ከመስጠት የሚበልጥ ፍቅር ማንም የለውም፤ ዮሐንስ 15:13 በዚህ ክፍል እያወራ ያለው እግዚአብሔር ወልድ ሲሆን ስለወዳጆቹ የተባሉት ደግሞ የሰው ልጆችን ነው ። እግዚአብሔር ወልድ በአብ ፈቃድ የተሰጠ እነሆ የተባለ ቢሆን እሱም በፈቃዱ ራሱን ሰጥቷል ። እነሆ እንደባለ ሁሉ እነሆኝ ብሏል ። በአብ እንደተሰጠ ሁሉ በራሱም ሙሉ ፈቃድ ራሱን ሰጥቷል ። በእግዚአብሔር መካከል የሚጋጭ ፈቃድ የለም አንድ ፈቃድ ነውና ። እነሆ ተብሏል ራሱም እነሆኝ ብሏል ፣ ተልኬያለሁ እንዳለሁ ሁሉ መጥቼላችኋለሁ ብሏል  ። በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ምክር ወልድ ተሰጥቷል ይሔ የሚያሳየው ድነታችን ስላሴያዊ መሆኑን ነው ። ትልቁም የድነታችን ውበት በስላሴ መከወኑ ነው ። @cgfsd
9
🔥 6
Пост от 30.12.2025 22:59
392
1
1
(የእግዚአብሔር ሰው) እግዚአብሔር ሰውን በመልኩና በአምሳሉ በመፍጠር ሰውን አከበረው ። ሰው በሀጢያት ውድቀት ምክኒያት ውስጥ ቢሆንም እግዚአብሔር በድጋሚ በሁለተኛው አዳም ክርስቶስ በኩል ሰው የሚለውን ትርጉም ከፍ አደረገው ። በመጀመሪያው አዳም እግዚአብሔር ሰውን በመልኩ በመፍጠር አከበረ ። በሁለተኛው አዳም ክርስቶስ በኩል የሰውነት ምንነት በይበልጥ አከበረ ። ሰው መሆን በሰው ከበረ ማለትም በሁለተኛው አዳም ክርስቶስ እግዚአብሔር ሰውን  የፈለገበትን ምክኒያት ግልፅ በማድረግ ሰውን አከበረ። በክርስቶስ ሰው መሆን እግዚአብሔር የፈለገው የእግዚአብሔር ሰው ተገለጠ ። የእግዚአብሔር ሰውን ማወቅ የሚፈልግ በሙሉ ሁለተኛው አዳም ክርስቶስን ይመልከት ። @cgfsd
10
🔥 5
🥰 1
Смотреть все посты