Каталог каналов Мои подборки Мои каналы Поиск постов Рекламные посты
Инструменты
Каталог TGAds Мониторинг Детальная статистика Анализ аудитории Бот аналитики
Полезная информация
Инструкция Telemetr Документация к API Чат Telemetr
Полезные сервисы

Не попадитесь на накрученные каналы! Узнайте, не накручивает ли канал просмотры или подписчиков Проверить канал на накрутку
Прикрепить Телеграм-аккаунт Прикрепить Телеграм-аккаунт

Телеграм канал «በክርስቶስ ( in christ)»

በክርስቶስ ( in christ)
1.1K
334
3
0
7.3K
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Подписчики
Всего
1 515
Сегодня
+1
Просмотров на пост
Всего
406
ER
Общий
21.25%
Суточный
12.6%
Динамика публикаций
Telemetr - сервис глубокой аналитики
телеграм-каналов
Получите подробную информацию о каждом канале
Отберите самые эффективные каналы для
рекламных размещений, по приросту подписчиков,
ER, количеству просмотров на пост и другим метрикам
Анализируйте рекламные посты
и креативы
Узнайте какие посты лучше сработали,
а какие хуже, даже если их давно удалили
Оценивайте эффективность тематики и контента
Узнайте, какую тематику лучше не рекламировать
на канале, а какая зайдет на ура
Попробовать бесплатно
Показано 7 из 1 092 постов
Смотреть все посты
Пост от 06.06.2026 10:13
291
0
5
(የአሸዋ ሰጎን እና የሳሎን ውሻ)


የአሸዋ ሰጎን ለየት ያለ ትዕይት አለው ። ራሱን  በአሸዋ ውስጥ ይደብቃል ። ሙሉ ሰውነቱ ውጭ እንዳለ ራሱን ብቻ አሸዋ ውስጥ ይቀብራል ። ነፋስ ቢነሳ ፣ ቀውጢ ቢመጣ የሚሰሚው ጉዳይ አይኖር ራሱን አሸዋ ውስጥ ቀብሮ ይኖራል ። የበረታ ነፋስ ከመጣ ጠራርጎ  ይወስደዋል ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ባልሰማ ተደብቆ የቆየበት አሸዋ አያድነውም ።  የሳሎን ውሻ መላመድ ነው ባህሪው ፣ ከአሳዳጊው ስር ስር መሆን ፣ የመጣውን መልመድ ፣ አሳዳጊው ሳሎን ውስጥ መንጎራደድ መገለጫው ነው ።

ክርስትናንና ፖለቲካን ስንመለከት የአሸዋ ሰጎንና የሳሎን ውሻ መሆን አያዋጣም ። ቤተክርስቲያን እንደ አሸዋው ሰጎን ምንም አላቅም እያገባኝም ብላ ባልሰማ ባላየ ራሷን አሸዋ ውስጥ ብትደብቅ የሚመጣው ነፋስ የሞራል ውድቀት ፣ ጦርነት ፣ አምላክ የለሽ ስርአት ይሸረሽራታል ። እንደ ሳሎኑ ውሻው ፖለቲካን ለምዳ ለፖለቲካው ቤተኛ መሆን  የፖለቲካው ውድቀት ውድቀቷ፣ የፖለቲካው ግፍ ግፏ ፣ በደሉ በደሏ ይሆናል ፣ ምክኒያቱ ቤተኛ ሆናለች ።

ቤተክርስቲያን አያገባኝም በማለት እንደ ባለ አሸዋው ሰገን ባይተዋር ፤ እንደ ሳሎኑ ውሻ ሁሉ ያገባኛል በማለት ቤተኛ መሆን የተጠራችበት ተልዕኮ ያስረሳታል ።  ቤተክርስቲያን ለፖለቲካው ህሊና መሆን አለባት ። ህሊና ክፉንና ደጉን መመዘኛ ሚዛን ነው ። የፅድቅ መለኪያ እንደመሆኗ የተበላሸው ፖለቲካ ክፍቱቱን በፅድቋ  ትመዝናለች። ፖለቲካው ሲያጠፋ እረፉ የምትል ይሔ ግፍ ነው ብላ በደልን ክፋት የምታነቅፍ ፣ ደግሞ ስልጣን ከእግዚአብሔር ስለሆነ ፖለቲካው ውስጥ ገብታ የምትቆጣጠር ሳይሆን ማንም ይሁን አይሁን ፤ አማኝ ይሁን አይሁን የምትፀልይ ናት ። ቤተክርስቲያን በፖለቲካው ዙሪያ የሚኖሯት መፀሃፍ ቅዱሳዊ አቋም የስልጣን(power) ይገባኛል ላስተዳድረው ሳይሆን የፅድቅ አቋም ነው ።


@cgfsd
6
🔥 4
Пост от 06.06.2026 07:35
24
0
0
እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ ይገኛል፤ በልዩ ቦታም ይገኛል። በልዩነት የሚገኘው ግን ለህብረት ነው ።

@cgfsd
1
🔥 1
Пост от 05.06.2026 09:25
119
0
1
በክርስቶስ ቻናል 1500 እያለፍን ነው 😁 ። የበክርስቶስ ቤተሰቦች ስለ ቤተሰብነታችሁ እናመሰግናለን ።  ቻናሉ 8 አመት ሞልቶታል ። 8 አመት የመቆየቱን ያክል ብዙ አልሰራንበትም ። በቀጣዩ ጊዜ አሻሽለን በተከታታይነት መፀሃፍ ቅዱሳዊ መሰረት ያላቸውን ሀሳቦች ፣ ተልዕኮ ተኮር የሆኑ ፣ ወደ ተግባራዊ ህይወት (Devotional ) የሚጋብዙን ይዘት ያላቸውን ስራዎች ጨምረን ለመስራት እንሞክራለን ።

ቢሻሻል ፣ ቢጨምር ፣ ቢታረም ፣ ቢቀጥል የምትሉትን አስተያየታችሁን በዚህ በኩል 👉@filicross ሀሳባችሁን መስጠት ትችላላችሁ ።

@cgfsd
13
Пост от 04.06.2026 21:35
205
1
9
ምናልባት አንዳንዱን ነገር አጥርተን የምናየው በእምባ በረጠቡ አይኖቻችንስ ቢሆን?!


✍️ አበበ አብዲሳ
@cgfsd
17
👍 7
🤔 1
😢 1
Пост от 03.06.2026 21:50
247
0
4
ጌታዬ ድምፅህ ውስጥ ልብ አለ
 ለአፍታ የሰማህ እግርህ ስር ዋለ
አባቴ ልብህ ውስጥ ድምፅ አለ
አንተኑ ያገኘ ሸክምን ተካፈለ
15
🔥 4
Пост от 03.06.2026 08:55
280
0
1
(የመስቀል እሳቤ)


በቆሮንቶስ መፀሃፍ ሐዋሪያው ጳውሎስ መስቀልን የመስቀሉ ቃል በማለት መስቀሉን ይጠራል(1ቆሮ 1:18) ። ግሩም አገላለፅ ነው ። የመስቀሉ ቃል የመስቀሉ ስራ እንደማለት ነው  ። የመስቀሉ ቃል የመስቀሉ ስራ ተብሎ ሊገለፅ ይችላል ። ሐዋሪያው ጳውሎስ መስቀሉን ሲገልፅ ስለ አሰቃቀል ሂደቱ ወይም ስለ ቢስማሩ አልፎ ጅራፉን ሲጠቅስ ወይም ሲያነሳ አናይም ፤ ይልቁን የመስቀሉን ምክኒያት የመስቀሉን ስራ ውጤት ያብራራል ። መስቀል አንድ በቀራንዮ ላይ የተከናወነ የአንድ ቀን ክስተት ሳይሆን እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ውጤቱ የቀጠለና ምክኒያቱም ስለሰው ልጅ ድነት የሆነ አድርጎ ያስቀምጥልናል ። ለዚህም ነው የመስቀሉ ስራ ውጤትና ምክኒያት ላይ ትኩረት ስላደረገ ጳውሎስ የመስቀሉ ቃል የሚለውን ቃል ስለ መስቀል ስራው ወካይ አድርጎ ያስገባውል ። የመስቀሉ ቃል መስቀሉን የሚገልፅ ድንቅ ቃል ።

@cgfsd
9
Пост от 02.06.2026 17:36
79
0
0
(መንፈሱና መስቀሉ )


በቆሮንቶስ መፀሃፍ ላይ መስቀል ጥበበ እግዚአብሔር ነው ። መስቀል በቆሮንቶስ መፀሃፍ ላይ እንዴት ተገለጠ ብንል ጥበብ እግዚአብሔር የሚለው መልስ ገላጭ ሁኖ እናገኘዋለን ። መስቀል የእግዚአብሔር አስደናቂ ጥበብ እንደሆነ ስዕል ይስልናል ። ጥበቡም የእግዚአብሔር ሃይል ፣ እቅድ ፣ ርህራሄ ፣ ማዳን ፣ ፍቅር ፣ቸርነት ፣ የፀጋውን ባለጠግነት ፣ ልብ የሚገልጥ ጥበብ ነው ። እግዚአብሔር ለአለሙ ምስቅልቅል የሰጠው መልስ በጥበብ ነው እርሱም መስቀል ነው ። ጥበብ እንደመሆኑ መጠን መስቀል በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ ያለው ምክር ለመረዳት መንፈስ ቅዱስ ያስፈልጋል ። መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ጥልቅ ነገር የሚገለጥበት የእውነት መንፈስ ነው ። ስለዚህ የጥበቡን ጥልቀት ለመረዳት የመንፈሱ እርዳታ ያስፈልጋል ። መግለጥ የመንፈሱ ስራ ነውና ።  በቆሮንቶስ መፀሃፍ የመስቀሉን ጥበብነት ሲገልጥ በአይን ያልታየ፣ በሰው ልብ ያልታሰበ(1ቆሮ 2:5) በማለት እቅዱ የእግዚአብሔር ብቻና አስደናቂ  እንደሆነ ይነግረናል።  መንፈሱን ደግሞ በመስቀሉ ዙሪያ የሚኖረው ሚና ገላጭ ነው ይለናል ።
 
  ይሁን እንጂ፣ እንደ ተጻፈው፣
“ዐይን ያላየውን፣
ጆሮ ያልሰማውን፣
የሰውም ልብ ያላሰበውን፣
እግዚአብሔር ለሚወዱት አዘጋጅቶአል፤”
እግዚአብሔር ግን ይህን በመንፈሱ አማካይነት ለእኛ ገልጦልናል።
መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራል።  በውስጡ ካለው ከራሱ መንፈስ በስተቀር ከሰው መካከል የአንድን ሰው ሐሳብ የሚያውቅ ማን አለ? እንደዚሁም ከእግዚአብሔር መንፈስ በስተቀር፣ የእግዚአብሔርን ሐሳብ የሚያውቅ ማንም የለም።
1 ቆሮንቶስ 2:9-11

   በነገራችን ላይ ይሔ ጥቅስ ስለ መስቀሉ እንደሚያወራ ልብ ማለት ያስፈልጋል ።

የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነውን የመስቀል ስራ በመንፈሱ አብሪነትና አስረጂነት ይብራራል ። ጥልቅ የመስቀሉን እውነት ለመረዳት የመንፈሱ አስረጂነት ያስፈልጋል ።


@cgfsd
2
🔥 2
Смотреть все посты