Каталог каналов Каналы в закладках Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds beta Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
709
340
3
0
8.1K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 414
Сегодня
+1
Просмотров на пост
Всего
416
ER
Общий
23.92%
Суточный
13.1%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 709 постов
Смотреть все посты
Пост от 22.01.2026 22:03
18
0
0
"አንድ ሰው ባመጸብህ ግዜ ባትወድደው እኳን ቢያንስ ይቅርታን በጠየቀ ግዜ ፍቅርን አሳየው" ✍️ቅዱስ አውግስጢኖስ @cgfsd
Пост от 22.01.2026 15:59
116
0
0
የእግዚአብሔር መንግስት ትርጓሜ ያለው ንጉስ ጋር ወይም ገዢው ጋር ነው ። kingdom የሚለው ቃል የሚገልፀው ንጉሱ ላይ ጥገኛ የሆነን የአገዛዝ ስርአት ነው ። ስለ እግዚአብሔር መንግስት ስናሳብ የንጉሱ ገዢነት ላይ ማተኮር ያለብን ። ሐዋሪያው ጳውሎስ በመልዕክቶቹ ውስጥ በጣም ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔር መንግስት የሚል ቃል አልተጠቀመም ። ይሔን ቃል ስላልተጠቀመ ስለእግዚአብሔር መንግስት አልፃፈም ማለት ግን አይደለም ። በይበልጥ እንደውም በመልዕክቶቹ ውስጥ ስለ እግዚአብሔር መንግስት ፅፏል ። የጳውሎስ ትኩረት የነበረው ገዥነቱ ላይ ስለነበር ። በተለይ ክርስቶስ ብዙ ቦታ "ጌታ" እያለ ፅፏል ። ጌታ ማለት ገዢነት የሚያሳይ ቃል ነው ። አብዝቶ ጌታ በማለት የእግዚአብሔን መንግስት አስተማረ ። ጳውሎስ የእግዚአብሔር መንግስት ኢየሱስ ጌታ ነው በማለት የመንግስቱን ጉዳይ የገዢነት ስርአቱን በግልፅ ከእነ አላማው አሳይቷል ። የእግዚአብሔር መንግስት የእግዚአብሔርን የገዢነት አገዛዝ ይጠቁማል ። @cgfsd
5
🥰 2
Пост от 17.01.2026 17:21
376
1
6
ለቁስሌ የሚሆን ዘይት በእጅህ አለ ያልጨመረ በእኔ  ስንቱን ቤት ያከመ ዛሬም ከእኔ ደርሶ አይቀንስ ጉልበቱ ፈሶ ያድነኛል ያደርገኛል ብርቱ 🎶
🔥 18
15
😢 5
🥰 3
Пост от 14.01.2026 16:47
412
0
1
(የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ 1)               - ዩሀንሰ ምዕራፍ 1 እና የመዋጀት ታሪክ                  (ክፍል 3) የዩሀንስ ወንጌል የመዋጀት ታሪክን (redemptive story) የሚያሳይ መፀሃፍ ነው ። የዩሀንስ ምዕራፍ አንድ አወቃቀር መፀሀፍ ቅዱስ የመዋጀት ታሪክ እንደሆነ ያሳየናል ። የመዋጀት ታሪክ ማለት ምን ማለት ነው ?  ይሔ ጥያቄ የመፀሀፍ ቅዱሳችን የጀርባ አጥንት የሆነ ጥያቄ ነው ። ምክኒያቱም የመዋጀት ታሪክ የመፀሃፍ ቅዱሳችን ግልፅ መልዕክቱ ነው ። የመዋጀት ታሪክ ማለት የእግዚአብሔር የማዳን ታሪክ ነው ፤ እግዚአብሔር ለፍጥረቱ ራሱን የገለጠበት የማዳንና ሰውን የራሱ የማድረግ ሂደት እርሱ የመዋጀት ታሪክ በመባል ይታወቃል ። የእግዚአብሔር የማዳን(የመዋጀት) ታሪክ አብዛኛውን ጊዜ በአዲስ ኪዳን መፀሃፍ ውስጥ የተገደበ ይመስለናል። ከአዲስ ኪዳንም ደግሞ በክርስቶስ የመስቀል ሞትና ትንሳኤ ላይ ያለ ብቻ እንደሆነ አንንዳንድ ቦታ ይታያል ። በእርግጥ መስቀሉና ትንሳኤው የመዋጀቱ ትልቁ መፈፀሚያ ስራዎች ናቸው ። ቢሆንም ግን የመዋጀት ታሪክ የመስቀሉና የትንሳኤው ገፅታ ብቻ አይደለም ። የሰው ልጅ ከወደቀበት ጊዜ አንስቶ እግዚአብሔር የመዋጀት ታሪክ ጉዞ ተስፋ በመስጠት ከኤደን ገነት ሲያጀምር እናያለን ። ያኔ ተስፋ ገባ በእስራኤል ውስጥ ስለ መዋጀቱ መንገድ ጠረጋ ነበር ። ብሉይ ኪዳን የሚነግረን ነገር ቢኖር እግዚአብሔር ከኤደን ገነት ጀምሮ በሰው ልጅ በፍጥረቱ መካከል የማዳን መንገድ ጀምሯል ። በኋላም በመስቀሉና ትንሳኤው ስራውን ወደ ፍፃሜ አምጥቷል ። ሁሉም የመፀሃፍ ቅዱሳችን ሀሳብ የመዋጀት ታሪክ ግባቸው ነው ። መፀሃፍ ቅዱስ የመዋጀት ታሪክ ነው ፣ የእግዚአብሔር ታሪክ የመዋጀት ታሪክ ነው ቢባል አሳማኝ ነው ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ የመዋጀት ታሪክ መስቀሉ ጋር ብቻ አያስቀረውም ። ምዕራፍ አንድ የሚያስገነዝበን የእግዚአብሔር የመዋጀት ታሪክ መስቀሉ ጋር ብቻ አልጀመረም ፤ ይሔን ስራ ቀድሞውን ጀምሯል በመስቀሉ የበለጠ ፈፀመው የሚል እይታ ያስገነዝበናል ። በዩሀንስ 1 የምናየው አምላክ የመዋጀት ታሪክ ስራን ለመፈፀም የሚተጋ አምላክ ነው ። ከፍጥረት በፊት ነበር (ዩሀ1:1)፣ ፍጥረትንም እሱ ፈጠረ(ዩሀ1:4)፣ በብሉይ ብርሃን ሆኖ እየመጣ ተገልጧል (ዩሀ1:9)፣ ሰው ሆኖ መጣ (ዩሀ1:14)፣ ለሞት የተዘጋጀ ሆነ (ዩሀ 1:29) ። ይሔ ሁሉ ትረካ የእግዚአብሔር መዋጀት ታሪክ በመስቀሉ ያልጀመረ በዚሁ ስራውን ተስፋ በመስጠት ፣ በማፅናት ፣ ሰው ሁኖ ማደስ በመጀመር ፣ በመስቀል ታልፎ ለመሰጠት በመዘጋጀት ስራው ይተርክልናል ። የእግዚአብሔር የማዳን ታሪክ ከጥንት የጀመረ እንደሆነ የዩሀንስ ወንጌል አንዱና ትልቁ ማሳያ ነው ። የመፀሃፍ ቅዱስ ሙሉ ዋና ትኩረት አቅጣጫ የመዋጀት ታሪክ በዩሀንስ አንድ ምዕራፍ ይንፀባረቃል ። @cgfsd
10
Пост от 11.01.2026 19:17
460
0
2
(የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ 1)                   -ዩሀንስ ወንጌልና ተመሳሳይ ወንጌላት           ክፍል -2 የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ በክርስትና ውስጥ ዋነኛ ትኩረት ማዕከል የሆኑትን ጉዳይ እያነሳ ይጀምራል ። በቀጥታ ወደ ጉዳዩ የሚገባ ምዕራፍ ነው ። ምንም እንኳን በወቅቱ  ደብዳቤው ሲፃፍ በምዕራፍና በቁጥር የተከፋፈ ባይሆንም በቤተክርስቲያን ታሪክ ለንባብ አመቺ እንዲሆን በምዕራፍና በቁጥር እንዲቀመጥ ተደርጓል  በዚህ በ21 ምዕራፍ ተዘጋጅቶ እጃችን ላይ አለ ። መጀመሪያ በተፃፈበት ወቅት የመጀመሪያዎች የዩሀንስ ወንጌል አንባቢዎች ምዕራፍ አንድ ምዕራፍ ሁለት እያሉ እየቆጠሩ ሳይሆን የደብዳቤው የመጀመሪያ ክፍል እያሉ በሀሳብ በታሪክ እየከፋፈሉት ሊረዱት ይችላሉ ። አሁን ባለበት በዚህ ዘመን የዩሀንስ ወንጌል ስናጠና ለንባብ ለመረዳትም ቀላሉ በምዕራፍና በቁጥር ከፋፍሎ ማንበቡ ለመረዳት አመቺ ያረግልናል ።  የዩሀንስ ወንጌል አራተኛው የወንጌል መፀሃፍት ነው ። ከዩሀንስ ወንጌል በፊት የምናገኛቸው የማቴዎስ ፣ የማርቆስ ፣ የሉቃስ ወንጌል መፀሃፍ synoptic gosple (ተመሳሳይ ወንጌላት) በመባል ይጠራሉ ። ሶስቱ ዘርፈ ብዙ የሆነ ተመሳሳይነት አላቸው ። የዩሀንስ ወንጌል ከሶስቱ የወንጌል መፀሃፍ የተለየ ነው ሲባል የወንጌሉ መልዕክት ይጋጫል ፣ ሌላ አስተምሮ ትምህርት ፣ ሌላ ወንጌል አለው ለማለት አይደለም ። ከተመሳሳይ ወንጌላት (synoptic gosple ) መፀሃፍት ከማቴዎስ ፣ ማርቆስና ሉቃስ የተለየ መልዕክት ዩሀንስ ወንጌል ካለው የሚጋጭ ወንጌላት አሉን ማለት ነው ። የዩሀንስ ወንጌል መለየት የመልዕክት ሳይሆን የአቀራረብ ፣ የታሪክ አዘጋገብ ፣ የትኩረት አቅጣጫ ፣ በሶስቱ ወንጌላት የበዛ ተአምራት ሲታይ በዩሀንስ ወንጌል የተወሰኑ ብቻ እናያለን ...እነዚህ የመሳሰሉን ነገሮች ሌሎች ነገሮች ጨምሮ ለማለት እንጂ በክርስቶስ ኢየሱስ ሞት ትንሳኤ የተሰራውን የወንጌል መልዕክት የተለያየ ለማለት አይደለም ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድም የተመሳሳይ ወንጌል መፀሃፍት (synoptic gosples book ) የሚለይ አጀማመር ሲጀምር እናያለን ። የዩሀንስ ወንጌል በተወሰነ አጀማመሩ ከተመሳሳይ ወንጌል መፀሃፍ መካከል ከማርቆስ ወንጌል ጋር ከሌሎቹ ማለት ከማቴዎስና ሉቃስ ይልቅ የተቀራረበ አጀማመር ያለው ይመስላል ። ከማርቆስ ወንጌልም ተመሳሳይ አጀማመር አለው ስንል ሙሉ ለሙሉ በማለት በማለት መድፈር አንችልም ። የሚያመሳስላቸው የማርቆስ ወንጌል ሲጀምር የሚጀምረው ከኢየሱስ አገልግሎት ነው ። በቀጥታ ወደ ኢየሱስ አገልግሎት ጅማሬ ማርቆስ ይገባል ።  ማርቆስ የኢየሱስ አገልግሎት ላይ ትኩረት አድርጓል ። በዩሀንስ ወንጌል በመጀመሪያው ምዕራፍ ለአገልግሎት የተዘጋጀን ደቀመዝሙር ያስከተለን ኢየሱስ እንመለከታለን ። በሁለተኛ ደረጃ በማርቆስም በዩሀንስ ምዕራፍ አንድ መጥምቁ ዩሀንስን ገና አጀማመራቸው ላይ ይታያል ይሔም ታሪክ ኢየሱስ ለማገልገል ራሱን ለመስጠት ዝግጅቱን መንገድ መጀመሩን ያሳያል ። በማርቆስና በዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ አጀማመር  መካከል ያለው  ልዩነት ማርቆስ በቀጥታ ወደ ኢየሱስ የአገልግሎቱ አጣዳፊነት የእግዚአብሔር መንግስት አንገብጋቢ እንደሆነ ሲያስገነዝብ ። የዩሀንስ ወንጌል የክርስቶስ ማንነት ትኩረት በማድረግ የሚያገለግለው ማነው? የሚለውን ከዛም ለምንድን ነው የሚያገለግለው ? የሚለውን መልስ መልሶ ይጀምራል ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ከሉቃስና ከማቴዎስ የሚለየው ዩሀንስ ከኢየሱስ ዘላለማዊነት ከሁሉ በፊት መሆኑን አስረግጦ ይጀምራል ። ሉቃስና ማቴዎስ ተወልዶ በበረት ስለማደሩ ይናገራሉ ። ዩሀንስ በበረት ስላለው ሳይሆን ሰው የሆነበትን ምክኒያቱንና በረከቱን ሲያስረዳ ሉቃስና ማቴዎስ ሰው ሁኖ የሆነውን ጎዳና ያካፍሉናል ።  እንደዚህ መለያየታቸው የአተራረክና ሊነግሩን የፈለጉት ትኩረት አቅጣጫ መለያየት እንጂ የወንጌሉ መልዕክት መለያየት አይደለም ። ሁሉም የፃፉልን ከተደራሲው አንፃር ሊያስተላልፉ የፈለጉት እንጂ የተያየ የወንጌል መልዕክት የለም ። ምሳሌ ማቴዎስ የክርስቶስ ንግስና ፣ ማርቆስ አገልጋይነት ፣ ሉቃስ የሰው ልጅ መሆኑን ፣ ዩሀንስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን አፅንኦት ሰጡት እንጂ አንዱ ከአንዱ አይጋጭም ። ስለዚህ የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ከተመሳሳይ ወንጌላት ለየት ያለው አፃፃፉ የክርስቶስ ሰው መሆን አላማና ሰው በመሆኑ ያለውን በረከት በልዩነት ይናገራል (ዩሀ 1:14- ዩሀ 1:18)። @cgfsd
13
👍 2
🔥 2
Пост от 10.01.2026 08:57
417
0
1
(ፀጋ እንደ ውሃ ) ተወዳጁ ፊሊፕ ያንሲን የወንጌላዊያን ፀሃፊና አስተማሪ ነው። በሁሉም አለም ማለት በሚቻል መልኩ መፀሃፉ ተደራሽ ነበር ።   ወንጌላዊው ቢሊግርሃም ከፀሃፊዎች መካከል ፊሊፕ ያንሲን የምወደው ፀሃፊ ነው በማለት በመፀሃፉ ላይ አስተያየት ሰጥቷል ። ቅይማት ፣ ያላወኩት ኢየሱስ ፣ ፀሎት በእውን ለውጥን ያደርጋል? የተሰኙ መፀሃፎቹ ወደ አማረኛ ተተርጉመዋል ። በእነዚህ መፀሃፎች ተግባራዊ ህይወት የተሞገትንበትና ለመንፈሳዊ ህይወታችን የታነፀበት እንደሆነ የሁላችንም ሀቅ ነው ። ለመጀመሪያ ጊዜ ያነበብኩት" ያላወኩት ኢየሱስ" የተሰኘውን ነበር ። ኢየሱስን የቅርብ እንደሆነ በማንነቱ የተደነቁበትና የተገረምኩበት ስራ ነው ። በተለይ ልቤ ውስጥ የቀረ አንድ አባባል ነበረው " ኢየሱስ ተገናኝቶ እንደቀድሞ ሁኖ መኖር አይችልም " የሚለው ቃል በጣም ወድጄዋለው ። የኢየሱስ ማንነትና ስራ ብርቱ ለዋጭ መሆን ያስገነዝበናል ። ፍሊፕ እጅግ በጣም ተወዳጅ ብዙ ሰዎች የጠቀመ መንፈሳዊ ሰው ነው ። ከሰሞኑን የ75 አመቱ ፍሊፕ ያንሲን ስለ አንድ የህይወት ክፍሉ በግልፅ ተናገረ ። ቀድሞውንም ቢሆን ግልፀኝነት መታወቂያው ነው ። በአጭር ግለ ታሪክ ህይወቱ በፃፈበት ፅሁፍ ላይ ለራሱ ሳይሳሳ ፍርጥር አድርጎ ተናግሮ ነበር ። ሰሞኑን በተናገረው ላይ የበለጠ ራሱ ላይ ያለውን ክፍተት አጋራ ። ከ55 አመት አካባቢ የሚጠጋ የትዳር ቆይታ ውስጥ አለ ግን በዚህም ውስጥ ሁኖ  ያለፉትን ስምንት አመታት ከሌላ ሴት ከትዳር ውጭ ይሄድ እንደነበረ ተናገረ ። ራሱን ለማየት ከብዙ ነገር አግልሎ ለመመለስ እንደሚፈልግ ተናገረ ። ባለቤቱም ይቅርታ እንደምታደርግ ይሔ የክርስቶስ ያሳየው የፍቅር ባህሪ ነው አለች ። ፍሊፕ ወደ ፊት በመውጣት በህይወት እያለ ለእግዚአብሔርና ለህዝብ ያለውን ክብር አሳይቷል። ዘሪቱም ከበደ በድፍረት የፀጋውን ጥንካሬ ያለፍራቻ ድካሟንና ውድቀቷን በመናገር ፀጋው እንዳገዛት ለራሷ ለክብሯ ሳትሳሳ በግለ ታሪኳ አሳይታን ነበር። ሀጢያት በጨለማ ውስጥ ሲደበቅ ይፋፋል ለሀጢያት ምቹ ቦታ ጨለማ ነው ድብቅ መሆኑ ፤ ብርሃን ደግሞ ያከስመዋል የእግዚአብሔር እውነት በዛ ስላለ ። አስቀድሞ ፊሊፕ ፀጋን በውሃ ምሳሌ አርጎ አውርቶናል ። " ፀጋው እንደ ውሃ ነው ዝቅ ወዳለው ስፍራ ይፈሳል " ። እውነት ከፍ ካለው አምላክ ዝቅ ወዳለው ወደ ትሁቱ ፣ ወደ ተሰበረው ፣ ለደከመው ፣ አቅም ወደሌለው ወደ ታች ቁልቁል ይፈሳል። ዝቅ ላለው ይበዛለታል ። ፊሊፕ ራሱን ዝቅ አድርጓል ። ለደከመው ወደ ፀጋው ዙፋን ተመላለሱ ያለው አምላክ ይረዳዋል ። ደጉ ጌታ ፀጋውን ለፍሊፕ ያብዛለት ። ፀጋው ግን እንደ ውሃ መፍሰሱን አያቆምም ከፀጋ በታች ካለን እናገኘዋለን ። ፀጋው ባይኖር ምን ይውጠን ነበር ? ስንት ጉድ ሸፈነልን ፣ ስንት ጉዳችን አስወገደልን ። የፀጋ ሁሉ አምላክ ይባረክ  ! ለፀጋው ክብር ምስጋና ይሁንለን ። @cgfsd
17
👍 2
🔥 2
😢 1
Пост от 09.01.2026 09:11
405
0
2
       (#ቃል ክርስቶስ) - የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ 1 ክፍል 1 የዩሀንስ ወንጌል አራተኛ የወንጌል መፀሃፍ ነው ። በርካቶች ዘንድ ተወዳጅ ተነባቢ በተደጋጋሚ የሚነሳ የቅዱሳት መፀሃፍ ክፍል ነው ። ዩሀንስ ወንጌል ከባድም ቀላልም ነው ። ጥቅል የሆኑ የክርስትና ትምህርቶች አሉበት ደግሞ ተግባራዊ ህይወት ይስተዋልበታል ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ሰፋ ያሉ ቁጥሮችንና ሀሳቦችን አካቶ ይዟል ። የምዕራፍ አንድ አተራረክ ከዘፍጥረት አንድና ከኢዮብ መፀሃፍ አንድ ጋር የሚያመሳስሉት ብዙ ሰዎች አሉ ። ከዘፍጥረት አንድ ጋር በንፅፅር ያስቀምጡታል ። የዘፍጥረት መፀሃፍ አጀማመሩ ከፍጥረት አጀማመር ያሳያል ። የዩሀንስ ወንጌል ደግሞ ከፍጥረት ጅማሬ በፊት ስለነበረው የሁሉ አስጀማሪው ስለሆነው ዘላለማዊ አምላክ ይናገራል ። በዚህ ንፅፅር መልክ የዩሀንስ ወንጌል ከዘፍጥረት እየተነፃፀረ ለመረዳት ይሞከራል ። የኢዮብ መፀሃፍ ደግሞ በምዕራፍ አንድ ላይ ኢዮብ ከመጣበት መከራ በፊት ስለመጣበት የመከራው ምክኒያት በትረካ መልክ መፀሃፉን ስናነብ እንመለከታለን ። በዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ቁጥር ሃያ ዘጠኝ ላይ ኢየሱስ ስለሚመጣበት የመከራ ምክኒያት ስለሚቀበለው መከራ " የአለምን ሀጢያት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ " ተብሎ ሲጠራ እናያለን ።  የሚመጣበትን  መከራ ምክኒያት የአለምን ሀጢያት ለማስወገድ እንደሆነ በክፍሉ ይገለፃል ። ከሚመጣበት መከራ በፊት ለምን መከራውን እንደሚቀበል አስረድቶን ያልፋል በዚህ ከእዮብ መፀሃፍ ጋር በንፅፅር ለመረዳት ሲሞከር ይስተዋላል ። የዘፍጥረትና የኢዮብ መፀሃፍ ሲተረጎሙ እንደ ዩሀንስ ወንጌል አንድ ነው ለማለት ሳይሆን ለንፅፅር በማቅረብና በተሻለ መልኩን ዩሀንስ ወንጌል ለመረዳት እንደ መነሻ ስለሚያገለግሉ ነው ። የዩሀንስ ወንጌል በዚሁ በምዕራፍ አንድ ስለ ዘላለማዊ ከምንም ነገር በፊት ስለነበረው  ስለ ቃል አምላክ (1:1) ፣ ስለፍጥረት መፈጠርና በቃል(ክርስቶስ) ስለመፈጠራቸው(1:4) ፣  ስጋ ስለበሰው ሰው ስለሆነው ቃል ክርስቶስ (1:14)፣ በብሉይ ኪዳን እየመጣ ሰውን ስለሚጎበኘው ቃል(1:9) ፣ የስላሴ ወኪል ስለሆነው አባቱን ስለሚያብራራው ቃል ክርስቶስ (1:18)፣ ለሞትና መከራን ለመቀበል ስለተዘጋው የእግዚአብሔር በግ ( 1:29-1:35) ፣ ደቀመዛሙር ስላስከተለው ረቢ መምህር (1:36) በስፋት ይነገራል ። በአጠቃላይ የክርስቶስ ዘላለማዊነት የሚያሳይ ፤ይሔም ዘላለማዊነት ክርስቶስ ከአባቱ ጋር ዘላለማዊ ያለህብረት ያለው መሆኑ ፣ ስለ ክርስቶስ ፈጣሪነት የሚያሳይ ፣ በፍጥረቱ መካከል ያለ መሆን የሚናገር ፣ ፍጥረቱ መሃል መሆኑ ብቻም ሳይሆን ሰው በመሆን የበለጠ የሰው ወገን የሆነ ፣ መከራን ለመቀበል የተዘጋጀ በግ መሆኑን ፣ ደቀመዛሙር በማስጠጋት መከተል የተባለ ህይወት እንዳለ እሱን በተግባር የመምሰል የመከተል ጉዞ እንዳለ ይታያል ። የዩሀንስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ ሰፊ የሆነ የክርስቶስ የማንነትና ስራ የሚተረክበት አስደናቂ ምዕራፍ ነው ። @cgfsd
🔥 10
7
👍 1
Смотреть все посты